እየው ስሙር ሲያሰምረው
ሲሆን ሲሆንማ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ማለት እንደ ደጉ ሳምራዊ ወንበዴዎች በተባሉ አጋንንት ተደብድበው ወድቀው መስማት መልማት ያልቻሉትንም አይቶ ማዘን፣ አዝኖ መቅረብ፣ ቀርቦ ቁስላቸውን ማጠብ፣ ወይንና ዘይት አድርጎ ማሠር፣ ማንሣት መሸከም የእንግዶች ማረፊያ ወደተባለች ቤተ ክርስቲያን አምጥቶ ማዳን ነበረ። አሁን ያለው ግን በግልባጭ ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን ማቅረብ ሳይሆን ድካም ያለበትን አውጥቶ ለመጣል መድከም፣ የወደቀ ማንሣት ሳይሆን የሚፍገመገመውን ለመጣል መታገል ነው። ይህም ሆኖ ደግሞ ራሳችን ችለን ያልቆምን ሰዎች የቆምን መስሎን መድከማችን ያሳዝናል። ቅዱስ ጳውሎስ "ማንም የቆመ የመሰለው ቢኖር እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ" ያለውም ትዝም አይለንም። እግዚአብሔር ልቡና ይስጠን።
ለሁሉም ስሙር የሆነ አሳብ ነውና ያስምርልን።
✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
ሲሆን ሲሆንማ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ማለት እንደ ደጉ ሳምራዊ ወንበዴዎች በተባሉ አጋንንት ተደብድበው ወድቀው መስማት መልማት ያልቻሉትንም አይቶ ማዘን፣ አዝኖ መቅረብ፣ ቀርቦ ቁስላቸውን ማጠብ፣ ወይንና ዘይት አድርጎ ማሠር፣ ማንሣት መሸከም የእንግዶች ማረፊያ ወደተባለች ቤተ ክርስቲያን አምጥቶ ማዳን ነበረ። አሁን ያለው ግን በግልባጭ ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን ማቅረብ ሳይሆን ድካም ያለበትን አውጥቶ ለመጣል መድከም፣ የወደቀ ማንሣት ሳይሆን የሚፍገመገመውን ለመጣል መታገል ነው። ይህም ሆኖ ደግሞ ራሳችን ችለን ያልቆምን ሰዎች የቆምን መስሎን መድከማችን ያሳዝናል። ቅዱስ ጳውሎስ "ማንም የቆመ የመሰለው ቢኖር እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ" ያለውም ትዝም አይለንም። እግዚአብሔር ልቡና ይስጠን።
ለሁሉም ስሙር የሆነ አሳብ ነውና ያስምርልን።
✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ