................የአክሊል ጉዳይ "..............
መፍትኄ ብትሆን ብየ ነው። አስተምህሮ ከሚለጠጥ
ከላይ የምንሰማው አንድ ድምጽ የለንም?
ስለ ወንድማችን አክሊል ቲክቶከሩም ፤ ዩትዩበሩም ልጁ ያለውንም ያላለውንም እየጨመረ እያውራ ሰዎች ከሚጨነቁ ፤ አስተምህሮዎችም በሆነ ባልሆነው ከሚንገላቱ አጭር መፍትኄ የለንም እንዴ ? አንዳንዴ የገበያ ግር ግር ለቀጣፊ ይመቻል እንዳይሆን እና ምናልባት ጉዳዩን አዠንዳ አድርጎ የሰጠን ይኖር ይሆን?ብሎ ቆም ብሎ ማሰብም ተገቢ ይመስለኛል ።
1ኛ የሊቃውንት ጉባኤ ውስጥ የሚሰሩ አባቶቻችን ልጁን ቀን ሰጥተው ፤ በፍቅር ጠርተው እርሱም ተዘጋጅቶ ፦ ከጉባኤ መምህራንም ፤ ከቲኦሎጅ መምህራንም ፤ በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ ከሚያገለግሉ ከምናውቃቸው ታላላቅ መምህራንም በቅርቡ ያሉ
አንድ ስድስት መምህራን ተጠርተው ሀሳቡን አቅርቦ በመጽሐፍ ቅዱስ ፤ በአበው አስተምህሮ ታይቶ ተመርምሮ
ባቋጭስ? ምክንያቱም እርሱም ለመታረም ዝግጁ ነኝ ያለ መስሎኛል ። ከአካሄዱ ጀምሮ የሚታረመውን አርሞ ፦ ልክ የሆነውን ልክ ነው ብሎ ፦ ልክ ያልሆነውን ሕዝቡ ሲሰማው ስለቆየ እርሱም እራሱ በራሱ ምክንያት አንድ ሰው ቢሰናከልበት ስለሚያስጠይቀው ፈቃደኛ ሁኖ ተወያይቶ ቢዘጋ ምን ችግር አለው ?
የሊቃውንት ጉባኤ አባላት አባቶቻችን ጉዳዩ ከሆነች ጎጆ ውስጥ ያሉ ሰዎች ጩኸት ብቻ አይደለም። ከሀገር ውስጥ እስከ ሀገር ውጭ ደርሷል። ይህንን አዠንዳ ማስተካከል እንዴት ተሳነው? ለልጁም ለቤተ ክርስቲያኗም እረፍት ነው። ሁሌም ከኔ ጀምሮ በያንዳንዱ አፍ ሲባረክ ሲረገም ከሚውል " እራሱ በተገኘበት ውይይቱ ሲጠናቀቅ ራሱም በዚህ ሀሳብ ልክ አይደለሁም እንዲል። ልክ የሆነበት ሀሳብ ደግሞ ይሄ ሰዎች እያጣመሙበት ወይም ያለ መረዳዳት ችግር እንጅ ልክ ነው ቢባል ምናለ?
↗️ ለቤ/ክርስቲያኗም ለምእመንም እኮ እረፍት ነበር ።እኔ ምድያ ላይ ተወያይቶ ከወደታች የኮሜንት በረዶ እየወረደ ምድያ ላይ ችግርን ማረምም ሆነ ማስተካከል የሚቻል አይመስለኝም ። የሀሳቡን ልብም ማግኘት አይቻልም። ምድያ ላይ የተሰራጨን ሁሉ በዚያው በምድያ ማስተካከል ጥሩ ነው። ነገር ግን ለማስተካከል ይ
የምንጓዝበትን ጉዞ ሁሉ በምድያ ማድረጉ አግባብ ውጤታማ አይመስለኝም። መፍትኄው ከተገኘ እና ከመረዳዳት በኋላ ከጅግሩ እስከ መፍትኄው በምድያ ማቅረብ የበለጠ ነው።ችግሩን ለይቶ ለማወቅም ለማሳወቅም ከዚያው ምድያ ላይ ከሆነ ግን ችግርን ጨምሮ ያርፋርል እንጅ ችግርን አይፈታም ።
↗️ በአጭሩ የሚቋጭ ቢሆን የእስከ ዛሬው የመምህራኑ ጥረት በቂ ነበርና። ለሁሉም ይህ ሁሉ ክርክር ለምን መጣ? ብላችሁ የምትደነግጡ ? የምትሸበሩ ምእመናን ትኖሩ ይሆን? ይህ የሆነው ሃይማኖታችሁ ድንቅ እጹብ ቢሆን ነው። የማርያም ነገር እንዲህ ነው ።መላእክት እንኳን ተጨምረው ቢያስቡት በእርሷ የተከናወነው ምሥጢር ክቡድ ነው። ሃይማኖታችሁ እንዲህ ነው።የማርያም ነገር ዛፎች ተሰብስበው ስለ እርሷ ቢያጨበጭቡ!! ተራሮች ተከማችተው ስለ ክብሯ ቢዘምሩ" የራሳችን ጠጒሮች አንድ ሁነው ቢያሸበሽቡ የማርያም ነገር የድንቅ ድንቅ ነው። ሃይማኖታችሁ ተራ ተረት ተረት አይደለም። ከሕሊና በላይ ነው።የማርያም ነገርም እንዲሁ ነው። ወላዕለ ኲሉ ሕሊና አይደለች። ማርያም ታማልዳለች አታማልድም ማለት ብቻ ሳይሆን በነገረ ድኅነት ያላት ድንቅ ሱታፌም እንደ ፋና ሲያበራ ይታያል።
አንድ ሊቅ ባለፈው በየ ዘመኑ በጥባጭ ጸሐፊ በጥባጭ ሊቅ መነሳት አለባት ያሉት ትዝ አለኝ። በጥባጭ መናፍቅ አይነሳ እንጅ በጥባጭ ሊቅማ ይነሳ። እንዲህ ያነቃቃልና። በስንፍና የረጋውን ሁከት መንፈሳዊ ሰጥቶ ይቀሰቅሰዋልና።
መምህር ጽጌ አስተርአየ እንደጻፉት
መፍትኄ ብትሆን ብየ ነው። አስተምህሮ ከሚለጠጥ
ከላይ የምንሰማው አንድ ድምጽ የለንም?
ስለ ወንድማችን አክሊል ቲክቶከሩም ፤ ዩትዩበሩም ልጁ ያለውንም ያላለውንም እየጨመረ እያውራ ሰዎች ከሚጨነቁ ፤ አስተምህሮዎችም በሆነ ባልሆነው ከሚንገላቱ አጭር መፍትኄ የለንም እንዴ ? አንዳንዴ የገበያ ግር ግር ለቀጣፊ ይመቻል እንዳይሆን እና ምናልባት ጉዳዩን አዠንዳ አድርጎ የሰጠን ይኖር ይሆን?ብሎ ቆም ብሎ ማሰብም ተገቢ ይመስለኛል ።
1ኛ የሊቃውንት ጉባኤ ውስጥ የሚሰሩ አባቶቻችን ልጁን ቀን ሰጥተው ፤ በፍቅር ጠርተው እርሱም ተዘጋጅቶ ፦ ከጉባኤ መምህራንም ፤ ከቲኦሎጅ መምህራንም ፤ በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ ከሚያገለግሉ ከምናውቃቸው ታላላቅ መምህራንም በቅርቡ ያሉ
አንድ ስድስት መምህራን ተጠርተው ሀሳቡን አቅርቦ በመጽሐፍ ቅዱስ ፤ በአበው አስተምህሮ ታይቶ ተመርምሮ
ባቋጭስ? ምክንያቱም እርሱም ለመታረም ዝግጁ ነኝ ያለ መስሎኛል ። ከአካሄዱ ጀምሮ የሚታረመውን አርሞ ፦ ልክ የሆነውን ልክ ነው ብሎ ፦ ልክ ያልሆነውን ሕዝቡ ሲሰማው ስለቆየ እርሱም እራሱ በራሱ ምክንያት አንድ ሰው ቢሰናከልበት ስለሚያስጠይቀው ፈቃደኛ ሁኖ ተወያይቶ ቢዘጋ ምን ችግር አለው ?
የሊቃውንት ጉባኤ አባላት አባቶቻችን ጉዳዩ ከሆነች ጎጆ ውስጥ ያሉ ሰዎች ጩኸት ብቻ አይደለም። ከሀገር ውስጥ እስከ ሀገር ውጭ ደርሷል። ይህንን አዠንዳ ማስተካከል እንዴት ተሳነው? ለልጁም ለቤተ ክርስቲያኗም እረፍት ነው። ሁሌም ከኔ ጀምሮ በያንዳንዱ አፍ ሲባረክ ሲረገም ከሚውል " እራሱ በተገኘበት ውይይቱ ሲጠናቀቅ ራሱም በዚህ ሀሳብ ልክ አይደለሁም እንዲል። ልክ የሆነበት ሀሳብ ደግሞ ይሄ ሰዎች እያጣመሙበት ወይም ያለ መረዳዳት ችግር እንጅ ልክ ነው ቢባል ምናለ?
↗️ ለቤ/ክርስቲያኗም ለምእመንም እኮ እረፍት ነበር ።እኔ ምድያ ላይ ተወያይቶ ከወደታች የኮሜንት በረዶ እየወረደ ምድያ ላይ ችግርን ማረምም ሆነ ማስተካከል የሚቻል አይመስለኝም ። የሀሳቡን ልብም ማግኘት አይቻልም። ምድያ ላይ የተሰራጨን ሁሉ በዚያው በምድያ ማስተካከል ጥሩ ነው። ነገር ግን ለማስተካከል ይ
የምንጓዝበትን ጉዞ ሁሉ በምድያ ማድረጉ አግባብ ውጤታማ አይመስለኝም። መፍትኄው ከተገኘ እና ከመረዳዳት በኋላ ከጅግሩ እስከ መፍትኄው በምድያ ማቅረብ የበለጠ ነው።ችግሩን ለይቶ ለማወቅም ለማሳወቅም ከዚያው ምድያ ላይ ከሆነ ግን ችግርን ጨምሮ ያርፋርል እንጅ ችግርን አይፈታም ።
↗️ በአጭሩ የሚቋጭ ቢሆን የእስከ ዛሬው የመምህራኑ ጥረት በቂ ነበርና። ለሁሉም ይህ ሁሉ ክርክር ለምን መጣ? ብላችሁ የምትደነግጡ ? የምትሸበሩ ምእመናን ትኖሩ ይሆን? ይህ የሆነው ሃይማኖታችሁ ድንቅ እጹብ ቢሆን ነው። የማርያም ነገር እንዲህ ነው ።መላእክት እንኳን ተጨምረው ቢያስቡት በእርሷ የተከናወነው ምሥጢር ክቡድ ነው። ሃይማኖታችሁ እንዲህ ነው።የማርያም ነገር ዛፎች ተሰብስበው ስለ እርሷ ቢያጨበጭቡ!! ተራሮች ተከማችተው ስለ ክብሯ ቢዘምሩ" የራሳችን ጠጒሮች አንድ ሁነው ቢያሸበሽቡ የማርያም ነገር የድንቅ ድንቅ ነው። ሃይማኖታችሁ ተራ ተረት ተረት አይደለም። ከሕሊና በላይ ነው።የማርያም ነገርም እንዲሁ ነው። ወላዕለ ኲሉ ሕሊና አይደለች። ማርያም ታማልዳለች አታማልድም ማለት ብቻ ሳይሆን በነገረ ድኅነት ያላት ድንቅ ሱታፌም እንደ ፋና ሲያበራ ይታያል።
አንድ ሊቅ ባለፈው በየ ዘመኑ በጥባጭ ጸሐፊ በጥባጭ ሊቅ መነሳት አለባት ያሉት ትዝ አለኝ። በጥባጭ መናፍቅ አይነሳ እንጅ በጥባጭ ሊቅማ ይነሳ። እንዲህ ያነቃቃልና። በስንፍና የረጋውን ሁከት መንፈሳዊ ሰጥቶ ይቀሰቅሰዋልና።
መምህር ጽጌ አስተርአየ እንደጻፉት