ምእመናን እንዲረዱ ማድረግ የሚገባን መሠረታዊውን የታምራትን አረዳድ ነው። ተአምር በቃ እንደ ተአምር የሚወስዱት መኾኑን ልብ ማለት ይገባል። መቼስ ተአምራትን እንደ ተለመደ ክስተት አድርገን ብቻ እንውሰዳቸው ካልን ትልቅ ችግር ውስጥ የምንገባ መኾኑን አንዘነጋም። አረዳዳችን ካልተስተካከለ ኦርቶዶክሳዊ መኾን አንችልም። ሕሊናችንን አበዋዊ ለማድረግ መጣር ይጠበቅብናል። የአበውን አረዳድ ትተን በኛ መጠን ልክ ብቻ ነገሮችን የምንቃኝ ከኾነ መጽሐፍ ቅዱስንም ቢኾን የመቀበል ዕድላችን አናስ ይኾናል። ስለዚህ በጣም በጥንቃቄ እና በእርጋታ በትሕትናም ኾኖ አካሄድን መመርመር ያስፈልጋል።
መርሳት የሌለብን ነገር "አዳኛችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ አምላክን ያለምንም እንከን የወለደች የአምላክ እናት እና ቅዱሳን የሚያደርጉትን ልዩ ተአምራት በንጽሕና፣ በፍጹም እምነት በፍጹም ነፍስና በፍጹም ልብ ኾነው የማይቀበሉ ነገር ግን ይህን ማድረግ አይችሉም በማለት የሚያሾፉ፣ በራሳቸውም ሐሳብ አጣመው የሚተረጒሙ፣ በራሳቸው ሐሳብ ብቻ የሚመዝኑ፣ ውግዘት የሚገባቸው መኾናቸውን የሚጠቁሙ ምንባባት ኹሉ አሉ። (The Synodikon of Orthodox)። በተአምረ ማርያም መቅድም ላይ ያለውንም ግዝት የምናውቀው ነው። ስለዚህ ስላልመሰለን ብቻ ቸኩለን ሌላ ባዕድ ነገር ለማምጣት ባንጥር መልካም ነው።
¤ በአዋልድ መጻሕፍት ውስጥ ያሉ ጸነን የሚሉ ምንባባት ይውጡን?
ጸነን የሚሉ ምንባባት ይውጡ ከማለት ይልቅ የሚሻለው አረዳዳቸውን ማወቅ ነው። ትክክል ቢኾኑ እንኳን ጸነን ስለሚሉ እያሉ በራስ የመረዳትና የማሰብ መጠን ልክ አድርጎ ማሰብ ወደ ከባድ ሌላ ስሕተት ሊወስድ ይችላልና። ኹሉን ነገር በራሱ መጠን ልክ አድርጎ ማሰብ የሚፈልግ ሰው እንዴት ኾኖ ኦርቶዶክስ ሊኾን ይችላል? ይህ ሰው ኋላ ሃይማኖትን በራሱ መጠን ልክ አድርጎ ወደ መረዳት እንደማይወርድ ማን እርግጠኛ ይኾናል? የአረዳድ መንገዱ ስሑት ከኾነ ያን አቅንቶ መሠረታዊ በኾነው የክርስትና ትምህርት መሠረት ላይ እምነቱን እንዲተክል ማድረግ ይገባል እንጂ እምነቱን በሥነ አመክንዮው ልክ አድርጎ እንዲያስብ የሚያደርግ በር መክፈት ተገቢ አይደለም።
ለምሳል "ፍጥረት ኹሉ እመቤታችንን ለማመስገን ተፈጠረ" የሚል ንባብ ያየ ሰው ኦርቶዶክሶች ቅድስት ድንግል ማርያም ያመልኳታል ከሚለው ቀድሞ በንጹሕ ልቡና አረዳዱን ይፈልጋል። አይ ይሄ ንባቡ ጸነን ይላልና ይውጣ ቢባል፤ ይህን አካሄድ የለመደ ሰው ምን ሊኾን ይችላል? ደረቅ ንባብ እያየ መልእክቱን ከመፈለግ ይልቅ ይጸናልና ይውጣ ወይም አልቀበልም ወደ ማለት አይወርድምን? እነ መርቅያንን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ቆነጻጽለው የሉቃስ ወንጌል ላይ ወስዶ የጣላቸው፣ እነ ሉተርን በሕሊናዬ ውስጥ ካለው ሐሳብ ጋር ይጋጫል ብሎ ከማሰብ የተነሣ የያዕቆብን መልእክት ገለባ መልእክት ለማለት የዳረገው ምን ኾኖ ኖሯል? ሌሎች ብዙ መናፍቃን እስካኹን ድረስ ውጭ አውጥቶ የጣላቸው ምንድን ነው? በራሳቸው ልክ መጥነው ማሰባቸውና የራሳቸውን አረዳድ እንዳለቀለት እውነት ማቅረባቸው አይደለምን?
ሊቁ አባ ጀሮም "መርቅያንና ባሲሊድስ፣ እና ሌሎችም መናፍቃን ኹሉ... የእግዚአብሔርን ወንጌል ገንዘብ አላደረጉም። ... ወንጌል ማለት ትርጒሙ (ሐሳቡ፣ መልእክቱ) ነው እንጂ ገጸ ንባቡ ነው ብለን አናስብም፤ በውጫዊ ቆዳው ሳይኾን በውስጣዊ ይዘቱ፣ በስብከቱ ቅጠሎቹ ላይ ሳይኾን በትርጒም ሥሩ ነው እንጂ። በዚህ ኹኔታ መጽሐፍ ቅዱስ ለሚያነቡትና ለሚሰሙት በእውነት የሚጠቅማቸው የሚኾነው ያለ ክርስቶስ የማይነገር ሲኾን ነው፥ ከአባቶች አስተምህሮና አረዳድ ሳይለይ የቀረበ ሲኾን ነው፥ የሚሰብኩት ሰዎች ያለ መንፈስ ቅዱስ የማይናገሩ ሲኾኑ ነው። ... የክርስቶስን ወንጌል በተጣመመ አተረጓጎም የሰዎች ወንጌል እንዳናደርግ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለ ጥንቃቄ መናገር ታላቅ አደጋ አለው።" እንዲል። (in Galat, I, 1. II. M.L. XXVI, c. 386) (ያረጋል አበጋዝ (ዲያቆን)፣ መድሎተ ጽድቅ ቅጽ 2፣ 2013 ዓም፣ ገጽ 176)። እንግዲህ አዋልድ መጻሕፍት የዐሥራው መጻሕፍት ልጆች ናቸው ካልን ልጅ አባቱን በሚመስልበት መንገድ እናየዋለን እንጂ በደረቁ ስሕተት ይገኝባቸዋልና እያልን ባላወቅነው ኹሉ በድፍረት መናገር ድፍረትም አለፈ ሲልም ነውርም ነው።
የአንድን ሰው አረዳዱን ኦርቶዶክሳዊ እስካላደረግነው ድረስ ምንም ያህል ዝቅ ብንል ላይረዳ ይችላል። ከዚያ ይልቅ ራሱን ብቁ ገምጋሚና አስተካካይ፤ የሃይማኖታዊ ጉዳይ ሚዛን በማድረግ ስሕተት ውስጥ እንዳይወድቅ ልንጠነቀቅለት ይገባል። መሠረታዊውን አስተምህሮ የተረዳ ነው፤ ምንም ነገር አያናውጸውም። የተኛውንም ንባብ ከወንጌል እውነታ አንጻር ነው የሚያየው እንጂ በውስጡ ባለ ምናባዊ ሥዕል ችግር አይፈጥርም። አምላክ ሰው ኾነ የሚለው እኛን የማይረብሸን ሙስሊሞችን ግን ለመቀበል የሚከብዳቸው በእነርሱ መጠን ውስጥ አድርገው ስለሚያስቡት ነው። የማስረጃ ዓይነት ቢጠቀስላቸው እንደ ተረት የሚቆጥሩት የተዘጋ አረዳድ ስላለ ነው። ይህን ዝግ የኾነ አረዳድ ካልከፈትንላቸው ነጻ ሊወጡ አይችሉም። ልክ እንዲሁም የኑፋቄ ዝናም ዘንቦባቸው፣ የክሕደት ጎርፍ ውስዷቸው ከእውነተኛው በረት ውጭ የነበሩ አካላትም መጀመሪያ ማጥራት ያለባቸው አረዳዳቸውን ነው። ንባብ ላይ ብቻ እየሄዱ መለጠፍን ማቆም አለባቸው። "ንባብ ይቀትል ወትርጓሜ የሐዩ ሕይወተ" ንባብ ይገድላል ትርጓሜ ሕይወትን ይሰጣል የሚለውን ልብ ይበሉት።
ይህን አካሄድ ትተን ይህን አልቀበልም ይውጣ ይጸናል ዓይነት አካሄድ ከጀመርን ለኔ የሚታየኝ መርቅያን ነው። ጌታችን "በኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ያደርጋል፤ ከእኔም የሚበልጥ ያደርጋል" ሲል ስናነብ ይህ በጣም ይጸናል፤ ተገላበጠ እኮ! ፍጡር ፈጣሪ የሚያደርገን እንዴት ያደርጋል? ከዚያም ብሶ ፈጣሪ ከሚያደርገው በላይ ያደርጋል ይባላልን? ኧረ ይሄስ ይውጣ ሊባል ነውን? "ሰላምን ላመጣ የመጣው አይምሰላችሁ ሰይፍን እንጂ" ሲል ስናነብ እንዴ ጨካኝ ነው ማለት ነውን? ይህን እንዴት ያደርጋል ልንል ነውን? "ከኔ አብ ይበልጣል" ሲል ታዲያ ከአብ የሚያንስ ከኾነ እንዴት ልናመልከው እንችላለን? ይህ ንባብ ያሰናክላልና በሌላ ግልጽ ንባብ ይቀየርልን ልንል ነውን? ጌታ በወንጌል "ነገር ግን እነዚያን በላያቸው ልነግሥ ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጧቸው በፊቴም እረዱአቸው" ሉቃ 19፥27 ስላለ ግድያን እየበረታታ ነውና ይህ ምንባብ ይውጣ ይባላልን?
መዝ 136፥9 "ሕፃናቶችሽን በዓለት ላይ የሚፈጠፍጥ ብፁዕ ነው" ይላል። ይህ ንባብ ጸነን ያለ ነውና ለመረዳት ስለሚያስቸግር ይውጣ ሊባል ነውን? "ኀጥእ የጻድቅ ቤዛ ነው፤ በደለኛም የቅን ሰው ቤዛ ነው፡፡" ይላል መጽሐፍ ቅዱስ፡፡ ምሳ 21፡18፡፡ ኀጥእ እንዴት የጻድቅ ቤዛ ነው ይባላል? ስንኳንስ ኀጥእ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ጻድቃን ስንኳን ቤዛ አይባል ይሉ የነበሩ ይህን ንባብ እንዴት ሊቀበሉ ይችላሉ? እንግዲህ እንዲህ እያልን ከሄድን የሚቀረን ምንድን ነው? የምንደርሰውስ ወዴት ነው? ስለዚህ ጭንቀታችን መኾን ያለበት ንባብ ላይ ሳይኾን አረዳድ ላይ ነው ሊኾን የሚገባው።
መርሳት የሌለብን ነገር "አዳኛችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ አምላክን ያለምንም እንከን የወለደች የአምላክ እናት እና ቅዱሳን የሚያደርጉትን ልዩ ተአምራት በንጽሕና፣ በፍጹም እምነት በፍጹም ነፍስና በፍጹም ልብ ኾነው የማይቀበሉ ነገር ግን ይህን ማድረግ አይችሉም በማለት የሚያሾፉ፣ በራሳቸውም ሐሳብ አጣመው የሚተረጒሙ፣ በራሳቸው ሐሳብ ብቻ የሚመዝኑ፣ ውግዘት የሚገባቸው መኾናቸውን የሚጠቁሙ ምንባባት ኹሉ አሉ። (The Synodikon of Orthodox)። በተአምረ ማርያም መቅድም ላይ ያለውንም ግዝት የምናውቀው ነው። ስለዚህ ስላልመሰለን ብቻ ቸኩለን ሌላ ባዕድ ነገር ለማምጣት ባንጥር መልካም ነው።
¤ በአዋልድ መጻሕፍት ውስጥ ያሉ ጸነን የሚሉ ምንባባት ይውጡን?
ጸነን የሚሉ ምንባባት ይውጡ ከማለት ይልቅ የሚሻለው አረዳዳቸውን ማወቅ ነው። ትክክል ቢኾኑ እንኳን ጸነን ስለሚሉ እያሉ በራስ የመረዳትና የማሰብ መጠን ልክ አድርጎ ማሰብ ወደ ከባድ ሌላ ስሕተት ሊወስድ ይችላልና። ኹሉን ነገር በራሱ መጠን ልክ አድርጎ ማሰብ የሚፈልግ ሰው እንዴት ኾኖ ኦርቶዶክስ ሊኾን ይችላል? ይህ ሰው ኋላ ሃይማኖትን በራሱ መጠን ልክ አድርጎ ወደ መረዳት እንደማይወርድ ማን እርግጠኛ ይኾናል? የአረዳድ መንገዱ ስሑት ከኾነ ያን አቅንቶ መሠረታዊ በኾነው የክርስትና ትምህርት መሠረት ላይ እምነቱን እንዲተክል ማድረግ ይገባል እንጂ እምነቱን በሥነ አመክንዮው ልክ አድርጎ እንዲያስብ የሚያደርግ በር መክፈት ተገቢ አይደለም።
ለምሳል "ፍጥረት ኹሉ እመቤታችንን ለማመስገን ተፈጠረ" የሚል ንባብ ያየ ሰው ኦርቶዶክሶች ቅድስት ድንግል ማርያም ያመልኳታል ከሚለው ቀድሞ በንጹሕ ልቡና አረዳዱን ይፈልጋል። አይ ይሄ ንባቡ ጸነን ይላልና ይውጣ ቢባል፤ ይህን አካሄድ የለመደ ሰው ምን ሊኾን ይችላል? ደረቅ ንባብ እያየ መልእክቱን ከመፈለግ ይልቅ ይጸናልና ይውጣ ወይም አልቀበልም ወደ ማለት አይወርድምን? እነ መርቅያንን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ቆነጻጽለው የሉቃስ ወንጌል ላይ ወስዶ የጣላቸው፣ እነ ሉተርን በሕሊናዬ ውስጥ ካለው ሐሳብ ጋር ይጋጫል ብሎ ከማሰብ የተነሣ የያዕቆብን መልእክት ገለባ መልእክት ለማለት የዳረገው ምን ኾኖ ኖሯል? ሌሎች ብዙ መናፍቃን እስካኹን ድረስ ውጭ አውጥቶ የጣላቸው ምንድን ነው? በራሳቸው ልክ መጥነው ማሰባቸውና የራሳቸውን አረዳድ እንዳለቀለት እውነት ማቅረባቸው አይደለምን?
ሊቁ አባ ጀሮም "መርቅያንና ባሲሊድስ፣ እና ሌሎችም መናፍቃን ኹሉ... የእግዚአብሔርን ወንጌል ገንዘብ አላደረጉም። ... ወንጌል ማለት ትርጒሙ (ሐሳቡ፣ መልእክቱ) ነው እንጂ ገጸ ንባቡ ነው ብለን አናስብም፤ በውጫዊ ቆዳው ሳይኾን በውስጣዊ ይዘቱ፣ በስብከቱ ቅጠሎቹ ላይ ሳይኾን በትርጒም ሥሩ ነው እንጂ። በዚህ ኹኔታ መጽሐፍ ቅዱስ ለሚያነቡትና ለሚሰሙት በእውነት የሚጠቅማቸው የሚኾነው ያለ ክርስቶስ የማይነገር ሲኾን ነው፥ ከአባቶች አስተምህሮና አረዳድ ሳይለይ የቀረበ ሲኾን ነው፥ የሚሰብኩት ሰዎች ያለ መንፈስ ቅዱስ የማይናገሩ ሲኾኑ ነው። ... የክርስቶስን ወንጌል በተጣመመ አተረጓጎም የሰዎች ወንጌል እንዳናደርግ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለ ጥንቃቄ መናገር ታላቅ አደጋ አለው።" እንዲል። (in Galat, I, 1. II. M.L. XXVI, c. 386) (ያረጋል አበጋዝ (ዲያቆን)፣ መድሎተ ጽድቅ ቅጽ 2፣ 2013 ዓም፣ ገጽ 176)። እንግዲህ አዋልድ መጻሕፍት የዐሥራው መጻሕፍት ልጆች ናቸው ካልን ልጅ አባቱን በሚመስልበት መንገድ እናየዋለን እንጂ በደረቁ ስሕተት ይገኝባቸዋልና እያልን ባላወቅነው ኹሉ በድፍረት መናገር ድፍረትም አለፈ ሲልም ነውርም ነው።
የአንድን ሰው አረዳዱን ኦርቶዶክሳዊ እስካላደረግነው ድረስ ምንም ያህል ዝቅ ብንል ላይረዳ ይችላል። ከዚያ ይልቅ ራሱን ብቁ ገምጋሚና አስተካካይ፤ የሃይማኖታዊ ጉዳይ ሚዛን በማድረግ ስሕተት ውስጥ እንዳይወድቅ ልንጠነቀቅለት ይገባል። መሠረታዊውን አስተምህሮ የተረዳ ነው፤ ምንም ነገር አያናውጸውም። የተኛውንም ንባብ ከወንጌል እውነታ አንጻር ነው የሚያየው እንጂ በውስጡ ባለ ምናባዊ ሥዕል ችግር አይፈጥርም። አምላክ ሰው ኾነ የሚለው እኛን የማይረብሸን ሙስሊሞችን ግን ለመቀበል የሚከብዳቸው በእነርሱ መጠን ውስጥ አድርገው ስለሚያስቡት ነው። የማስረጃ ዓይነት ቢጠቀስላቸው እንደ ተረት የሚቆጥሩት የተዘጋ አረዳድ ስላለ ነው። ይህን ዝግ የኾነ አረዳድ ካልከፈትንላቸው ነጻ ሊወጡ አይችሉም። ልክ እንዲሁም የኑፋቄ ዝናም ዘንቦባቸው፣ የክሕደት ጎርፍ ውስዷቸው ከእውነተኛው በረት ውጭ የነበሩ አካላትም መጀመሪያ ማጥራት ያለባቸው አረዳዳቸውን ነው። ንባብ ላይ ብቻ እየሄዱ መለጠፍን ማቆም አለባቸው። "ንባብ ይቀትል ወትርጓሜ የሐዩ ሕይወተ" ንባብ ይገድላል ትርጓሜ ሕይወትን ይሰጣል የሚለውን ልብ ይበሉት።
ይህን አካሄድ ትተን ይህን አልቀበልም ይውጣ ይጸናል ዓይነት አካሄድ ከጀመርን ለኔ የሚታየኝ መርቅያን ነው። ጌታችን "በኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ያደርጋል፤ ከእኔም የሚበልጥ ያደርጋል" ሲል ስናነብ ይህ በጣም ይጸናል፤ ተገላበጠ እኮ! ፍጡር ፈጣሪ የሚያደርገን እንዴት ያደርጋል? ከዚያም ብሶ ፈጣሪ ከሚያደርገው በላይ ያደርጋል ይባላልን? ኧረ ይሄስ ይውጣ ሊባል ነውን? "ሰላምን ላመጣ የመጣው አይምሰላችሁ ሰይፍን እንጂ" ሲል ስናነብ እንዴ ጨካኝ ነው ማለት ነውን? ይህን እንዴት ያደርጋል ልንል ነውን? "ከኔ አብ ይበልጣል" ሲል ታዲያ ከአብ የሚያንስ ከኾነ እንዴት ልናመልከው እንችላለን? ይህ ንባብ ያሰናክላልና በሌላ ግልጽ ንባብ ይቀየርልን ልንል ነውን? ጌታ በወንጌል "ነገር ግን እነዚያን በላያቸው ልነግሥ ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጧቸው በፊቴም እረዱአቸው" ሉቃ 19፥27 ስላለ ግድያን እየበረታታ ነውና ይህ ምንባብ ይውጣ ይባላልን?
መዝ 136፥9 "ሕፃናቶችሽን በዓለት ላይ የሚፈጠፍጥ ብፁዕ ነው" ይላል። ይህ ንባብ ጸነን ያለ ነውና ለመረዳት ስለሚያስቸግር ይውጣ ሊባል ነውን? "ኀጥእ የጻድቅ ቤዛ ነው፤ በደለኛም የቅን ሰው ቤዛ ነው፡፡" ይላል መጽሐፍ ቅዱስ፡፡ ምሳ 21፡18፡፡ ኀጥእ እንዴት የጻድቅ ቤዛ ነው ይባላል? ስንኳንስ ኀጥእ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ጻድቃን ስንኳን ቤዛ አይባል ይሉ የነበሩ ይህን ንባብ እንዴት ሊቀበሉ ይችላሉ? እንግዲህ እንዲህ እያልን ከሄድን የሚቀረን ምንድን ነው? የምንደርሰውስ ወዴት ነው? ስለዚህ ጭንቀታችን መኾን ያለበት ንባብ ላይ ሳይኾን አረዳድ ላይ ነው ሊኾን የሚገባው።