Church and Civil Laws, 13th Century A.D. page 6) (ሄኖክ ኃይሌ (ዲ/ን)፣ ተአምረ ማርያምና አንዳንድ ጉዳዮች)
- በራእየ ማርያም ውስጥ የዘረኝነት በሽታ የጸናበት አካል ያልኾነ ሥርዋጽ አስገብቷል። ራእየ ማርያም መጀመሪያ የተጻፈው በግሪክ ሲኾን ወደ ሀገራችን ከመምጣቱ በፊት ወደ ዐረብኛ ተተርጉሟል። ከ39 በላይ የራእየ ማርያም ቅጂዎች ይገኛሉ። ወደ አማርኛ የተተረጎሙ የ1961 የተስፋ ገብረ ሥላሴ ትርጉም ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ አላገኘኹትም ይላሉ። 1985 በተስፋ ገብረ ሥላሴ የተተረጎመ እና በ2007 በአክሱም ማተሚያ የተተረጎመ አመሳክረው ጥናት አቅርበዋል። (አምሳሉ ተፈራ (ቀሲስ፡ ዶ/ር)፣ ነቅዓ መጻሕፍት፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 294-302)
- "ማክሰኞና ሐሙስ እባብን የገደለ እንደ ዐርባ ቀን ሕፃን ይኾናል" የሚል ትምህርት የመጣው በደብረ አስቦ ለነበሩ ገዳማውያን ዋናዎቹ ፈተናዎች እባብና ዘንዶ ስለ ነበሩ ነው። በዚያ ዘመን ዕባቡንና ዘንዶውን መታገሥ፣ አልፎም ማጥፋት ጽናትን ማሳያ ነበርና። (ዳንኤል ክብረት፣ ኢትዮጵያዊው ሱራፊ፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 660፣ የግርጌ ማስታወሻ 1974)። ይህ አባባል በመጀመሪያ ቅጅ ላይ የለም፤ ሥርዋፅ ኾኖ የገባው ኋላ ነው። የገባው ግን ከላይ የተገለጸውን ሐሳብ ለማስጠበቅ ነበር። መናፍቃን ግን ይህን ለጥጠው "እባብን የገደለ ይጸድቃል" እያልን እንደ ኾነ ለማስቆጠር ይጥራሉ። ይህ ግን Straw man Fallacy (ያልተባለን ነገር እንደ ተባለ አድርጎ የማሰብ ስሕተት) ነው። ይህ አካሄድ ቅንነት የሌለው ጥላቻንና ማነወርን ማዕከል ያደረገ ስሑት አካሄድ ነው።
- በዚቅ ላይ ደግሞ "ኦ አምላክ መርቆሬዎስ ዘአሠርገውከ ሰማየ " የሚል ንባብ በሥርዋፅ ገብቶ መገኘቱን ልብ እንላለን። የተሐድሶ መናፍቃንም እንዲህ ብለን እንደማናምንና ይህ ሥርዋፅ እንደ ኾነ ቢረዱም የመስማት ፍላጎት የሌላቸውና እነርሱ የሚሉትን ብቻ እንድንቀበል የሚፈልጉ ስሑታን ስለ ነበሩ ያልኾኑ ነገሮችን ሲያራግቡ ተመልክተናል። ሌሎችም ይህን የመሰሉ ጉዳዮች ሊገኙ ይችላሉ። ያን ኦርቶዶክሳዊ በኾነ መንገድ በጉዳዩ ላይ በሥርዓትና በጥንቃቄ ጥናት ለሚያደርጉ በጉዳዩ ብዙ ለቆዩበት ለነ ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ ዓይነት ለቀቅ ብናደርግ መልካም ነው። በኹሉ ነገር ላይ ራስን አዋቂ አድርጎ ያውም በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ንባብና ጥናት ሳያደርጉ ኦርቶዶክሳዊ ባልኾነ መንገድ አዋልድ መጻሕፍትን እያዩ ደረቅ ትችት ማቅረብ አግባብ አይደለም። ደረጃን እና አቅምን በመረዳት በማያውቁት ነገር በመሰለኝ ከማውራት እንቆጠብና ብዙ ዓመታትን በሥነ ድርሳናት ለቆዩት አካላት በአክብሮት ቦታውን ለቀቅ ብናደርግ መልካም ነው። በችኩልነትና በድርቅና የቤተ ክርስቲያን አረዳድ ኹሉ በኔ በር በኲል ሲያልፉ ነው የሚያገኙት ከሚያሰኝ አካሄድ ብንቆጠብ መልካም ነው።
የአዋልድ መጻሕፍት ምንነት፣ ዓይነት፣ ጥቅም ...! እንዳይሰፋ ትቼው እነሆ ይህን አቀረብኹላችሁ።
✍️ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው እንደጻፈው
- በራእየ ማርያም ውስጥ የዘረኝነት በሽታ የጸናበት አካል ያልኾነ ሥርዋጽ አስገብቷል። ራእየ ማርያም መጀመሪያ የተጻፈው በግሪክ ሲኾን ወደ ሀገራችን ከመምጣቱ በፊት ወደ ዐረብኛ ተተርጉሟል። ከ39 በላይ የራእየ ማርያም ቅጂዎች ይገኛሉ። ወደ አማርኛ የተተረጎሙ የ1961 የተስፋ ገብረ ሥላሴ ትርጉም ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ አላገኘኹትም ይላሉ። 1985 በተስፋ ገብረ ሥላሴ የተተረጎመ እና በ2007 በአክሱም ማተሚያ የተተረጎመ አመሳክረው ጥናት አቅርበዋል። (አምሳሉ ተፈራ (ቀሲስ፡ ዶ/ር)፣ ነቅዓ መጻሕፍት፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 294-302)
- "ማክሰኞና ሐሙስ እባብን የገደለ እንደ ዐርባ ቀን ሕፃን ይኾናል" የሚል ትምህርት የመጣው በደብረ አስቦ ለነበሩ ገዳማውያን ዋናዎቹ ፈተናዎች እባብና ዘንዶ ስለ ነበሩ ነው። በዚያ ዘመን ዕባቡንና ዘንዶውን መታገሥ፣ አልፎም ማጥፋት ጽናትን ማሳያ ነበርና። (ዳንኤል ክብረት፣ ኢትዮጵያዊው ሱራፊ፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 660፣ የግርጌ ማስታወሻ 1974)። ይህ አባባል በመጀመሪያ ቅጅ ላይ የለም፤ ሥርዋፅ ኾኖ የገባው ኋላ ነው። የገባው ግን ከላይ የተገለጸውን ሐሳብ ለማስጠበቅ ነበር። መናፍቃን ግን ይህን ለጥጠው "እባብን የገደለ ይጸድቃል" እያልን እንደ ኾነ ለማስቆጠር ይጥራሉ። ይህ ግን Straw man Fallacy (ያልተባለን ነገር እንደ ተባለ አድርጎ የማሰብ ስሕተት) ነው። ይህ አካሄድ ቅንነት የሌለው ጥላቻንና ማነወርን ማዕከል ያደረገ ስሑት አካሄድ ነው።
- በዚቅ ላይ ደግሞ "ኦ አምላክ መርቆሬዎስ ዘአሠርገውከ ሰማየ " የሚል ንባብ በሥርዋፅ ገብቶ መገኘቱን ልብ እንላለን። የተሐድሶ መናፍቃንም እንዲህ ብለን እንደማናምንና ይህ ሥርዋፅ እንደ ኾነ ቢረዱም የመስማት ፍላጎት የሌላቸውና እነርሱ የሚሉትን ብቻ እንድንቀበል የሚፈልጉ ስሑታን ስለ ነበሩ ያልኾኑ ነገሮችን ሲያራግቡ ተመልክተናል። ሌሎችም ይህን የመሰሉ ጉዳዮች ሊገኙ ይችላሉ። ያን ኦርቶዶክሳዊ በኾነ መንገድ በጉዳዩ ላይ በሥርዓትና በጥንቃቄ ጥናት ለሚያደርጉ በጉዳዩ ብዙ ለቆዩበት ለነ ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ ዓይነት ለቀቅ ብናደርግ መልካም ነው። በኹሉ ነገር ላይ ራስን አዋቂ አድርጎ ያውም በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ንባብና ጥናት ሳያደርጉ ኦርቶዶክሳዊ ባልኾነ መንገድ አዋልድ መጻሕፍትን እያዩ ደረቅ ትችት ማቅረብ አግባብ አይደለም። ደረጃን እና አቅምን በመረዳት በማያውቁት ነገር በመሰለኝ ከማውራት እንቆጠብና ብዙ ዓመታትን በሥነ ድርሳናት ለቆዩት አካላት በአክብሮት ቦታውን ለቀቅ ብናደርግ መልካም ነው። በችኩልነትና በድርቅና የቤተ ክርስቲያን አረዳድ ኹሉ በኔ በር በኲል ሲያልፉ ነው የሚያገኙት ከሚያሰኝ አካሄድ ብንቆጠብ መልካም ነው።
የአዋልድ መጻሕፍት ምንነት፣ ዓይነት፣ ጥቅም ...! እንዳይሰፋ ትቼው እነሆ ይህን አቀረብኹላችሁ።
✍️ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው እንደጻፈው