Wolkite University Registrar


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Ta’lim


It is the official telegram channel of Wolkite University Registrar Directorate.

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri




*የብሔራዊ መታወቂያ (ፍይዳ) ምዝገባን ይመለከታል*

ትምህርት ሚኒስቴ ከሰኔ 2017 ጀምሮ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ለሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች እና ዳግም ተፈታኞች ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ እንደቅድመ ሁኔታ መቀመጡ ይታወቃል። በመሆኑም በተቋማችሁ እየተማሩ ያሉና ከዚህ ቀደም ተፈትነው ማለፊያ ውጤት ሳያሟሉ የቀሩ የተቋማችሁ ተፈታኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ምዝገባ እንዲያካሂዱ ባሉት አማራጮች በሙሉ በቂ መረጃ እንድታደርሷቸው እናሳስባለን።

*ማሳሰቢያ፡*
1.ለመጀመሪያ ዙር ተፈታኞች መረጃ ማስገቢያ ሲስተም (https://eap.ethernet.edu.et ) ላይ ማስተካካያ ስልተደረገ በቅርቡ ORIENTATION የምንሰጥ ይሆናል።
2.ዳግም ተፈታኝ አመልካቾች ከሚያዝያ 14/2017 ዓ.ም -- ግንቦት 05/2017 ዓ.ም ድረስ ከላይ የተጠቀሱትን ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት በ https://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ ይችላሉ።
3.ዳግም ተፈታኞች የአገልግሎት ክፍያ የሚከፍሉት በቴሌ ብር በኩል ብቻ ነው።

*የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር*


ለመጀመርያ ዓመት ተማሪዎች በሙሉ Introduction to Emerging
Technologies Course ለመመዝገብ የምትጠቀሙበት ሊንክ https://courses.wku.edu.et/


Law Selected Students.pdf
144.8Kb
Round II_Law_Placed_2017_


#Digital_ID

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ማውጣት ይጠበቅባቸዋል።

ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች እና ሰራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ እንዲይዙ እና የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ደኅንነት ለማስጠበቅ ጠቀሜታ አለው ተብሏል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ኮራ ጡሹኔ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጻፉት ሰርኩላር፤ በዚህ ዓመት ሰኔ 2017 ዓ.ም ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ሁሉም የግል እና የመንግሥት ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ እንደ ቅድመ ሁኔታ የተቀመጠ መሆኑን አስታውሰዋል።

በመሆኑም ሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂ ተማሪዎቻቸው የፋይዳ መታወቂያ እንዲያወጡ እንዲያደርጉ እና የተማሪዎቹን የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ቁጥር በኤሜል አድራሻ eyobie2002@yahoo.com በኩል እንዲልኩ አሳስበዋል።

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባ ማድረግ መጀመራቸው ይታወቃል።


ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ ማሳሰቢያ ተሰጠ

ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ የኢንፎርሜሽን መረብ አስተዳደር ኤጄንሲ አሳስቧል።

አስተዳደሩ የኢንተርኔት አጠቃቀም በየቀኑ እየጨመረ በሄደበት በዚህ ዘመን፤ ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ስጋቶችም እየተስፋፉ መሆናቸውን ገልጿል።

በቅርቡም በርካታ አደገኛ የኢንተርኔት አድራሻዎችን (URLs) መርምሮ፣ እነዚህ አድራሻዎች የኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በይበልጥ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች አካውንቶችን በመንጠቅ ከፍተኛ ስጋት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ማረጋገጡን አስታውቋል።

እነዚህም ከተለያዩ አካላት በቴሌግራም የሚደርሱ ሊንኮች በርካታ አደጋዎችን የሚይዙ ሲሆን፤ የሚከተሉት አደጋዎች በዋናነት ይገኙበታል።

👉 የግል መረጃ መጠለፍ፦ እንደ የባንክ መለያ ወይም የይለፍ ቃል ያሉ መረጃዎችን መሰረቅ፤

👉የማልዌር ስርጭት፦ ስልኮችን ወይም ኮምፒውተሮችን የሚጎዱ ቫይረሶች፤

👉ማጭበርበሪያ፦ ተጠቃሚዎችን በሀሰተኛ ተስፋዎች (እንደ ውርርድ ወይም ኢንቨስትመንት) መታለል እንደሚገኙበት ገልጿል።

👉 ከዚሁ ጋር በተያያዘ ማኅበረሰቡ በቴሌግራሙ ላይ አጠራጣሪ የሆኑ ሊንኮች ሲያጋጥሙት፤ ለኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር  e-mail: ethiocert@insa.gov.et
ወይም ነጻ የስልክ መስመር፡ 933 ማሳወቅ የሚችል መሆኑን አስታውቋል።

👉 ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና በፍጹም ልንከፍታቸዉ ከማይገቡ ሊንኮች መካከል ጥቂቶቹ ከላይ በምስሉ ተያይዘዋል።


ማስታወቂያ ለህግ ት/ት ክፍል አመልካቾች በሙሉ ፈተና የሚሰጠው LTH 127 ከቀኑ 5:00 ( 2/08/2017) የሚጀመር መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ እናሳስባለን።


Lab_schedule_for_e_SHE_Introduction_to_emerging_technologies_course.pdf
230.0Kb
ለመጀመርያ ዓመት ተማሪዎች ለ e-SHE እና Introduction to Emerging Technologies Course የምትማሩበት የኮምውተር ላብራቶሪ ምደባ የተያያዘ ሲሆን በተመደባችሁበት ግዜ እና ቦታ በመገኘት ትምህርቱን online እንድትከታትሉ እናሳስባለን፡፡


ማስታወቂያ
ለመጀመሪያ ዓመት ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ
በተቋዎችን የህግ ትምህርት ክፍል ተጨማሪ አንድ ሴክሽን(40 ተማሪ) መቀበል ስለፈለግን ፍላጎቱ ያላችሁ other social Science የተመደባችሁ ተማሪዎች እስከ ዛሬ (1 1:30 1/08/2017 ዓ/ም) ድረስ ብቻ ዋና ሬጅስትራር እንድታመለክቱ እናሳስባለን




Did not Complete SS 6_April 2025.pdf
194.3Kb
You have to Complete SS6 Course before 29/07/2017
E.C, Unless Your Introduction to Emerging
Technologies Course Grade will be Invalid


Did not Complete SS 1_April 2025.pdf
453.5Kb
You have to Complete SS1 Course before 29/07/2017
E.C, Unless Your Introduction to Emerging
Technologies Course Grade will be Invalid


Freshman Students did not Enroll any SS Courses_April_2025.pdf
150.2Kb
❗️❗️Warning ❗️❗️ List of Freshman Students did not Enroll any SS Courses You have to report the reason to e-Learning Management office by tomorrow (24/07/2017 EC) @4:00 Local Time.




ማስታወቂያ ለ 2017 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ

እንደሚታወቀው ት/ት ሚኒስቴር ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የ2017 ዓ/ም በመደበኛ እንዲሁም በextention ፕሮግራም ተመራቂ ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ መያዝ ግዴታ እንደሆነ መግለፃችንና ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ምዝገባ መጀመራችን ይታወቃል። ነገር ግን ተመራቂ ተማሪዎች በበቂ ቁጥር እየተመዘገቡ እንዳልሆነ መረጃው ያመለክታል። ስለሆነም ተመራቂ ተማሪዎች የ መጨረሻ ብሔራዊ መታወቂያ ማውጫ ሳምንት ከሰኞ ( 22/07/2017)እስከ አርብ ( 26/07/2017) መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ ከኢትዮ ቴሌኮም የመጡት የባለ ድርሻ አካላት ከግቢ ቢወጡ እና መታወቂያውን ሳትይዙ ብትቀሩ Exit Exam መፈተን እንደማትችሉ ከውዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን።

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራር ዳይሬክትሬት ፅ/ቤት


የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ቅደመ ሁኔታ ሆነ
****
ከሰኔ 2017 ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ቅደመ ሁኔታ መቀመጡ ተገልጿል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንደሚመቻችም ነው ተቋሙ ያስታወቀው።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የተማሪዎችን እና የሰራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝና ከከፍተኛ ትምህርት መረጃ አገልግሎት ጋር በማስተሳሰር ጥራት ያለው መረጃ ለማግኘት እና የሚሰጡ ሀገር ሀቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ይረዳል።




#NGAT_Result

ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል።

ተፈታኞች ውጤታችሁን 👇
https//:result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት NGAT የሚለውን በመምረጥና የራስዎን User Name በማስገባት ውጤትዎን መመልከት ይችላሉ።




ቀን፡ 15/07/2017 ዓ.ም
ተጨማሪ መረጃ
ከአንደኛ ዓመት ተማሪዎች መካከል በዝውውር የመጡ ተማሪዎችን ሳይጨምር በ e-SHE ፖርታል ላይ ምንም ኮርስ መማር ያልጀምራችሁ ተማሪዎች ዝርዝር ተያይዞል፡፡ከላይ በማስታወቂያው የተጠቀሱትን ተግባራት በግዜው ካልፈጸማችሁ በኮርሱ የሚያዝ ውጤት እንደማይኖራችሁ እናሳውቃለን፡፡ e-SHE Portal: https:/ courses.wku.edu.et
የኤሊክትሮኒክ ትምህርት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.