TGStat
TGStat
Qidiruv uchun matnni kiriting
Ilg‘or kanal qidiruvi
  • flag Uzbek
    Sayt tili
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Saytga kirish
  • Katalog
    Kanal va guruhlar katalogi Kanallar qidiruvi
    Kanal/guruh qo‘shish
  • Reytinglar
    Kanallar reytingi Guruhlar reytingi Postlar reytingi
    Brendlar va shaxslar reytingi
  • Analitika
  • Postlarda qidiruv
  • Telegram'ni kuzatish
ቤተ ዝማሬ መላእክት ዘደብረ ገነት

8 Sep 2020, 10:59

Telegram'da ochish Ulashish Shikoyat qilish

የባሕረ ሐሳብ ትምህርት
ክፍል አንድ
ባሕረ ሐሳብ ማለት፤ መርሐ ዕውራን ማለት ነው አ አላዋቂዎችን መርቶ ወደ ዕውቀት የሚያደርስ ስለኾነ፤ ሐሳብ ቊጥር ነው ብፁዓን እለ ተኃድገ ሎሙ ኀጢአቶሙ ወለእለ ኢኃሰበ ሎሙ ኲሎ ጌጋዮሙ እንዲል፤ ባሕረ ሐሳብ አለው ባሕር
እስኪ ለምዱት ድረስ ያስፈራል ይገርማል፤ ከለመዱት በኋላ በልብ ተኝቶ ይውሏል ይኽም
መጽሐፍ እስኪ ለምዱት ድረስ ያስፈራል ይገርማል ከለመዱት በኋላ ብዙ ምስጢር አስታውቆ
ደስ ያሰኛልና፤ አንድም ባሕር ከለመዱት በኋላ ከመሠረቱ ወርዶ አሸዋ ይዞ ይወጧል ይኽም
መጽሐፍ ከለመዱት በኋላ ብዙ ምስጢር ያስታውቃል ያስመርምራል፤ አንድም የባሕር አዟሪቱ
መንገዱ ብዙ ነው የዚኽም መጽሐፍ መንገዱ ስልቱ ብዙ ነውና፤ አንድም ሐሳበ ባሕር
ባሕር ዘመን ነው ሠፈራ ለባሕር በመሥፈርት ወደለዋ ለዓለም በመዳልው መኑ ዘአእመረ ስፍሐ
ሰማይ ወዕመቀ ቀላይ እንዲል በባሕር ውስጥ ያለውን እግዚአብሔር እንጂ ሰው
እንዳያውቀው በዘመንም ኹሉ የሚደረገውን እግዚአብሔር እንጂ ሰው አያውቀውምና፤ ኢኮነ
ለክሙ ታእምሩ መዋዕለ ወአዝማነ ዘሠርዐ አብ እንዲል፡፡
ባሕረ ሀሳብን የአጽዋማትና የበዓላት መውጫ እንዲሆን የደረሰው ቅዱስ ድሜጥሮስ ነው
ዲሜጥሮስ ማለት መጽሔት ማለት ነው፤
አንድም ፀሓይ ማለት ነው
ሰውን በትምህርቱ ብሩህ ያደርጋልና የድሜጥሮስ ትውልዱ ነገዱ ከአዝማደ እስክንድርያ ነው ጥንተ
ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ ያባቱ ወንድም ያጐቱ ሴት ልጅ ነበረችው አባቷ ሲሞት ልጄን ከልጅህ
አትለይብኝ አደራ ብሎት ሞተ፤ አብረው አደጉ አካለ መጠን አደረሱ ዘመኑ መናፍቃን የበዙበት
ነበርና ርሱንም ከሌላ ብናጋባው ርሷንም ለሌላ ብንድራት ከሃይማኖት ይወጣሉ ከምግባር
ይጎድላሉ ሕንጻ ሃይማኖት ከሚፈርስ ሕንጻ ሥጋ ይፍረስ ዕርስ በርሳቸው እናጋባቸው ብለው መከሩ
መክረው አልቀሩም ሠርግ አደረጉ፤ ሥርዓተ ከብካቡ ሲፈጸም ሥርዓተ መርዓዊና ሥርዓተ መርዓት
ያድርሱ ብለው ከጫጉላው ቤት አግብተዋቸው ሄዱ፡፡
❖ ርሷን አስቀድሞ መንፈስ ቅዱስ አነሣሥቶ ድሜጥሮስ ያንት ወንድምነት ለኔ የኔ እኅትነት
ላንተ አልበቃ ብሎ የባዕድ ሥራ እንሥራ አልህን አለችው፤ እኔስ የናት ያባቴን ፈቃድ
ማፍረስ ይሆንብኛል ብዬ ነው እንጂ ፈቃዴም አይደል ፈቃድሽ ካልሆነ አንተወውምን አላት
እንተወው አለችው፤ እንኪያስ የተለያየን እንደኾነ አንችን ለሌላ ወንድ እኔንም ለሌላ ሴት
ያጋቡናልና መስለን እንኑር አላት እንኑር አለችው፤ በአንድ ቤት በአንድ አልጋ እየተኙ 48
ዘመን ኖሩ፤ ርሱን መልአኩ ቀኝ ክንፉን ርሷን ግራ ክንፉን እያለበሳቸው ያድራል፤ ሲነጋ
በመስኮቱ በአምሳለ ርግብ ወጥቶ ሲሄድ ያዩታል ስለምን ቢሉ በቅተዋልና አንድም
በንጽሕናቸው ይትጉበት ብሎ::
በዘመኑ የተሾመው ሊቀ ጳጳስ ሉክዮስ/ሉክያኖስ ይባላል አረጀ ደከመ፤ ሕዝቡ ተሰብስበው
አባታችን አንተ አረጀህ ደከምህ ካንተ ቀጥሎ የሚሾመውን ንገረን አሉት፤ እናንተም ወደ
እግዚአብሔር አመልክቱ እኔም ወደ እግዚአብሔር አመለክታለሁ ብሎ ቀን ቀጥሮ ሰደዳቸው
ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጣ ስሙ ድሜጥሮስ የሚባል ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን
ዘለላ ይዞ ካንተ ሊባረክ ይመጣል ካንተ ቀጥሎ የሚሾመው ዕርሱ ነው አለው፤ ሕዝቡም
በቀጠራቸው ቀን መጡ አገኛችኹት አላቸው እኛስ አላገኘንም አሉት እኔ አገኘሁላችሁ
አላቸው፤ ስሙ ድሜጥሮስ የሚባል ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ ይዞ ሊባረክ ይመጣል ከኔ
ቀጥሎ የሚሾመው እርሱ ነው ለጊዜው እንቢ ይላችኋል ግድ ብላችሁ ሹሙት አላቸው፡፡
ይኸም ድሜጥሮስ ተክል አጽድቆ ዕርፍ አርቆ የሚኖር ገበሬ ነበር ይላሉ፤ ከዕለታት በአንድ
ቀን ተክል ለመጎብኘት ከተክል ቦታ ገብቶ ሳለ ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ አገኘ ይህንስ
ከሊቀ ጳጳሱ ወስዶ ሊባረኩበት ይገባል ብሎ በንጹሕ ዕቃ አድርጎ ይዞ ሄዶ ንገሩልኝ አለ፤
እንዲህ ያል ይዞ የመጣ ሰው ከደጅ ቁሟል ብለው ነገሩት እንዲህ ያል ይዞ የመጣውን ከደጅ
ያቆሙታልን ያገቡታልን እንጂ ግባ በለው አለው፤ ገብቶ ተባርኳል፤ ከኔ ቀጥሎ የሚሾመው
ይህ ነው ብሏቸው ወዲያው ዐረፈ፤ ቀብረው ሲመለሱ ሕዝቡ ተሾምልን አሉት በማርቆስ
ወንበር የሚቀመጥ የተማረ ነው ደግሞም ንጹሕ ድንግል ነው፤ እኔ እንደምታውቁኝ ሕዝባዊ
ነኝ ደግሞም ሥጋዊ ነኝ እንደምን አድርጎ ይሆናል አላቸው፤ እኛስ አባታችን ያዘዘንን ትተን ሌላ
አንሾምም አሉት፤ ርሱም እንደማይተውት ዐውቆ ሊቀ ጳጳሱ ሲሾም ምን ያደርግላችሁ ነበር
አላቸው አንቀጸ አባግዕን አንብቦ ይተረጒምልን ነበር አሉት ወንጌል አምጡልኝ አለ፤
አመጡለት እንኳን ትርጓሜውን ንባቡን አያውቀው የነበረ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት
ተርጒሞላቸዋል፤ ይህም ብቻ አይደለም ብሉይና ሐዲስ ተርጒሟል፡፡
ከዚህ በኋላ ከደጀ ሰላም ቆሞ አንተ በቅተሃል ተቀበል አንተ አልበቃህም ቆይ እያለ
ከልክሏቸዋል፤ ሕዝቡም ቆንጆ ሚስቱን ከቤቱ አስቀምጦ እኛን ይከለክለናል ብለው
አምተውታል፤ መልአኩም ኢትፍቅድ አድኅኖ ርእስከ ወብእሲትከ አላ አድኅኖ ሕዝብከ አለው፤
እርሱም ዕንጨት እየያዛችሁ ተሰብሰቡ ብሎ ዐዋጅ ነገረ ምእመናኑም ዕንጨት እየያዙ
ተሰበሰቡ ደመራ አሠርቶ በእሳት አቃጥሎ ልብሰ ተክህኖውን ለብሶ ሊቀድስ ገባ ጸሎተ
ቅዳሴውን ፈጽሞ ልብሰ ተክህኖውን እንደለበሰ በእሳቱ መካከል እየተመላለሰ ያጥን ጀመር፤
ሚስቱም ከዚያ ነበረችና ስፍሒ አጽፈኪ ልብስሽን ዘርጊ አላት ዘረጋች እሳቱን እየታፈነ ከልብሷ
ላይ አደረገላት ልብሷ ሳይቃጠል ቀርቷል ሕዝቡም አባታችን ይህን ተአምራት ያደረግኸው
ስለምን ነው አሉት፤ አምታችሁኝ አላቸው፤ አላበጀንም በድለናል ይቅር በለን አሉት፤ ይፍታሕ
ወይኅድግ ያንጽሕ ወይስረይ ብሎ ናዟቸዋል፤ ኑዛዜ ከዚያ ወዲኽ ተጀምሯል፡፡ ዲሜጥሮስም 11ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሁኖ ተሹሟል።
ታሪክ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ተጠምቆ ሳይውል ሳያድር ገዳመ ቆሮንቶስ ሄዶ 40 ቀን ጾመ።
ይህም ማለት ጥር11 ተጠምቆ
ጥር 12 ጀምሮ እስከ የካቲት 21 ድረስ ጾመ ይህን ጾም ጌታ የጾመው በመሆኑ ዐቢይ ጾም ወይም ጾመ ኢየሱስ እንለዋለን።
ከሐዋርያት ጀምረው እስከ 241 ዓመተ ምሕረት ድረስ አካባቢ ምእመናን ዐቢይ ጾምን ጥር
12 ጀምረው የካቲት 21 ድረስ ይጾሙና።እንደገና ሰሙነ ሕማማትን ከመጋቢት
22 እስከ መጋቢት 27 ይጾሙ ነበረ።ትንሳኤንም ሰኞም ይሁን ማክሰኞም ይሁን
ብቻ መጋቢት 29 ቀን በዋለበት ቀን ያከብሩ ነበር።ሐዋርያት ግን በድድስቅሊይ
የትንሳኤ በዓል እሑድን መልቀቅ የለበትም ብለው ስርዓት ሰርተው ስለነበር
ቅዱስ ድሜጥሮስ የነነዌ ጾም የዐቢይ ጾም እና ጾመ ሐዋርያት ከሰኞ።ደብረ
ዘይት ሆሳእና ትንሳኤ ጰራቅሊጦስ ከእሁድ።ስቅለት ከአርብ።ዕርገት
ከሐሙስ።ርክበ ካህናት፥ጾመ ድኅነት ከረቡዕ ባይወጡ በወደድኩ ነበር።ብሎ
ተመኘ።መልአኩም መጥቶ ባሕረ ሀሳብን ገለጸለት።

በመሆኑም ቤተክርስቲያን ከሰከንድም ከማይክሮ ሰከንድም እጅግ በጣም የረቀቀ የዘመን
የጊዜ መለኪያ አላት
1ኛ ሳድሲት ይህ ቁጥር 0.00000185 ሰከንድ ነው።አስበውማ ከሰከንድ
እጅግ ያነሰ መለኪያ ነው።
2ኛ ኀምሲት ይህ ቁጥር 0.00011 ሰከንድ ነው።
3ኛ ራብዒት ይህ ደግሞ 0.0067 ሰከንድ ነው።
4ኛ ሣልሲት ይህ ደግሞ 0.4 ሰከንድ ነው።
5ኛ ካልዒት ይህ ደግሞ 24 ሰከንድ ነው
6ኛ ኬክሮስ ይህ ደግሞ 24 ደቂቃ ነው።

በሌላ አገላለጽ
60 ሳድሲት=1 ኃምሲት
60 ኃምሲት=1 ራብዒት
60 ራብዒት=1 ሣልሲት
60 ሣልሲት=1 ካልዒት
60 ካልዒት=1 ኬክሮስ
60 ኬክሮስ=1 ዕለት ወይም 24 ሰዓት ነው። ይህ ማለት

402 0 5
Katalog
Kanal va guruhlar katalogi Kanallar to‘plamlari Kanallar qidiruvi Kanal/guruh qo‘shish
Reytinglar
Telegram-kanallar reytingi Telegram-guruhlar reytingi Postlar reytingi Brendlar va shaxslar reytingi
API
Statistika API'si Postlar qidiruvi API'si API Callback
Kanallarimiz
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
O‘qish
Blogimiz Telegram tadqiqoti 2019 Telegram tadqiqoti 2021 Telegram tadqiqoti 2023
Kontaktlar
Справочный центр Qo‘llab-quvvatlash Email Vakansiyalar
Har xil narsalar
Foydalanuvchi shartnomasi Maxfiylik siyosati Ommaviy oferta
Botlarimiz
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot