ደብረ ዘይት ሚዲያ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


ቤተክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


✔ በምጸልይበት ጊዜ ልቤ አይሰበሰብም
✔ እንዲህ ከሆነ መጸለይ ቢቀርብኝስ ??

ልቡናውን ሰብስቦ መጸለይ ያቃተው አንድ ደቀ መዝሙር አረጋዊውን አባት እንዲህ ሲል ይጠይቃቸዋል፡- “አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ልቡናዬ አይሰበሰብልኝም፤ አፌ ቢያነበውም ልቡናዬ ግን ይበታተናል፡፡ እኔ ደግሞ ዝም ብዬ ሳስበው፦ ቅዱሳን በፍጹም ሐሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የጻፉትን እኔ በልቤ ሌላ እያሰብኩ በአፌ ብቻ ባነበንበው እንደ ገደል ማሚቶ ፊደሉ አፌ ላይ እየነጠረ ይሄዳል እንጅ ጸሎትም አይሆንልኝም ፡፡

ስለዚህ አባቴ የአፍ ብቻ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል?" ብሎ ጠየቃቸው። አረጋዊው አባትም እንዲህ ሲሉ አስረዱት፡-

“አየህ ልጄ ዐይነ ስውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው የበትሩን ድምጽ ሰምቶ ይመታኛል ብሎ ይሸሻል እንጅ ዐይነ ስውር ነው አላየኝም ብሎ ባለበት አይጠብቀውም። ስለዚህ አንተም አስተውለህ ብትጸልይ መልካም ቢሆንም ለጊዜው ግን ጭራሽ ከምታቆመው በአፍህ ውስጥ ያለው የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት የሚሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና መቼም ቢሆን ጸሎትህን አትተው፡፡ አጋንንትንም ማባረር አንድ ታላቅ ጥቅም ነውና፡፡ ብዙ ከመጸለይህም አንጻር አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ታደርስሃለች።

እናም ልጄ ልብህ ምንም ዝርው ቢሆንም አፍህም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነውና ይህንንም እንዳታቆመው። አሁን አንዱን ይዘህ ወደፊት ደግሞ ሁለቱንም ለማገናኘት መጣር ይኖርብሃል እንጅ አንተው በዳይ አንተው አኵራፊ ሆነህ ጭራሽ ከአምላክ ርቀህ የጠላት ሰይጣን መጫወቻ እንዳትሆን
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMBYPbBMJ/




ነገረ ቅዱሳን ተከታታይ ኮርስ
ዘወትር እሁድ ጠዋት ከመርሃ ግብር ብኋላ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ከአራተኛ አመት ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ጋር እንዲሁም ከሰዓት ዘጠኝ ሰዓት በደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት አዳራሽ ከአንደኛ አመት ተማሪዎች ጋር
ጥያቄዎችም ምንቀበል ይሆናል
የካቲት 30/6/2017 ዓ/ም
ቡሌ ሆራ(ሀ/ማርያም






++ በሰንበት መፍረስ ++

የኢያሪኮ ሰዎች የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ኃይል በመናቃቸው ምንኛ ተጎዱ?! እርሱ ዓለምን የፈጠረ መሆኑን ስላላመኑ እንዳልተፈጠሩ የሆኑት የኢያሪኮ ሰዎች መጨረሻ እጅግ አሳዛኝ ነበር፡፡

ቅጥራቸው ከመፍረሱ በፊት እስራኤል የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ለስድስት ቀናት ያህል በዝምታ ኢያሪኮን ዞሯት፡፡ ዓለምን በስድስት ቀናት የፈጠረውን ጌታ እንዲያስተውሉ ስድስት የዝምታ ቀናት ተሠጧቸው፡፡ በሰባተኛው ቀን ግን ጮኹ የኢያሪኮም ቅጥር ፈረሰ፡፡

ሰባተኛ ቀን የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ለኢያሪኮ ግን የመፍረስ ቀን ሆነባት፡፡ ሰባተኛ ቀን ፈጣሪን ለሚያምኑ የተቀደሰ ቀን ነበር ፤ ለኢያሪኮ የመረገም ቀን ሆነባት፡፡
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ ባየበት ሰባተኛ ቀን ኢያሪኮ ግን ከፉ እንደሆነች ታየባት፡፡

እግዚአብሔር የሌለበት ሕይወት እንዲህ ነው፡፡ ወዳጄ እግዚአብሔር በሕይወትህ ውስጥ ከሌለ የሰንበት ቀን የነፍስህ ዕረፍት ቀን መሆኑ ይቀርና እንደ ኢያሪኮ የመፍረስ ቀን ይሆናል፡፡ በዚያ ቅዱስ ቀን ቅጥርህን በመጠጥ ፣ ብስካር ብዝሙት ስታፈርስ ትውልና ታድራለህ፡፡ ራስህን አንድደህ ትሞቃለህ ፤ እያራገብህ ትቃጠላለህ፡፡ ታቦት ይዘው ቢዞሩህም የኃጢአት ግንብን አጥረሃልና አትሰማም፡፡ በላይህ ላይ ቢቀደስብህም እንደ ኢያሪኮ ሰዎች ካህናቱን እያየህ ‘ዝም ብሎ መዞር ምንድር ነው?’ እያልክ ትስቃለህ፡፡ የካህናቱ የቅዳሴ ዜማ ለአንተ የሚያፈርስ ጩኸት ይሆንብሃል፡፡ የኢያሪኮ ሰው ከመሆን ፣ በሰንበት ፈራሽ ከመሆን ያድንህ!

ቅዳሴያችን መካከል ካህኑ ዕጣን እያጠኑ ዞረው ሲመለሱ የዚህች አጭር ጽሑፍ መነሻ ሃሳብ የሆነውን ይህንን ጸሎት ይጸልያሉ፦ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አስቀድመህ በባሪያህ በነዌ ልጅ በኢያሱ እጅ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረስከው የእኔንና የሕዝብህን የኃጢአታችንን ግንብ አፍርሰው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 9 /2012

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h


ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ አብረው ይፀልያሉ አንደኛው ፀሎቱ ተመለሰለት አንደኛው ሳይመለስለት ቀረ። በዚህ ጊዜ ፀሎቱ ያልተመለሰለት ሰው "ጌታ ሆይ ሁለታችንም እኩል ፀልየን ለእርሱ ሰጥተኸው ለእኔ ከለከልኝ ለምንድ ነው?" አለው። እግዚዘብሔርም "ለእርሱ ባልሰጠው ይጠፋል፣ ላንተ ከሰጠሁህ ደግሞ ትጠፋለህ" አለው ይባላል።

እግዚአብሔር ከራሳችን በላይ እኛን ያውቀናል። ለአንዳችን በመስጠት፣ አንዳችንን በመከልከል ዕድሜያችንን ያረዝመዋል። መስጠቱም መንሳቱም ሁለቱም በፍቅር ነውና በልመናችን በፀሎታችን የአንተ ፈቃድ ይሁንልን ማለት ተገቢ ነው። ስለሁሉም የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን። አሜን!!

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h




በtiktok አንድ መቶ ሺ ቤተሰብ ደርሰናል የረዳኝ እግዚአብር የተመሰገነ ይሁን አሁንም እግዚአብሔር ቢወድና ቢፈቅድ በቅርቡ በLivE መሰረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርቶች መማማር ስለ ምንጀምር ቤተሰብ ያልሆናችሁ
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h


+ ጊዮርጊስ ሆይ ከእኛ ወገን ነህን? +

ወደ አድዋ ከዘመተው ሕዝብ አብዛኛው ባዶ እግሩን ነበር:: ዳዊት ጎልያድን ሊዋጋ ሲወጣ ከያዛት በትር በቀር አብዛኛው ሰው መሣሪያ አልታጠቀም:: አብዛኛው ዘማች ባዶ እጁን የዘመተው ሁለት ነገር አስቦ ነው:: መሣሪያ ባይኖረውም በውጊያው መካከል ከጠላት ጦር መሣሪያ ነጥቄ እዋጋለሁ አለዚያም ከሚወድቁት ላይ መሣሪያ አንሥቼ እዋጋለሁ ብሎ ነበር:: በውጊያው መድፍ በጎራዴ እስከመማረክ ያደረሳቸውም ይህ ቆራጥነታቸው ነበር::

ለመንፈሳዊ ጥንካሬያቸው ደግሞ ምሥጢሩ አብራ የዘመተችው የቤተ ክርስቲያን ጸሎት እና ንጉሡ በድንግል ማርያም ስም ምለው የሠጡት አደራ ነበር:: ለተገፉ የሚቆመው ሰማዕቱ ጊዮርጊስም በግፍ ባሕር አቁዋርጠው በደሃ ሕዝብ ላይ እሳት ከሚያዘንቡት ከአባቱ ዘመዶች ከሮማዊያን ጋር ሳይሆን እንደ ዳዊት በትር ይዘው በእግዚአብሔር ስም ከወጡት ባለማተቦች ጋር በምልጃው ተሰልፎ ዋለ::

በዚያች ዕለት አንድ ጣሊያናዊ ቅዱስ ጊዮርጊስን አግኝቶ ኢያሱ ቅዱስ ሚካኤልን እንደጠየቀው "ከእኛ ወገን ነህ ወይንስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? " ብሎ ቢጠይቀው ኖሮ "እኔ አሁን ከእግዚአብሔር ተልኬ መጥቻለሁ ይልቅስ የቆምክባት መሬት ኢትዮጵያ የተቀደሰች ናትና ጫማህን ከእግርህ አውልቅ" ባለው ነበር::

የዐድዋ ዘማቾች ጾመኞች ነበሩ:: እንግሊዝም ጣሊያንም ሰይጣን ይመስል ኢትዮጵያን የተዋጉአት በዐቢይ ጾም ነበር:: "ወድቀህ ብትሰግድልኝ መንገድና ፎቅ እሰራልሃለሁ" ያለንን ጣሊያን አባቶቻችን "ሒድ አንተ ጣሊያን የራስህን እንጂ የእኔን አታስብምና" ብለው ድል ነሡት::

ዘማቾቹ የምግብ እጥረት ቢኖርም እንኩዋን ጾሙን ትተን ካልበላን አላሉም:: ድንገት መሞቴ አይቀር ብበላ ይሻለኛል ሳይሉ ተዋግተው ድል ተቀዳጁ:: እኛ በሰላም ጊዜ የምንተወውን ጾም እነርሱ በጦርነት ላይም ሆነው አልተዉትም:: በዚያ ድል  ሀገሪቱ ለዐርባ ዓመት ከጦርነት ስታርፍ ለዕድሜ ዘመንዋ ደግሞ ከቅኝ ግዛት ዐረፈች::

ቅኝ ግዛት ብንገዛ ኖሮ ደሃ አንሆንም ነበር የሚል ሰው አይጠፋም:: ይህንን አሳብ የብዙ አፍሪካውያን ሀገራት ጆሮ አይስማው:: ዛሬ ነጻ ከወጡም በኁዋላ በባርነት ሕሊና የሚሰቃዩ ብዙ ናቸው::

ብዙ በፈረንሳይ የተገዙ የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ዛሬም ድረስ በአደራ አስተዳደር በፈረንሳይ በእጅ አዙር ይተዳደራሉ:: በተባበሩት መንግሥታት ሳይቀር ቅኝ ገዢዎቻቸውን ተወካይ ሁነኝ ብለው የሚልኩ ሀገራት አሉ::

ዛሬም ድረስ በአንዳንድ አፍሪካ ሀገራት ጥቁሮች ሊስተናገዱ በተሰለፉበት ሱፐር ማርኬት አንድ ነጭ ከመጣ ሰልፍ ሳይይዝ ቅድሚያ ይስተናገዳል:: (በዓይኔ ያየሁት ነው)

ዛሬም ድረስ ብዙ አፍሪካዊያን ጥቁር በአስተሳሰብ ከነጭ በታች ነው ብለው ያምናሉ:: በዜኖ ፎቢያ የገዛ ወንድሞቻቸው አፍሪካውያንን የሚያሰቃዩ ደቡብ አፍሪካውያን ነጭ ሰፈር ግን ዝር አይሉም:: ሂሳብ ስታሰላ ሲያዩህ እንኩዋን አንተ ጥቁር ሆነህ እንዴት ያለ ካልኩሌተር መደመር ቻልክ የሚሉ ሰዎች ተፈጥረዋል::

በአውሮፓ በአሜሪካ ተወልደው አድገው ስኬታማ የሆኑት ጥቁሮች እንኩዋን የቤተሰብ ስማቸው ላይ አያቶቻቸውን በባርነት የገዛው ነጭ ገዥ ስም አብሮ ስለሚለጠፍ የዕድሜ ልክ የበታችነት ይሰማቸዋል:: አባቶቻችን ከብዙ ጣጣ አድነውናል አሁን ራሳችን የምንፈጥረውን ችግር ቢያዩ ለማመን የሚቸገሩ የሚሆኑትም ዘር ሳይለዩ አብረው የተዋደቁት ጀግኖች ናቸው:: ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬም ቤሩታዊት ኢትዮጵያን ከዘረኝነትና ጥላቻ ከመጨካከን ደራጎን ይታደጋት ዘንድ የምንማጸንበት ጊዜ ነው::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
የካቲት 23 2012 ዓ ም
ወላይታ ሶዶ ኢትዮጵያ

ፎቶ :- ሊባኖስ ቤሩት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤሩታዊትዋን ያዳነበትን ሥፍራ ተሳልሜ የተነሣሁት ነው::

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h


✞ ድንቅ አድርጎልኛል

ድንቅ አድርጎልኛል የሠራዊት ጌታ (2)
አልረሳኝም አምላክ አነሳኝ ከትቢያ (2)

ድንቅ አድርጎልኛል በደሌን ሳይቆጥር
ድንቅ አድርጎልኛል ወደቤቱ ጠራኝ
ድንቅ አድርጎልኛል ረክሼ ሳለሁ
ድንቅ አድርጎልኛል ልጄ ሆይ ና አለኝ
ድንቅ አድርጎልኛል በዳግም ምጻቱ
ድንቅ አድርጎልኛል መንግስቱን ሊያወርሰኝ

አዝ-----------------

ድንቅ አድርጎልኛል ከአንበሳ መንጋጋ
ድንቅ አድርጎልኛል ከጉድጓድ አወጣኝ
ድንቅ አድርጎልኛል በጠላቶቼ ፊት
ድንቅ አድርጎልኛል ግርማ ሞገስ ሰጠኝ
ድንቅ አድርጎልኛል ምን እመልሳለሁ
ድንቅ አድርጎልኛል እንዲ ለወደደኝ

አዝ-----------------

ድንቅ አድርጎልኛል ጠላቶቼ ሁሉ
ድንቅ አድርጎልኛል ሲጓደዱብኝ
ድንቅ አድርጎልኛል ማን ይደርስለታል
ድንቅ አድርጎልኛል እያሉ ሲሉኝ
ድንቅ አድርጎልኛል ፈጥነህ ደረስክልኝ
ድንቅ አድርጎልኛል ከሞት አዳንከኝ

መዝሙር
በ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሀኑ




#ዘወረደ_አራት_ነገሮች_ይነገሩበታል 👇
1.የአዳም ከገነት ወደ ምድረ ፋይድ መውረድ
2.የወረደውን ለመመለስ የአካላዊ ቃል ከሰማይ መውረድ
3.ከሰማይ የወረደው ጌታ የተሰቀለበት የዕፀ መስቀል ከኢየሩሳሌም ወደ ፋርስ መውረድ
4.ክርስቶስ የወረደለት የእኛ ሰውነት ከጽድቅ ከቅድስና ወደ ኃጢአት መውረድ በሥጋ ወደ መቃብር በነፍስ ወደ ሲኦል ይነገርበታል!

ለአራቱም ከፍታ/መመለስ/ትንሣኤ/ዕርገት አላቸው 👇
1.አዳም ወደ ገነት ተመልሷል
2.ክርስቶስም ወደ ሰማይ ዐርጓል
3.ዕፀ መስቀሉም በንጉሠ ሮም ኅርቃል አማካይነት በምእመናነ ኢየሩሳሌም ጾምና ጸሎት በ 614 ዓ.ም ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሷል
4.እኛም በንስሐ እናርጋለን (ወደ ጽድቅ ወደ ቅድስና እንመለሳለን)

አጠቃላይ የጾሙ ምሥጢርም ይኸው ነው
ከፍታ የሚነገርበት በይቅርታ እግዚአብሔርን የምንመስልበት የሥጋ ሳይሆን የመንፈስ ለውጥ የምናሳይበት ነው!
👉ጾም ዕድል ነው
• የመለወጥ እድል
• ንስሓ የመግባት ዕድል
• የመቁረብ ዕድል
• ራስን የማየትና የማዳመጥ
• የጽሙና የፀጥታና የመረጋጋት ዕድል
• የጸሎትና የስግደት
• የማስቀደስ ...ከመላእክት ጋር ከቅዱሳን ከጻድቃን ከሰማዕታት ጋር የማመስገን ዕድል
• በአጠቃላይ የእግዚአብሔርን የምሕረት ፊት የማየት ዕድል ነው!!!

ጾሙን ለምሕረትና ለበረከት ድል ለመንሣት ያድርግልን🙏

ሠናይ ዐቢይ ጾም!

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው

ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h




ኹለት ጉዳዮች...
በሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረው
1ኛ፦
ነገረ ማርያም፥ እንኳን የአዳምን መርገም የተፈጥሮን ሕግ የሻረ ነው።
አሮጌው ክርክር በቤታችን እንደ አዲስ ባይነሣ ጥሩ ነበር።

ለማንኛውም፥
አምጦ መውለድ የመርገም ውጤት ነበር።
“ለሴቲቱም አለ፦ በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ።” እንዲል
ዘፍጥረት 3፥16።
ጌታችን ክርስቶስ ይኽን ቀዳማዊ(አበሳ ዘጥንት) መርገምንና ኀጢኣትን ከደመሰሰልንም በኋላ፥በሰማንያ ቀን ተጠምቀው ከእግዚአብሔር ለተወለዱ እናቶችም በምጥ መውለድ አልቀረም።
እንግዲህ ሴቶች በምጥ ስለወለዱ፥ የወደቀ ሥጋ ስለያዙ ነው እንላለን?? አንልም።

እንዲኽ የምንል ከኾነማ የክርስቶስ ቤዛነት ከመርገም ከፍሎ ያስቀረው አለ ያሰኝብናል።
ነገረ ማርያም፥ የተፈጥሮን ሕግ እንኳ የሻረ መኾኑ፥ ሰይጣን እንኳ ያወቀው ፀሓይ የሞቀው ዕውነት ነው።
ለዚኽም ምስክራችን ብዙ ነው።አንዱን ብንጠራ እንዲኽ ይለናል።
"ወሊድ ዘእንበለ መወልዲት ወዘእንበለ ሕማም፤
ያለ አዋላጅ ያለ ሕመም መውለድ"። እያለ ይደነቃል ኤራቅሊስ።

ጌታችን ክርስቶስ ከመሰቀሉ አስቀድሞ የውድቀት ውጤት የኾነው ምጥ በወሊድ ጊዜ ካላገኛት
የመርገም ምልክት የነበረ መስቀልን የድል ምልክት አድርጎት የኀጢኣት ውጤት የነበረ ሞትን በሞቱ ክቡር አድርጎት ሳለ፥ የእመቤታችን ሞት እንዴት የውድቀት ምልክት ይኾናል?አይኾንም።
ሲጠቃለል
ነገረ ማርያም፥ እንኳን የአዳምን መርገም የተፈጥሮን ሕግ የሻረ ነውና ዕፁብ ብለን ማለፍ ይሻለናል።

2ኛ፦
በማኅበራዊ ሚዲያ ብዙ ወጣት ከሚሰማቸው አንዱ ወንድማችን፥ አገልግሎቱን ለጊዜው እንዳቆመ ሰማኹ። እኔ ግን እላለኹ። አገልግሎቱን ከምታቆም አቋምኽን አስተካክል። ምን ማለት ነው? ዕይታኽ ከውስጥ ወደ ውጭ ይኹን።
እና ደግሞ በአብነት ትምህርት ወይም በነገረ መለኮት ትምህርት ቤት የሚነሱ አከራካሪ ጉዳዮችን በማኅበራዊ ሚዲያ አታንሣ።
የጥብርያዶስ ቀለም ለዮርዳኖስ አይኾንም። ቦታው አይደለምና።

ወንድማችን ላይ ጥርጣሬ ያለን ሰዎች፦
ከመቶ ዘጠና ያመጣውን ተፈታኝ ከትምህርት ማባረር አግባብ አይደለም። ሙሉ በሙሉ ፈተናውን እንዲያልፍ ከተፈለገ እንዲያነብብ ያነበበውን በውስጣዊ ዐይን እንዲረዳ ማድረግ ነው ትርፍ። ማባረር ኪሳራ ነው።

ውስጣዊ ዐይን የምለው ምኑን መሰላችኹ?
ኹሉም የሊቃውንት መጻሕፍት ትርጓሜዎች ናቸው። ለምሳሌ የቄርሎስ የዮሐንስ... መጻሕፍት ሃይማኖተ አበውን ጨምሮ ራሳቸው ሊቃውንቱ ሲጽፏቸው በትርጓሜ መልክ ነው።
የእኛ ሊቃውንት ደግሞ ትርጓሜውን ተረጎሙት። ዐውድ እንዳንስት በሀገርኛ ምሳሌ አብራሩት። የሊቃውንት መጻሕፍት የትርጓሜ ትርጓሜ ናቸው። ውስጣዊ ዐይን ያልኩት ይኽ ነው።

Edited
"የወደቀ ሥጋ ማለት ሞት የሚስማማው ማለት ነው" የሚል መልስ እያየኹ ነው፡፡ መልካም፡፡
አዳም ከመውደቁ በፊት ሞት የሚስማማው እንጂ የማይስማማው አልነበረምኮ፡፡ ስለኾነም "የወደቀ ሥጋ" ማለትና ሞት የሚስማማው ማለት፥ እንዴት አንድ እንደሚኾን ለሚነግረኝ ሰው እርማቴ ፈጣን ነው፡፡

መጭው ዐቢይ ጾም የፍቅር ጾም ይኹንልን።






እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና
የሐዋርያት ሥራ 4-12


1 በገና በ437,000 ብር በጨረታ ተሽጧል።

በዕለተ ሰንበት የመቄዶንያ ገቢ ማሰባሰብ ዘመቻ ከኤማን የዜማ መሳሪያ ማሰልጠኛ የተበረከተው ይህ በገና ለጨረታ ቀርቦ ነበር።

ከአሜሪካ ሜሪላንድ በአንድ እህታችን አማካኝነት በ437,000 የኢትዮጲያ ብር ተሽጧል።

አሸናፊዋ ስሜ አይጠቀስ ያሉ እህትም በገናው ለመቄዶንያ እንዲሰጥና አንድ ሰው ሰልጥኖ ለአረጋውያኑ እንዲዘምርላቸው እንደሚፈልጉ ነገሩን።

ኤማን ማሰልጠኛም ከመቄዶንያ አንድ ሰው በነጻ እንደሚያሰለጥን ቃል ገብቷል።

ቢኒም አመስግኖ ተቀብሏል።

መስከረም ጌታቸው


በደብራችን የነበረው ልዩ ጉባኤ ሊቀ መዘመራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.