ትምህርተ ሃይማኖት
ክፍል 5
❖ ሥነ ፍጥረት
ልዑል እግዚአብሔር በእውቀቱ ሰማይን ምድርን እንዲሁም በእነርሱ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉ ከምንም ወይም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ ብቁና ንቁ የሆኑ ሥነ ፍጥረታትን የፈጠረበትን ሁኔታና ሥርዓት የምንማርበት ትምህርት ሥነ ፍጥረት ይባላል፡፡
❖ ሥነ ፍጥረት ማለት፡- የፍጥረታት መበጀት/መሠራት ማለት ነው፡፡ይህ የሚታየው ዓለምና በውስጡ ያለው ሁሉ ከዚህ ከሚታየው ዓለም ውጭም ያለው የማይታይ ዓለምና በውስጡ ያሉት ረቂቃን ፍጥረታት ሁሉ በእግዚአብሔር ተፈጥረዋል። / ዘፍ1:1 መዝ 101:25 ኢሳ 66:1-2 ዕብ 11:3/
❖እግዚአብሔር ግዙፉንና ረቂቁን ዓለም የፈጠረው ከምንም ተነስቶ የሚያገናኛቸውና የሚያዋሕዳቸው ነገር ሳይኖረው /እም ኀበ አልቦ ኀበ ቦ / ካለ መኖር ወደ መኖር ነው፡፡
/መዝ 32:9 2ኛመቃ 14:10 ጥበብ11:18 የሐዋ ሥራ 17:24 መዝ 148:5/::
❖ እግዚአብሔር ፍጥረታትን የፈጠረው ሰውንና መላእክትን ስሙን ለመቀደስ ክብሩን ለመውረስ ሲሆን ሌሎችን ፍጥረታት ደግሞ ለአንክሮ ለተዘክሮ ለምግበ ሥጋና ለምግበ ነፍስ ነው/መዝ 148:1-13 ራዕ ይ4:11 ሮሜ 1:20/::
❖ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ ያከናወነው በስድስት ቀናት ውስጥ ነው፡፡/ዘፍ 1 እና 2 ዘፍ 20:9-11/
በነዚህ ቀናት የተፈጠሩት ፍጥረታት እያንዳንዳቸው ቢቆጠሩ ፍጡር ተናግሮ አይፈጽማቸውም ነበር፡፡ ነገር ግን በባህርያቸውና በአኗኗራቸው በ22 ይመደባሉ፡፡ኩፋሌ 3:9
የተፈጠሩትም በ3 መንገድ ነው ይኸውም፡-
1 በአርምሞ/በዝምታ/:- አራቱ ባሕርያተ ሥጋ ጨለማ፡መላእክት ሰማያት
2 በነቢብ/በመናገር/:- ብርሃን ጠፈር ፡እንስሳት፡ ዕፅዋት፡፡
3 በገቢር /በመስራት/:- ሰውን ብቻ፡፡
❖ የስድስቱ ቀናት ፍጥረታት
እግዚአብሔር በመጀመርያ ቀን 8 ፍጥረታትን እም ኀበ አልቦ ኀበ ቦ አምጥቶ የፈጠረ ሲሆን እነርሱም፡-
1,እሳት
2,ነፋስ
3,ውኃ
4,አፈር/መሬት/
5,ጨለማ
6,ሰማያት
7,መላእክት
8,ብርሃን ናቸው፡፡ /ዘፍ1:1/ እሳት፡ነፋስ ውኃና መሬት አራቱ ባሕርያተ ሥጋ ይባላሉ፡፡
ሰማያት ሰባት ናቸው፡፡/መዝ 18: 1 ማቴ 3:17 2ኛቆሮ 12:3 ዮሐ14:2 ዕዝ ሱቱኤል 4:4/።
ማሳሰቢያ
ለአንባብያን በትኩረት እንድትከታተሉት እና ከቻላችሁ ባላችሁበት ቦታ በማስታወሻ ማለትም በኖት ቡክ ኮፒ እያደረጋችሁ እንድታነቡ በጥብቅ ማስገንዘብ እወዳለሁ
ሊቀ ማዕምራን መዓዛ ፈንታሁን
የባሶ ሊበን ወረዳ ቤተ ክህነት
የስብከተ ወንጌል ልፍል ኃላፊ
የጁቤ
ክፍል 5
❖ ሥነ ፍጥረት
ልዑል እግዚአብሔር በእውቀቱ ሰማይን ምድርን እንዲሁም በእነርሱ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉ ከምንም ወይም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ ብቁና ንቁ የሆኑ ሥነ ፍጥረታትን የፈጠረበትን ሁኔታና ሥርዓት የምንማርበት ትምህርት ሥነ ፍጥረት ይባላል፡፡
❖ ሥነ ፍጥረት ማለት፡- የፍጥረታት መበጀት/መሠራት ማለት ነው፡፡ይህ የሚታየው ዓለምና በውስጡ ያለው ሁሉ ከዚህ ከሚታየው ዓለም ውጭም ያለው የማይታይ ዓለምና በውስጡ ያሉት ረቂቃን ፍጥረታት ሁሉ በእግዚአብሔር ተፈጥረዋል። / ዘፍ1:1 መዝ 101:25 ኢሳ 66:1-2 ዕብ 11:3/
❖እግዚአብሔር ግዙፉንና ረቂቁን ዓለም የፈጠረው ከምንም ተነስቶ የሚያገናኛቸውና የሚያዋሕዳቸው ነገር ሳይኖረው /እም ኀበ አልቦ ኀበ ቦ / ካለ መኖር ወደ መኖር ነው፡፡
/መዝ 32:9 2ኛመቃ 14:10 ጥበብ11:18 የሐዋ ሥራ 17:24 መዝ 148:5/::
❖ እግዚአብሔር ፍጥረታትን የፈጠረው ሰውንና መላእክትን ስሙን ለመቀደስ ክብሩን ለመውረስ ሲሆን ሌሎችን ፍጥረታት ደግሞ ለአንክሮ ለተዘክሮ ለምግበ ሥጋና ለምግበ ነፍስ ነው/መዝ 148:1-13 ራዕ ይ4:11 ሮሜ 1:20/::
❖ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሁሉ ፈጥሮ ያከናወነው በስድስት ቀናት ውስጥ ነው፡፡/ዘፍ 1 እና 2 ዘፍ 20:9-11/
በነዚህ ቀናት የተፈጠሩት ፍጥረታት እያንዳንዳቸው ቢቆጠሩ ፍጡር ተናግሮ አይፈጽማቸውም ነበር፡፡ ነገር ግን በባህርያቸውና በአኗኗራቸው በ22 ይመደባሉ፡፡ኩፋሌ 3:9
የተፈጠሩትም በ3 መንገድ ነው ይኸውም፡-
1 በአርምሞ/በዝምታ/:- አራቱ ባሕርያተ ሥጋ ጨለማ፡መላእክት ሰማያት
2 በነቢብ/በመናገር/:- ብርሃን ጠፈር ፡እንስሳት፡ ዕፅዋት፡፡
3 በገቢር /በመስራት/:- ሰውን ብቻ፡፡
❖ የስድስቱ ቀናት ፍጥረታት
እግዚአብሔር በመጀመርያ ቀን 8 ፍጥረታትን እም ኀበ አልቦ ኀበ ቦ አምጥቶ የፈጠረ ሲሆን እነርሱም፡-
1,እሳት
2,ነፋስ
3,ውኃ
4,አፈር/መሬት/
5,ጨለማ
6,ሰማያት
7,መላእክት
8,ብርሃን ናቸው፡፡ /ዘፍ1:1/ እሳት፡ነፋስ ውኃና መሬት አራቱ ባሕርያተ ሥጋ ይባላሉ፡፡
ሰማያት ሰባት ናቸው፡፡/መዝ 18: 1 ማቴ 3:17 2ኛቆሮ 12:3 ዮሐ14:2 ዕዝ ሱቱኤል 4:4/።
ማሳሰቢያ
ለአንባብያን በትኩረት እንድትከታተሉት እና ከቻላችሁ ባላችሁበት ቦታ በማስታወሻ ማለትም በኖት ቡክ ኮፒ እያደረጋችሁ እንድታነቡ በጥብቅ ማስገንዘብ እወዳለሁ
ሊቀ ማዕምራን መዓዛ ፈንታሁን
የባሶ ሊበን ወረዳ ቤተ ክህነት
የስብከተ ወንጌል ልፍል ኃላፊ
የጁቤ