ደብረ ዘይት ሚዲያ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


ቤተክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


ካህናት በሚሰሩት ኃጢአት እግዚአብሔር ይቀጣቸዋል እንዲያውም ከራሳቸው በደል አልፎ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ "የሲኦል መሬቱ በካህናት አጥንት ተደምድምድሞ ይገኛል "እስከማለት ደርሶ የሓላፊነቱን ክብደት እንደገለጠው ካህናት በአግባቡ ባልጠበቋቸው
በጎቻቸውንና በምዕምናን በደል ሳይቀር ይጠየቃሉ ሆኖም በካህናቱ ድክመት አሳብበን እነሱን ብናቃልል ደግሞ እነሱ ለጥፋታቸው ሲቀጡ እኛ ደግሞ በእግዚአብሔር ካህናት ላይ ባሳየነውንንቀታችን ምክንያት እንቀጣለን።

አንዳድ ሰዎች የቤተክህነትንና የካህናትን ክፉ ዜና ከመስማት ብዛት ተማርረው "እግዚአብሔር እንዴት ይታረቀን በእነርሱ እጅ ንስሃ ገብተን እውነት ይቅር ልንባል ነው እውነት ፈጣሪ በእገሌ አድሮ ይሠራል? "ብለው ተስፋ ቆርጠው ይጠፋሉ። እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ግን
እግዚአብሔር እጅግ የረከሰ ሕይወት በነበራቸው ካህናትአድሮ ሲሠራ ታይቶል።

እግዚአብሔር ቤተመቅደሱን ሲዳፈሩ የነበሩት ልጆቹን እያየ ዝም ባለውና መቅደሱን የምናምንቴዎች መፈንጫ ባደረገው በካህኑ ኤሊ አድሮ ስራ ሰርቷል። ኤሊ ለራሱ መጨረሻው ባያምርም በካህንነቱ ግን ሕዝቡ ተጠቅመው መሥዋዕታቸው አርጓል ሰክረሻል "ብሎ ያስቀየማት መካኒቱ ሐናም ለዘመናት ስታነባ ቆይታ ያልተመለሰላት ጥያቄ መልስ ያገኘው ናት ዕንባናልቅሶዋ ውጤት አምጥቶ ሳሙኤልን የመሰለ ልጅ እናት ለመሆን ያበቃት "በደህና ሂጂ የእስራኤል አምላክ የለመንሽውን ልመና ይስጥሽ "በሚለው በካህኑ ኤሊ ቡራኬ ነበር(1ሳሙኤል1፥17)
ካህን ለራሱ ለልጆቹ የማይጠቅም እንኳ ቢሆን በተሰጠው ስልጣን እግዚአብሔር ስለማይለየው ጸሎት የሚያሳርግና ዕንባን የሚያብስ ለመሆኑ ማሳያ ነው።ጌታችን እንዲሰቀል ነገር ጎንጉነውና በጨለማ ግፍ ሸንጎ የፈረደበትን በማለዳም በጲላጦስ ከፊት ያስፈረደበትን ሊቀ ካህናቱን ቀያፋንስ ማን ይረሳዋል

በነቀዘ የቤተ ዘመድ ሹመት ሊቀ ካህናትነቱን አማትና ምራት እየተፈራረቁ ሲያዙበት በነበረው በዚያብልሹ ወቅት በቤተ መቅደስ በጸሎት ፋንታ የገበያተኞች ጫጫታና የሚሸጡ እንሰሳት ጩኸት እንዲሞላ በተደረገበት ዘመን እግዚአብሔር በክፉው ሊቀ ካህናት አድሮ ይሰራ ነበር።ይህ ክፉ ሰው ክርስቶስ እንዲሞት ነቀሥሲጎነጉን
"ሕዝቡ ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡምን "?ብሎ ነበር ወንጌላዊው ስለዚህ ንግግር ሲያብራራ"ይሕንም የተናገረከራሱ አይደለም ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው
ትንቢት ተናገረ"ይላል(ዮሐ11፥50-51)
በሰቃዮቹ ላይ እንኳን አድሮ በሊቀ ክህነታቸው የሚሠራ አምላክ እንደምን ያለ ነው።የካህንን ክፋት ስንሰማ እንደ ዘካርያስ ዘመን ሰዎች ራእይ አይቶ ይህናል የሚል የዋሕ ልብ ይስጠን።

(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)

የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq


@ ራእይ'እንዳየ 'አስተዋሉ።!)

በአንዲት እለት ካህኑ ዘካርያስ በቤተ መቅደስ ለእግዚአብሔር የዕጣን መሰዋዕት በማቅረብ ላይ ነበረ። ለዚህ ጻድቅ ሰው ታዲያ ድንገት በእጣኑ መሰዊያ በስተቀኝ ቅዱስ ገብርኤል ታየው። መላዕኩ ለዚህ አረጋዊ ለብዙ ዘመናት የተመኘውን ጸሎቱን እግዚአብሔር እንደተቀበለውና ሚስቱ ኤልሳ ቤጥ ታላቅ የሚሆን ልጅ እንደምትወልድ ለት ነገረው ዘካርያስ ይኽንን የመላዕኩን ብስራት በሰማ ግዜ
ምንም እንኳን አብርሃም ና ሳራ በስተርጅና ወለዱ የሚለውን ታሪክ ሲያስተምር የኖረ ካህን ቢሆንም ለማመን ተቸግሮ "ይኽ እንደሚሆን በምን አምናለሁ "ብሎ ምልክትን ጠየቀ
ቅዱስ ገብርኤል ለዚህ ጥያቄ "እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ "ብሎ መለሰለት። ይኽ ምላሽ እንደሊቃውንቱ ትርጓሜ "እኔ የእግዚአብሔር አገልጋይ የሆንሁ ለአንተ መገለጤ ምልክት አይደለምን "?
እኔ ኮ "በነበያት መጻሕፍት የምታውቀኝ ገብርኤል ነኝ። በፊትህ የቆምኩት እኮ በእግዚአብሔር ፊት የመቆመው ነኝ
የምነግርህን እንዴት አታምነኝም "?የሚል ትርጉም ያለው ነበረ።
+++++
ቅዱስ ገብርኤል በዚህ አላበቃም "በፊቱ ተጠንቀቁ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሰሩ ይቅር አይልምና እዳታስመርሩት "ተብሎ ከተነገረላቸው የእግዚአብሔር ሹመኞች
አንዱ ነውና ቃሉን ያላመነውን ዘካርያስን ቀጣው (ዘጸ23፥21)የእምነትን ቃል ሊናገር ሲጠበቅበት የጥርጥር ቃል የተናገረውን አንደበቱን ዘጋው እንዴት የተዘጋ ማህጸን ሊከፍት ይችላል ብሉ ለተጠራጠረው ልቡ አንደበቱ ዘግቶ በመክፈት ማህፀንን የዘጋ አምላክ መልሶ እንደሚከፍት ምልክት አድርጓ ሠጠው።
ዘካርያስ በቤተ መቅደሱውስጥ ከመላዕኩ ጋር ሲነጋገር ህዝቡ በውጪ ቆመው ይጠብቁት ነበር እንደ ኦሪቱ ስርአት ካህኑ "እግዚአብሔር ይባርካችሁ ፊቱንም ያብራላችሁ ሀገር"ብሎ ሳያሰናብታቸው ወደ ቤታቸው አይሄዱም ነበረና ዘካርያስ እስኪወጣ ይጠብቁት ነበረ"ስለዘገየም ይደነቁ ነበረ።" እንጂ እንደ ዘመኑ አስቀዳሽ "እነዚህ ካህናት ከጀመሩ ማብቂያ የላተውም ብለው ተንገሽግሸው የካህኑን ማሰናበቻ ቡራኬ ሳይቀበሉ ወደቤታቸው ጥለው አይሄዱም ነበር።

++++++
ከሁሉም የሚያስደንቀውና በዚች አጭር ስብከት የምናሰላስለው ዘካርያስ ከቤተ መቅደስ ዲዳ ሆኖ ከወጣ ቡዃላ ያለውን የሕዝቡን ምላሽ ነው።ሕዝቡ ዘካርያስን ይጠብቁት ነበር በቤተመቅደስ ምን ስለዘገየ ይደነቁ ነበር
በወጣም ግዜ ሊነግራቸው አልቻለም በቤተመቅደስ ራእይ እንዳየ አስተዋሉ።እርሱም ይጠቅሳቸው ነበረ ዲዳ ሆኖ ኖረ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄድ።(ሉቃ1፥21-23)
ወዳጄ ሆይ እስኪ ቀና ብለህ ለአፍታ ባለንበት ዘመን ቢህን ብለህ አስበው
አንድ ሰንበት ምዕመናን አስቀድሰው ካህኑ ወተው እስከሚባርኳቸው ሲጠባበቁ ቄሱ በጣም ዘግይተው ሲወጡ ዲዳ ሆነው ቢወጡና ሕዝቡን ማነጋገር ቢያቅታቸው ሕዝቡ ምን የሚህ ይመስልሃል "ራዕይ አይተው ወጡ "ብሎ የሚደነቅ ይመስልሃል ከሆነ ድንቅ ነው።

እውነቱን ለመናገር ግን ይኽ ተከስተው መረጃን ለአለም ለማዳረስ ጥቂት ደቂቃዎች በሚበቁበት በዚህ የኢንተርኔት ዘመን ቢሆን ሕዝቡ ከቤተ ክርስቲያኑ ሳይወጣ ወሬው ለአለም በተሰማ ነበር ካህኑ ዲዳ የሆኑት "ተቀስፈው ነው" ለማለትና እርሳቸውም ድፍረቱን አብዝተውት ነበር ዋጋቸውን ሰጣቸው ብሎ በደላቸውን ለማብዛት ሰውሁሉ ሳይረባረብ አይቀርም። ዘካርያስ "በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ"ሆኖ ሳለ ዲዳ ሆኖ ሲወጣ ሰው እራዕይ አየ ብሎ አሰበለት በዚህ ዘመን ግን ሰውዬው መልካም ሰው ቢሆንም እንኳን ይኽ ክስተት ቢከሰትበት "እንግዲህ ላይ ላዩን ጥሩ መስሎ ውስጡ ችግር ይኖር ይሆናል "እንላለን እንጂ ራእይ አይቶ ይሆናል የሚል ግምት ጨረሶ አይኖረንም።

የዚያ ዘመን ሰዎች ግን ለመንፈሳዊነገር በቅርብ የሆነ አስተሳሰብ ነበራቸው ራእይ አየ ብለው መገመታቸውን ሳይበቃ ዲዳሆኖ የወጣ ሰው ሰሞነኛ ነቱን እስኪፈጽም አገልግልቱን ሲቀጥል
ዲዳ ያደረገው የሆነ ጥፋት ቢያይበት ነው ለምን ያገለግለናል ? ብለው አላጉረመረሙም። ይህ የዚያ ዘመን ሰዎችን መንፈሳዊ ህሊና በዚህ ዘመን ሆነን ስናየው ትልቅ ወቀሳ ያለው ነው።
ምክንያቱም ከፓትርያሪክ እስከ ቀሳውስት አባቶችን ማቃለል የዚህ ዘመን ሙያ ከሆነ ሰንብቷል የፖለቲካ ባለስልጣናትን ሲተቹ እንኳን በጥንቃቄና በፍርሃት የተሸበበባቸው ሰዎች ከመንግስት ስልጣን የሚበልጥ መንፈሳዊ ስልጣን ያላተውን አባቶች መቼም በሰማይ እንጂ በምድር እስር ቤት አይወረውሩንም ብለው ነው። መሰል አንዳንዶች ሲሳደቡ ይታያል ። በዚህ ዘመን ካህናትን ማቃለል ጀግና ለእውነት የቆመ የሚያሰኝ ተግባር እየመሰለ መቷል።
++++++
ይኽንን ስል "ካህናቱም እኮ አልከበር አሉ እንዲህ እያደረጉ ብሎ የሚሞግት አይጠፋም ሆኖም አንድን ካህንነ ጥሩ ስለሆነ ብናከብረው ያስከበረው ጥሩነቱ ነው እንጂ እኛ ክህነቱን አስበን አከበርነው ሊባል አይችልም። እንዲያውም እውነተኛ አክባሪ የሚባለው መጥፎ ምግባር የለውን አባት ስለአባትነቱ የሚያከብር ነው። እውነተኛ አክባሪ የሚባለው እንደኖህ ሰክሮ እርቃኑን የጣለ አባቱን እያየ የሚስቅና ለሌሎች የሚናገር ሳይሆን እንደ ሴምና ያፌት እንኳን ለሌላው ላሳይ ራሴም የአባቴን ውርደት አላይም የሚል ነው።

ቅዱስ ጳውሎስ ያደረገውን እናስታውስ በሸንጎ ቀርቦ ሳለ በዳኛው ትዕዛዝ በጥፊ ተመታ። ይኽን ግዜ ሳይፈረድበት መመታቱ አበሳጭቶት ዳኛውን "አንተ ቀኖራ የተለሰነ ግድግዳ እግዚአብሔር አንተን ይመታ ዘንድ አለው አንተ ልትፈርድብኝ ተቀምጠህ ሳለ ያለ ሕግእመታ ዘንድ ታዘለሕን አለው ጳውሎስ ይህንን ሲናገር ከአጠገቡ የቆሙት "የእግዚአብሔር ን ሊቀ ካህናት ትሳደባለህን አሉት። ጳውሎስ እንዲህ ሲሉት "እንደሊቀካህንነቱ አልከበር ሲል ምን ላርግሽ " አላለም ወይንም በዚያ ዘመን የነበረውን የነቀዘ የፈሪሳውያን ህይወት እንደማስተባበያ አልተጠቀመም
ጳውሎስ ያለው እንዲህ ነበር "ወንድሞቼ ሆይ ሊቀ ካህናት መሆኑን ባላውቅ ነው
በሕዝብ አለቃ ላይ ክፉ አትናገር ተብሎ ተጽፏልና (ሐዋ23፥2-5)

**
ልብአድርጉ የእብራውያንን መልዕክት የጻፈው ጳውሎስ ለምን ሊቀ ካህናት ትሳደባለህ ሲሉት "የሐዲስ ኪዳን ካህናት ኢየሱስ ነው ማለት አቅቶት አይደለም። በጥፊ እያስ መታውም እንኳ ቢሆን
ሊቀ ካህናት መሆኑን ሲረዳ "ሊቀ ካህናት መሆኑን ባላውቅ ነው። "አለ።

በዚህም ካህናትን እንኳን ወሬ ሰምተን ቀርቶ በጥፊ ቢያስመቱን እንኳ
አክብሮታችን እንዳይቀንስና ከተሰደብንም "ካህን መሆናቸውን ባላውቅ ነው ፣ፓትርያሪክ መሆናቸውን ባላውቅ ነው "እያልን እንድንጸጸት አስተማረን።




ዛሬ ጥር 25/5/2017 ዓ/ም
ስራተ ጋብቻችሁን በደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የፈጸማችሁ
የደብራችን የመሰረተ ተዋህዶ ፍሬ የሆንሽው ቤተልሔም ታፈሰና ዲያቆን አራጋው ገመደ መልካም ጋብቻ ይሁንላችሁ






++ በሰንበት መፍረስ ++

የኢያሪኮ ሰዎች የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ኃይል በመናቃቸው ምንኛ ተጎዱ?!  እርሱ ዓለምን የፈጠረ መሆኑን ስላላመኑ እንዳልተፈጠሩ የሆኑት የኢያሪኮ ሰዎች መጨረሻ እጅግ አሳዛኝ ነበር፡፡

ቅጥራቸው ከመፍረሱ በፊት እስራኤል የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ለስድስት ቀናት ያህል በዝምታ ኢያሪኮን ዞሯት፡፡ ዓለምን በስድስት ቀናት የፈጠረውን ጌታ እንዲያስተውሉ ስድስት የዝምታ ቀናት ተሠጧቸው፡፡ በሰባተኛው ቀን ግን ጮኹ የኢያሪኮም ቅጥር ፈረሰ፡፡

ሰባተኛ ቀን የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ለኢያሪኮ ግን የመፍረስ ቀን ሆነባት፡፡ ሰባተኛ ቀን ፈጣሪን ለሚያምኑ የተቀደሰ ቀን ነበር ፤ ለኢያሪኮ  የመረገም ቀን ሆነባት፡፡
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ ባየበት ሰባተኛ ቀን ኢያሪኮ ግን ከፉ እንደሆነች ታየባት፡፡

እግዚአብሔር የሌለበት ሕይወት እንዲህ ነው፡፡ ወዳጄ እግዚአብሔር በሕይወትህ ውስጥ ከሌለ የሰንበት ቀን የነፍስህ ዕረፍት ቀን መሆኑ ይቀርና እንደ ኢያሪኮ የመፍረስ ቀን ይሆናል፡፡ በዚያ ቅዱስ ቀን ቅጥርህን በመጠጥ ፣ ብስካር ብዝሙት ስታፈርስ ትውልና ታድራለህ፡፡ ራስህን አንድደህ ትሞቃለህ ፤ እያራገብህ ትቃጠላለህ፡፡ ታቦት ይዘው ቢዞሩህም የኃጢአት ግንብን አጥረሃልና አትሰማም፡፡ በላይህ ላይ ቢቀደስብህም እንደ ኢያሪኮ ሰዎች ካህናቱን እያየህ ‘ዝም ብሎ መዞር ምንድር ነው?’ እያልክ ትስቃለህ፡፡ የካህናቱ የቅዳሴ ዜማ ለአንተ የሚያፈርስ ጩኸት ይሆንብሃል፡፡ የኢያሪኮ ሰው ከመሆን ፣ በሰንበት ፈራሽ ከመሆን ያድንህ!

ቅዳሴያችን መካከል ካህኑ ዕጣን እያጠኑ ዞረው ሲመለሱ የዚህች አጭር ጽሑፍ መነሻ ሃሳብ የሆነውን ይህንን ጸሎት ይጸልያሉ፦  አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አስቀድመህ በባሪያህ በነዌ ልጅ በኢያሱ እጅ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረስከው የእኔንና የሕዝብህን የኃጢአታችንን ግንብ አፍርሰው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 9 /2012 ዓ.ም.
ቪክቶሪያ
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq


የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች በያላችሁበት ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ እሁድ 25/5/2017 ዓ/ም በሰንበት ት/ቤት በተለመደው ሰዓት አዲስ ኮርስ ስለ ምንጀምር ሰዓታችሁ ጠብቃችሁ እንድትገኙ
         ማሳሰብያ
ከዚህ ቀደም እንደ ምናደርገው አቴንዳንስ ደብተር ነጥብ ስለ ሚያሰጡ በሰዓቱ እንድትገኙ
         ዲ/ን ሳሙኤል ተመስገን


አንድ ሰው መጥቶ ለአንድ ቅዱስ አባት ጥያቄ አቀረበለት

"ተአምር መሥራት እፈልጋለሁ ፣ እንዴት ላድርግ?"
ቅዱሱ አባት መለሰለት

"አንድን ሰው ወንጌል እንዲያነብ ካስተማርከው ዓይን አበራህ ማለት ነው

ድሆችን እንዲረዳ ካስተማርከው ሽባውን አዳንክ ማለት ነው

ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔድ እንዲችል ካደረግህ አንካሳውን ፈውሰሃል

ሙት ማንሣት ከፈለግህ ደግሞ ንስሓ እንዲገባ አድርገው ያኔ የሞተ ሰውን አስነሥተሃል ማለት ነው
በል ሒድና ተአምር ሥራ!"

ለልጆቻችን ክርስቶስ ማን እንደሆነ እኛ ካልነገርናቸው ዓለም ክርስቶስ ያልሆነውን ሁሉ ይነግራቸዋል።

"ፍቅር እንዴት መቆጣት እንዳለበት አያውቅም"
ቅዱስ ማር ይስሐቅ

ኃጢአተኞች በሌላ ኃጢአተኛ ላይ ከእነርሱ ለየት ያለ ኃጢአት ስለ ሠራ ይፈርዱበታል ፣ ወይም ተመሳሳይ ኃጢአት ቢሠራም ይፈርዱበታል።

“የሚጾሙ የሚጸልዩና የሚተጉ ድቃቂ ሳንቲም እስካላስወጣቸው ድረስ በምንም ነገር ላይ የሚገኙ በችግር ላይ የሚሰቃዩትን ግን ዞር ብለው የማያዩ ብዙ ሰዎችን አውቃለሁ" ቅዱስ ባስልዮስ

"እኛ መነኮሳት ነን:: እኛ የሠለጠንነው ሰዎችን ለመግደል ሳይሆን ምኞታችንን ለመግደል ነው" አባ ጴኤሜን

★ ★ ★
አባታችን ሆይ እንዴት ትላለህ?

እንደ ልጅ ካልኖርህ እንዴት "አባት" ትለዋለህ?
ሌላውን ጠልተህ ራስ ወዳድ ከሆንክ እንዴት አባት "አችን" ብለህ በአንድነት ትጠራዋለህ?
ምድራዊ ነገር ብቻ እያሰብህ እንዴት "በሰማያት የምትኖር" ትለዋለህ?
ልብህ ከእርሱ ርቆ በአንደበትህ ብቻ እየጠራኸው "ስምህ ይቀደስ" እንዴት ትለዋለህ?
ሥጋዊና መንፈሳዊውን እየቀላቀልህ "መንግሥትህ ትምጣ" ለምን ትለዋለህ?
መከራን በጸጋ የማትቀበል ከሆነ "ፈቃድህ ይሁን" ለምን ትላለህ?
ለራስህ ሆድ እንጂ ለተራቡት ግድ የማይሰጥህ ከሆነ ለምን "እንጀራችንን ሥጠን" ትላለህ?
በወንድምህ ላይ ቂም ይዘህ "እኛም የበደሉልን ይቅር እንደምንል" እንዴት ትላለህ?
የኃጢአትን አጋጣሚዎች ሳትሸሽ "ወደ ፈተና አታግባን" እንዴት ትላለህ?
ክፉን ለመቃወም አንዳች ሳታደርግ "ከክፉ አድነን" እንዴት ትላለህ?
ጸሎቱን ከልብህ ሳትሰማውስ እንዴት አሜን ትላለህ?

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-

ዩቱብ

https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq


+ ጌታ ሆይ ይህን ውኃ ሥጠኝ +

ሳምራዊትዋ ሴት በጠራራ ፀሐይ ውኃ ልትቀዳ እንስራዋን ይዛ ከጉድጓድ አጠገብ ተቀምጣለች፡፡ በጠዋት ወይም በማታ ውኃ መቅዳት ስትልችል ፀሐይ አናት በሚበሳበት በስድስት ሰዓት መምጣት እንዴት ልትመርጥ ቻለች? ከጎረቤቶችዋ ጋር እየተጫወተች አብራ ቀድታ መመለስ አትችልም ነበር? ብቻዋን ለመቅዳት ለምን ፈለገች? ከሰው ፀሐይ ያስመረጣት ምንድነው? ዝርዝሩን እርስዋ ናት የምታውቀው፡፡

አምስት ባሎች የነበሩዋት እና አሁንም ባልዋ ካልሆነ ሰው ጋር የምትኖር ሴት መሆንዋ ግን ተጽፎአል፡፡ ለብዙ ወንዶች ሚስት በሆነች ቁጥር ስለራስዋ የሚኖራት ግምት እየወረደ መምጣቱ አይቀርም፡፡ በተደጋጋሚ አልሳካ ባላት ትዳር ምክንያት ልብዋ እየቆሰለ ተስፋ እየቆረጠች ሁሉን ነገር እየጠላች መምጣትዋ አይቀርም፡፡ እርስዋ ስላልተሳካው ትዳርዋና አሁንም ባልዋ ካልሆነ ሰው ጋር ስለመኖርዋ ሰዎች የሚያወሩት ግን ብዙ ነው፡፡ የእርስዋን ሕመም ሳይረዳ እንደ ርካሽ የሚቆጥራት ፣ ዝሙተኛ አድርጎ የሚያስባት ፣ ዕድለ ቢስ አድርጎ የሚፈርጃት በንቀት በአሽሙር ባለ አምስት ባሎች አድርጎ የሚነቁራት ሰው አይጠፋም፡፡ በግልጥ ባይነግሯትም በአስተያየት በአነጋገር የሚያሳቅቋት አይጠፉም፡፡ ስለዚህ ከሰው አፍ ፀሐይ ይሻለኛል ብላ መጣች፡፡ ሰዎች በነገር ከሚጠብሱኝ በፀሐይ ብትጠብሰኝ ይሻለኛል ብላ በበረሃማው ምድረ በዳ በአጉል ሰዓት ይህች ተስፋ ያጣች ምስኪን ውኃ ልትቀዳ ሔደች፡፡

“ኢየሱስም በሰማርያ ሊያልፍ ግድ ሆነበት” እርግጥ ነው ከይሁዳ ወደ ገሊላ ለመሔድ በሰማርያ ማለፍን መልክዓ ምድሩ ያስገድዳል፡፡ ክርስቶስ ግን ግድ የሆነበት በመልክዐ ምድሩ ብቻ አልነበረም፡፡ የጠፋውን የሰው ልጅ ሊያድን የመጣው መድኃኒት እርሱ ነውና አንዲትን በፀሐይ የምትለበለብ ነፍስ ፍለጋ ሊሔድ ግድ ሆነበት፡፡ ከሰው ሸሽታ ምድረ በዳ የመረጠችውን ተስፋ የቆረጠች ሴት የአሕዛብ ተስፋ ክርስቶስ ሊፈልጋት ተገኘ፡፡

ወደ እርስዋ ቀርቦ ውኃ አጠጪኝ አላት ፤ አባ ጊዮርጊስ ‘’አንተ የሕይወት ውኃ ስትሆን ከሳምራዊትዋ ሴት ውኃን ለመንህ ‘’ እንዳለ የሕይወት ውኃ ክርስቶስ ውኃ ለመናት፡፡ እርሱ የተጠማው ውኃ ሳይሆን የእርስዋን ነፍስ ነበረ፡፡

እርስዋም አንተ አይሁዳዊ ስትሆን ሳምራዊት ከምሆን ከእኔ ውኃ ትለምናለህ? አለችው፡፡ እንዲህ ነው ነገሩ፡፡ የቆሰለች ነፍስ ስለ ዘር ታወራለች፡፡ ተስፋ የቆረጠች ነፍስ የዘር ጉዳይ ሲሆን ልሳንዋ ይከፈታል፡፡ ውኃ ለማጠጣት ዘር መጠየቅን ምን አመጣው፡፡ ውኃው አይሁዳዊ ነው? ወይንስ ሳምራዊ? ውኃ ጠማኝ የሚል ሁሉ ውኃ ይገባዋል እንጂ ዘሩ አይጠየቅም፡፡ እርስዋ ግን ጠየቀችው፡፡ በእርግጥ ይህች ሳምራዊት ሴት ይህን ጥያቄ የጠየቀችው ክርስቶስ መሆኑን ከማወቅዋ በፊት ነበር፡፡ ክርስቶስ መሆኑን ካወቀች በኋላ ግን ስለ አይሁዳዊነትና ስለ ሳምራዊነት ስትናገር አልተሰማችም፡፡ ‘’አንተ አማራ ስትሆን ጉራጌ ከምሆን ከእኔ ውኃ ለምን ትለምናለህ?’’ ‘’አንቺ ኦሮሞ ስትሆኚ ትግሬ ከምሆን ከእኔ እንዴት ውኃ ትለምኛለሽ?’’ በሚል ጥያቄ ሀገሩን ያጨናነቁተ ክርስቶስን ያወቁ ክርስቲያኖች መሆናቸው ግን ልብን የሚሰብር እውነታ ነው፡፡ በዚህ ጠባያችን እንደ ክርስቲያን ሳንኖር እንደ ክርስቲያን ልንሞት መሆኑ ምንኛ ያሳዝናል?

ጌታችን የሴቲቱን የዘር ጥያቄ እንዳልሰማ አለፈውና ‘’ውኃ አጠጪኝ የሚልሽ ማን መሆኑን ብታውቂ የሕይወትን ውኃ እንዲሰጥሽ ትለምኚው ነበር’’ አላት፡፡ አሁንም የተጠማው የእርስዋን መመለስ ነውና እርስዋ ያነሳችውን ርእስ ሳያነሳ የውኃ ጥያቄውን ቀጠለ፡፡ ውኃን የፈጠረ ጌታ የሴቲቱን በተሰበረ ልብ የሚፈስስ ዕንባ ተጠምቶ ውኃ ለመናት፡፡

‘’ጌታ ሆይ መቅጃ የለህም ጉድጓዱ ጥልቅ ነው’’ አለችው፡፡ እንዴት ያለ ንግግር ነው፡፡ የነፍስዋን መመለስ ለተጠማው ጌታ ይህ ምላሽ እንዴት ከባድ ነው?
እውነት ጌታ መቅጃ የለውም? እውነትስ ጉድጓዱ ጥልቅ ነው? አዎ ልክ ነው የለውም፡፡

ጌታ ሆይ መቅጃ የለህም ፤ ጉድጓዱም ትልቅ ነው፡፡ ብዙ ተስፋ የቆረጡ ነፍሳትን ፣ ወደ አንተ መመለስ የሚሹ አንተም የተጠማሃቸው ነፍሳት በጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ወድቀዋል፡፡ የገቡበት አዘቅት ጥልቅ ነው ፤ በጥላቻ ፣ በክፋት ፣ በብዙ ተስፋ ማጣት ጉድጓድ ውስጥ የገቡ አንተ የተጠማሃቸው ነፍሳት ብዙ ናችው፡፡ ነገር ግን  ሳምራዊትዋ እንዳለችው ከጉድጓዱ ማውጫ መቅጃ የለህም፡፡ ካለህ እስቲ ንገረን፡፡ ሕዝብህን ከጉድጓድ ውስጥ የሚያወጣ የአንተን ፈቃድ የሚፈጽምልህ አገልጋይ አለህ?  ሁሉም ጉድጓድ ውስጥ ገብቶ የቀረ አይደለምን? ራሱ መቅጃ የሚፈልግ መቅጃማ ሞልቶሃል? እንደ ኢሳይያስ ዘመን ‘’ማንን እልካለሁ’’ ብለህ ብትጣራ ይሻልሃል እንጂ መቅጃስ የለህም፡፡ ወይ ሱራፊን ልከህ በእሳት ፍሕም ተኩሰህ ካላነጻኸን በቀር መቅጃ የለህም፡፡

ሴቲቱ የያዕቆብን አምላክ ክርስቶስን ‘አንተ ከያዕቆብ ትበልጣለህ?’’ አለችው፡፡ ተስፋ የቆረጠ ሰው ንግግሩ ሻካራ ነው፡፡ ‘’አንተ ከማን ትበልጣልህ? ከእገሌ ተሽለህ ነው?’’ የሚሉ ቃላት ነፍሱ የቆሰለ ሰው ንግግሮች ናቸው፡፡ ክርስቶስ አላስቀየማትም፡፡ አመል ያሳጣት የተመረረችበት ኑሮዋ እንደሆነ ያውቃል፡፡ “የተጎዱ ሰዎች ሰውን ይጎዳሉ” (hurt people hurt people) እንደሚባለው መጉዳትዋ ከመጎዳት ነውና ክብሬን ላስጠብቅ ሳይል ታገሳት፡፡ ባል የለኝም ስትል እንኳን ‘’እውነት ተናገርሽ’’ አሁን ያለው ባልዋ ባለመሆኑ እንዲህ እንዳለች አድርጎ ከሐሰትዋ ውስጥ እውነት አወጣላት፡፡

የተቀጠቀጠ ሸንበቆ የማትሰብረው የሚጤስ ጧፍ የማታጠፋው ትሑት አምላካችን ሆይ ክፉ ንግግሮቻችን የሚፈልቁት ከክፉ አኗኗራችን ነውና እባክህን እኛንም ታገሰን፡፡ ኢትዮጰያውያን ተሳዳቢዎች ፣ ዘረኞች ፣ ነውረኞች ያደረገን የተበላሸ ሕይወታችን ነውና ይቅር በለን፡፡ በመጥፎ ንግግሮቻችን የምናሳዝንህ ፣ በእርስ በእርስ መበላላት የምናስከፋህ ሳምራዊትዋ ሴት ባሎች እንደተፈራረቁባት ብዙ ፖለቲከኞች ተፈራርቀውብን ፣ ትዳር አልሳካ ብሎን ነውና እርስዋን እንደታግስህ ታገሰን፡፡

ሴቲቱን ጌታ ታግሶ የጎደላትን ሞላላት፡፡ ‘’እኔ ከምሠጠው ውኃ የሚጠጣ ለዘላለም አይጠማም ‘’ አላት፡፡ እርስዋም ‘ጌታ ሆይ እንዳልጠማ ውኃም ልጠጣ ወደዚህ እንዳልመጣ ይህን ውኃ ስጠኝ’’ አለችው፡፡ ይህ ውኃ ‘የሕይወት ውኃ እኔ ነኝ’’ ያለው ክርስቶስ ራሱ ነው፡፡ ሴቲቱም እርሱ መሆኑን ስታውቅ እንስራዋን ጣለች፡፡ እርሱን ካገኘች በኋላ እንደማትጠማ እርግጠኛ ነበረች፡፡

ወዳጄ ሆይ እንደ ሳምራዊትዋ ሴት መመላለስ የሰለቸህ መንገድ የለም? ስትጠጣው አሁንም ጨምር የሚያሰኝህ የማይቆርጥ ጥም የለህም? ልትቀዳ የምትመላለስበት ጉድጓድስ የለም? ሁለተኛ አልሔድም ብለህ ዝተህ የምሔድበት ቦታ የለም? ሁለተኛ አልጠጣውም ብለህ የምትጠጣው ሁሌ የሚጠማህ ውኃ ምንድር ነው?

ሁሌ የሚጠማህ መላቀቅ እየፈለግህ ያልተውከው ፣ ዞረህ የምትሔድበት ፣ ታጥቦ ጭቃ ፣ አድሮ ቃሪያ ፣ ከርሞ ጥጃ የሆንህበት ልማድ የለህም? ክርስቶስ ቦታውንም ውኃውንም ያውቀዋል፡፡ ከዚህ መገላገል ከፈለግህ እንደ ሳምራዊትዋ ሴት እንዲህ በለው፦
‘ጌታ ሆይ እንዳልጠማ ውኃም ልጠጣ ወደዚህ እንዳልመጣ ይህን ውኃ ስጠኝ’’

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መስከረም 28/ 2012 ዓ ም
ሜልቦርን አውስትራሊያ ተጻፈ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!+ ጌታ ሆይ ይህን ውኃ ሥጠኝ +








++ እንዴት ወድቀን እንዴት ተነሣን? ++ በዲ.ን ሄኖክ ኃይሌ ++
ኦሪት ዘፍጥረት ስለሰው ልጅ ውድቀት ሲናገር ዕባብና ሔዋን ያደረጉትን ቃለ ምልልስና በዕባብ ምክር ሠጪነት የሰው ልጅ እንዴት ከገነት እንደተባረረና ጸጋውን እንደተገፈፈ ያስረዳል፡፡
ይህንን የዕባብና የሔዋን ቃለ ምልልስን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብናወጣው ወይም ኦሪት ዘፍጥረት የአዳምና ሔዋንን ከገነት መባረር ብቻ የሚናገር ቢሆን ኖሮ ‹ምን አጥፍተው ነው የተባረሩት?› ወደሚል ግራ መጋባት ውስጥ እንገባ ነበር፡፡
ወዳጄ የዕባብና ሔዋንን ቃለ ምልልስ መስማት ሳይችል የአዳምና ሔዋንን ከገነት የመባረር ታሪክ ለመረዳት የሚችል እንደሌለ ሁሉ የእመቤታችንንና የቅዱስ ገብርኤልን ቃለ ምልልስ ሳያነብ የሰው ልጅን ወደ ገነት የመግባትና የመዳን ታሪክ ለመረዳት የሚችል ሰው ማንም የለም፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ በአዳምና በክርስቶስ ተምሳሌት (Christ-Adam analogy) አድርጎ ጻፈ:: ክርስቶስን ‹ኋለኛው አዳም› ብሎ ጠርቶታል፡፡ (1ቆሮ. 15፡45) አዳምንም ‹አዳም ይመጣ ላለው ለእርሱ አምሳሉ ነው› በማለት የክርስቶስ ምሳሌ እንደሆነ አስረድቷል፡፡ (ሮሜ. 5፡14) የሰው ልጅ ተፈጥሮ ታሪክ የተጀመረው ከአዳም ታሪክ እንደነበር የሰው ልጅ አዲሱ ተፈጥሮ ታሪክም የተጀመረው በዳግም ፍጥረት (Recaptulation) በተፈጠርንባት በቀራንዮ ነው፡፡
ይህም ንጽጽርም በኁዋላ ዘመን ለተነሡ እንደሰማዕቱ ዮስጦስና እንደ ያዕቆብ ዘሥሩግ ያሉ ሊቃውንት የማርያምና ሔዋን ተምሳሌትን (Mary eve analogy) እንዲያመሠጥሩ መነሻ ሆናቸው:: ያነጻጸሩት ሔዋንን ከማርያም ብቻ ሳይሆን እንዴት ወደቅን እንዴት ተነሣን የሚለውን ነው::
ሔዋን ለውድቀታችን መነሻ ነበረች ማርያም ግን ለመነሳታችን ምክንያት ሆነች:: ሔዋንን ሰይጣን በዕባብ ተመስሎ አነጋገራት:: ማርያምን ግን እግዚአብሔር በገብርኤል ሆኖ አነጋገራት:: ሔዋን የዕባቡን ቃል በመስማትዋ ከገነት ወጣን : ማርያም የገብርኤልን ቃል በመስማትዋ ወደ ገነት መለሰችን::
የዕባብና የሔዋንን ቃለ ምልልስ በቁጭት እናነበዋለን:: የድንግልና የገብርኤልን ምልልስ ግን በደስታ እንጸልየዋለን:: ያ ቃለ ምልልስ እኛን ወደ ሕይወት የመለሰ ቃለ ምልልስ ነው:: የ15 ዓመትዋ ብላቴና ማርያም ምድራዊያንን ሁሉ ወክላ ከሰማያዊው መልእክተኛ ጋር ተነጋግራ ዕርቃናችንን አለበሰችን:: የድሆች ልጅ የሆነችው ብላቴና የመላእክትን አለቃ በጥያቄ አስጨንቃ መርምራ ከጭንቃችን ገላገለችን::
ሔዋን የዕባብን ምክር ሳትመረምር ተቀበለች:: ድንግል ማርያም ግን የገብርኤልን ብሥራት መረመረች:: ለሔዋን ዲያቢሎስ "እግዚእብሔር እንደርሱ እንዳትሆኑ ብሎ ከለለላችሁ" ብሎ ከፈጣሪ አጣላቸው:: ሔዋን ሁሉን አዋቂ ለመሆን ቸኩላ ከባልዋ ጋር ፈጠነች:: ድንግል ማርያም ግን ሁሉን አዋቂ ልሁን አላለችም :: "ወንድ ስለማላውቅ እንዴት ይሆንልኛል? ብላ ጠየቀች : ሔዋን አምላክ ለመሆን ተታለለች:: ትሕትና የሞላባት ድንግል ግን "እነሆኝ የጌታ ባሪያው ነኝ" ብላ ተቀበለች::
ይህች ድንግል ገብርኤልን ሰምታ የሕይወትን ዛፍ አበላችን:: ይህች ድንግል ይሁንልኝ በማለትዋ የተጠመቅን ሁላችን ክርስቶስን ለበስን:: በእርስዋ ይሁንልኝ ማለት ኪሩብ ሰይፉን ጣለ : ከጥበቃም ተገላገለ:: እኛም ከዕፀ ሕይወት እንበላ ዘንድ ታደልን::
ብዙ ሰው " ሔዋን ለመውደቃችን ምክንያት ናት " ሲባል ይስማማል:: ድንግል ማርያም ግን ለመዳናችን ምክንያት ሆነች የሚለውን ግን አንዳንዶች ለመቀበል ይቸገራሉ:: ሔዋን ለመውደቃችን ካደረገችው ይልቅ ድንግል ማርያም ለመነሣታችን ያደረገችው ይበልጣል!
የድኅነታችን መጀመሪያ የሆነችውን ይህችን ድንግል ክብርዋን በሕሊናችን እንሳለው:: እሳታዊ መልአክ ቆሞ የዘመረላት ድንግል : አባትዋ ዳዊት ከሩቅ ሆኖ እያያት "ልጄ ሆይ ስሚ እዪም ጆሮሽን እዘንብዪ" እያለ የገብርኤልን ቃል እንድትሰማና ከሲኦል እንድታወጣው የሚማጸናትን ድንግል : ወንድምዋ ሰሎሞን "እኅቴ ሙሽራ ሆይ ሁለንተናሽ ውብ ነው ነውርም የለብሽም" እያለ የቀረበላትን 'የተባረክሽ ነሽ' የሚል ምስጋና እንድትቀበል የሚዘምርላትን : በእጆችዋ ሐርና ወርቅን : በማኅጸንዋ ሰውና አምላክን : በመውለድዋ ሰውና መላእክትን አስማምታ የፈተለችና ያዋሐደችዋን ይህች ድንግል እስቲ ለአፍታ እናስባት:: የባቢሎንን ሰባት እጥፍ የነደደ እሳት ያቀዘቀዘው ገብርኤል በፊትዋ በትሕትና አደግድጎ የቆመላትና ዘካርያስን ዲዳ ትሆናለህ ባለበት አንደበቱ "አንቺ የተባረክሽ ነሽ " እያለ የሚማጸናትን የዐሥራ አምስት ዓመት ብላቴና እስቲ እናስባት! ዓላማ ይዞ እንደተሰለፈ ሠራዊት የምታስፈራ ይህች ማናት?
ሽማግሌ አባትዋን ቅጠል ከለበሰበት ዛፍ አውጥታ ልጅዋን ሸማ አድርጋ ያለበሰች : እናትዋን ሔዋንንም የሚጎዳ ማሠሪያዋን ፈትታ ቁስልዋን ያከመች የሔዋን መድኃኒት ይህች ድንግል ማን ናት? የእርስዋን ክብር በኃጢአተኛ ብዕር እንደምን እጽፈዋለሁ?
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ያለውን ብዬ ብዘጋው ይሻለኛል
"የድንግል ማርያምን ክብር ከመግለጽ ፀሐይን ከነብርሃንዋና ከነሙቀትዋ መሣል ይቀልላል"
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-

ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq


''ቦሩ ሜዳ''   የፊት ለፊት የጥያቄና መልስ መድረክ
                                                                                                                 
  ''ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለምን የአዋልድ መጻሕፍትን ትጠቀማለች ?''

“ቦሩ ሜዳ” በማኅበረ ቅዱሳን ወርኃዊ የስብከተ ወንጌል ጉባኤ ላይ

ቀን፡- ጥር 25/2017 ዓ/ም
ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ

በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ

እርስዎም ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመገኘት ከአዋልድ ማጻሕፍት ጋር ተያይዞ ያለዎትን ጥያቄ በማንሳት ምላሽ ያገኙ ዘንድ ተጋብዘዋል፡፡


“ቁጭ ብላችሁ ችግራችሁን ፍቱ”-ብርጋዲየር ጀነራል ከበደ ረጋሳ
እኛ ከዚህ በኋላ ህዝባችን እንዲበጠበጥ፣ የእኛም ሆነ የህዝባችን ደም እንዲፈስ አንፈልግም። እናንተ በምትሰጡን ትዕዛዝ ሀገራችን ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከሀገር ውጪም ደማችንን እናፈሳለን። ቁጭ ብላችሁ ችግራችሁን ፍቱ። በ21ኛው ክፍለ ዘመን እርስ በርሳችን የምንዋጋው እኛ ብቻ ሳንሆን አንቀርም፣ይሄ የእያንዳንዱ የኢትዮጵያ ወታደር ድምፅ ነው።"




የማህበራዊ ሚዲያ አጠቀም

18 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.