TGStat
TGStat
Qidiruv uchun matnni kiriting
Ilg‘or kanal qidiruvi
  • flag Uzbek
    Sayt tili
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Saytga kirish
  • Katalog
    Kanal va guruhlar katalogi Kanallar qidiruvi
    Kanal/guruh qo‘shish
  • Reytinglar
    Kanallar reytingi Guruhlar reytingi Postlar reytingi
    Brendlar va shaxslar reytingi
  • Analitika
  • Postlarda qidiruv
  • Telegram'ni kuzatish
ቤተ ዝማሬ መላእክት ዘደብረ ገነት

8 Sep 2020, 11:56

Telegram'da ochish Ulashish Shikoyat qilish

ደግሞ 1 ሰዓት 2.5
ኬክሮስ ነው ማለት ነው።ስለዚህ ይህንን ካየን ካልዒትን ወደ ሣልሲት እንዲሁም
አንዱን ወደ አንዱ መለወጥ አያቅተንም ማለት ነው።
እንደሚታወቀው ፀሐይ ዓመቱን ሙሉ ብርሃኗን ትሰጣለች።በአንጻሩ ጨረቃ በቀን
በቀን ከፀሐይ 1 ኬክሮስ ከ 52 ካልዒት ከ31 ሣልሲት በአነሰ መጠን
ታበራለች።ይህንን እያንዳንዱን እንመልከተው።
በቀን 1 ኬክሮስ በ30 ቀን 30 ኬክሮስ ይሆናል።በ2 ወር 60 ኬክሮስ
ይሆናል።60 ኬክሮስ ደግሞ 1 እለት ስለሆነ።በ2 ወር 1 እለት በ12 ወር 6 እለት
ይገኛል። 52 ካልዒት 31 ሣልሲት በ12 ወር 5 ቀንና 15 ኬክሮስ ከ1 ሣልሲት
ይሆናል።52 ካልዒት×30 ቀን×12 ወር=18720 ካልዒት ይገኛል።ይህንን ወደ
ኬክሮስ ስንለውጠው 312 ኬክሮስ ይመጣል።በመቀጠል 30 ሣልሲት×30
ቀን×12 ወር 10800 ሣልሲት ይመጣል ይህንን ወደ ኬክሮስ ስንቀይረው 3
ኬክሮስ ይሆናል።ከላይኛው ጋር 312+3=315 ኬክሮስ ይሆናል።ይህንን ወደ
እለት ስንቀይረው 5 ቀን ከ15 ኬክሮስ ይሆናል።
ይህች 5 ቀን ጷግሜን ናት።ከዝያ 15 ኬክሮስ በ4 ዓመት 4×15=60 ኬክሮስ
ወይም አንድ እለት ይሆናል። በአራት ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜን 6 የምትሆን
በዚህ ምክንያት ነው።አንዷ ሣልሲት በ600 ዓመት 1 ቀን ትሆናለች።ይኽውም 1
ሣልሲት×30 ቀን×12 ወር×600 ዓመት 216000 ሣልሲት ይገኛል ይህንን ወደ
ኬክሮስ ስንቀይረው 60 ኬክሮስ ይሆናል።60 ኬክሮስ ደግሞ አንድ ቀን ወይም
እለት ነው። ስለዚህም በ600 ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜን 7 ትሆናለች ማለት ነው።

የዓለም እድሜ ስንት ነው በሚልየን ይቆጠራል ወይስ እንዴት ነው? ለሚለው
ብዙ አስተያየቶች አሉ።እኒህን ከስር መሰረቱ እንመልከት እንግዲህ ይህች ዓለም
የተፈጠረች በእለተ እሑድ ነው።ይህም እሁድ ጥንተ እለት ወይም የእለታት
መጀመሪያ ይባላል።ማክሰኞ ጥንተ ቀመር ይባላል።ረቡዕ ደግሞ ጥንተ ዖን
ይባላል።ዖን ማለት ፀሐይ ማለት ነው።ፀሐይ የተፈጠረች በዕለተ ረቡዕ
ስለሆነ።ጥንተ ዖን ማለት ፀሐይ የተፈጠረችበት የመጀመሪያ እለት እንደማለት
ነው ጥንተ ዖን ማለት።ዓለም የተፈጠረ መጋቢት 29 እሑድ ቀን ነው።ፀሐይ
የተፈጠረች ረቡዕ ስለሆነ ከረቡዕ በፊት ያለው ቀን በፀሐይ አቆጣጠር
ስላልተቆጠረ ምናልባት በሚልየን በቢልየን የሚቆጠር ዘመን ሊሆን ይችላል
ወይም በአንጻሩ በሰከንድ በደቂቃ የሚቆጠር ሊሆን ይችላል የሚሉ አሉ።ነገር
ግን ከረቡዕ በኋላ ያለውን ቀንና ከረቡዕ በፊት ያለውን ቀን ማታም ሆነ ጠዋትም
ሆነ አንድ ቀን እያለ ቀን በማለት ስለሚያስተባብረው ምንም እንኳ ፀሐይ ረቡእ
ብትፈጠርም ከረቡዕ በፊትም ጨለማንና ቀንን የሚለይ ብርሃን ነበረ።ስለዝህ
ተመሳሳይ አቆጣጠር ይኖረዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ። አዳም በእለተ አርብ
ተፈጠረ።ከ40 ቀን በኋላም ወደ ገነት እግዚአብሔር አስገባው።አዳምም
የእግዚአብሔርን ሕግ እየጠበቀ 7 ዓመት ከ3 ወር ከ17 ቀን በገነት
ተቀመጠ።ከዚያ በኋላ አትብላ የተባለውን እጸበለስ ስለበላ ተፈረደበት። አዳምም
ንሥሓ በገባ ጊዜ እግዚአብሔር ከ5500 ዘመን በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ
አድንሀለሁ የሚል ተስፋ ሰጠው።የአዳም ልጆችም ይህን ይዘው ጌታ ሰውን
ለማዳን የሚመጣበትን ጊዜ በፀሐይ በጨረቃ በከዋክብት እየቆጠሩ ይኖሩ
ነበር። የዘመን ቁጥር የተጀመረበት ምክንያቱ ይህ ነው።ጌታም
1.ኛ በ5500 ዘመን በዘመነ ዮሐንስ መጋቢት 29 እሑድ ቀን በ3 ሰዓት
ተፀነሰ
2.ኛ በ5501 ዘመን ወይም በ1 ዓመተ ምሕረት ዘመነ ማቴዎስ ታህሳስ 29
ማክሰኞ መንፈቀ ሌሊት ተወለደ።
3.ኛ 31 ዓመተ ምሕረት ዘመነ ሉቃስ ጥር 11 ማክሰኞ መንፈቀ ሌሊት
ተጠመቀ።
4.ኛ በ33 ዓመተ ምሕረት ዘመነ ማቴዎስ ነሐሴ 13 እሑድ ቀን በቀትር ጊዜ
ብርሃነ መለኮቱን ለሐዋርያት በደብረ ታቦር ገለጠ።
5.ኛ በ34 ዓመተ ምሕረት ዘመነ ማርቆስ መጋቢት 27 አርብ በቀትር ጊዜ ተሰቀለ።
6.ኛ በ34 ዓመተ ምሕረት በዘመነ ማትቆስ መጋቢት
29 እሑድ በመንፈቀ ሌሊት ተነሣ

©©አበቅቴ እና መጥቅእ©©
ከዚህ በኋላ መልአኩ አበቅቴን እና መጥቅእን ለዲሜጥሮስ ገለጸለት።አበቅቴ
ማለት ተረፈ ዘመን ማለት ነው።ይህም ማለት ጨረቃ ከፀሐይ ባነሰ የምታበራበት
የጊዜ መጠን ነው።ፀሐይ በዓመት 365 ቀን ከ15 ኬክሮስ ከ1 ሣልሲት
ታበራለች።ጨረቃ ደግሞ 11 ቀን አንሳ 354 ቀን ታበራለች።በሁለቱ መካከል
ያለው ልዩነት አበቅቴ ይባላል።መልአኩ ለዲሜጥሮስ የገለጸለት አበቅቴ ዓለም
ከተፈጠረ የመጀመሪያውን ዓመት ነው።ስለዝህ 11 ጥንተ አበቅቴ
ይባላል።ሌላው መጥቅዕ ማለት ነጋሪት ደወል ማለት ነው።ደወል ሲመታ ከሩቅ
ያሉት ተሰብስበው መጥተው እንዲገኙ ይህ መጥቅእም አጽዋማትን እና በዓላትን
የሚያስገኝ ስለሆነ ነው።መልአኩ ለዲሜጥሮስ የገለጸለት ጥንተ መጥቅእ 19
ነው።አበቅቴ እና መጥቅእ ሁለቱ ተደምረው ሁልጊዜም 30 ይሆናሉ።
ስለዚህ በመጀመሪያው ዓመት 11 አበቅቴ ከሆነ በሁለተኛው 22 ይሆናል
በሦስተኛው 33 ይሆናል።ከ30 በላይ ሲሆን በ30 አካፍለን ቀሪውን እየያዝን
አበቅቴን እናወጣለን ስለዚህ 3 ይሆናል።ከዚያ በአራተኛው 14 እያለ
ይሄዳል።አበቅቴና መጥቅእ ሁለቱ ተደምረው 30 ስለሚሆኑ አንዱ ከተገኘ
ሌላኛውን ከ30 በመቀነስ እናገኘዋለን።ምሳሌ አበቅቴ 6 ከሆነ መጥቅእ 24
ይሆናል ማለት ነው።

©©ሰባቱ አዕዋዳት®®
1ኛ ዓውደ እለት፦ይህ ከእሑድ እስከ ቅዳሜ ያሉት እለታት ናቸው።ይህም
ማለት ቅዳሜን መልሰን የምናገኘው ከሰባት ቀን በኋላ ነው።
2ኛ ዓውደ ፀሐይ፦በየ 28 ዓመቱ የሚገኝ ሲሆን ይህም ዕለትና ወንጌላዊ
ይገናኙበታል። ይህም ማለት ለምሳሌ ዛሬ ጳጉሜን 3 ማክሰኞ ቀን ዘመነ ዮሐንስ
ተመልሶ ይኸው ቀን ማለትም ጳጉሜን 3 ቀን ዘመነ ዮሐንስ እለተ ሠሉስ/ማክሰኞ
የሚገኘው የዛሬ 28 ዓመት ነው ማለት ነው።
3ኛ ዓውደ ወርኅ፦በፀሐይ 30 ቀን በጨረቃ አንድ ጊዜ 29 አንድ ጊዜ 30
የሚሆነው ነው። ይህም ማለት ለምሳሌ ሐምሌ 29 በዓለ ወልድን ከ30 ቀን በኋላ
ነሐሴ 29 እናገኛታለን ይህ ዓውደ ወርኅ ይባላል።
4ኛ ዓውደ ዓመት፦ይህ በፀሐይ 365.25 ቀን ነው። ይህም ማለት ለምሳሌ
ጳጉሜን 3ን መልሰን የምናገኘው ከ365.25 ቀን በኋላ ነው ማለት ነው።
5ኛ ዓውደ ንኡስ ቀመር ወይም ዓውደ አበቅቴ የሚባለው ደግሞ ከ19
ዓመት በኋላ የሚመላለስ ነው። ይህም ማለት ለምሳሌ ዛሬ ይህን በምታነብበት
ጊዜ ፀሐይም ካለችበት ቦታ ጨረቃም ካለችበት ቦታ በዚያው ቦታ የሚገኙት
ከ19 ዓመት በኋላ ነው። ከዚያ በፊት ግን ፀሐይ ባለችበት ብትገኝ ጨረቃ
ከሌላ ።ጨረቃ ባለችበት ስትገኝ ፀሐይ በሌላ እየሆኑ ይኖራሉ። በየ19 ዓመት ግን
መጀመርያ ከየነበሩበት ይገናኛሉ።
6ኛ ዓውደ ማእከላዊ ቀመር ወይም ዓውደ ማኅተም፦ይህ በየ 76 ዓመቱ
ይከሰታል። በዚህም ለምሳሌ በዘመነ ዮሐንስ ጳጉሜን 3 ቀን ፀሐይ እና ጨረቃ ካሉበት ቦታ መልሰን ማግኘይት ይምንችለው ዘመኑም ዘመነ ዮሐንስ ሆኖ የሚገኘው ከ76 ዓመት
በኋላ ነው። ይህም 4×19=76 ነው
7ኛ ዓውደ ዐቢይ ቀመር፦ ይህ ደግሞ 532 ዓመት ሲሆን በዚህ ወንጌላዊ
እለት እና አበቅቴ ይገናኙበታል።ይህም ማለት ለምሳሌ ጳጉሜን 3 ቀን ማክሰኞ ቀን ዘመነ ዮሐንስ ላይ አሁን ወጥታችሁ ብትመለከቱና ፀሐይም ያለችበትን ቦታ ጨረቃም
ያለችበትን ቦታ የምትይዘው ። ከዛሬ በኋላ እለቱም ምክሰኞ ቀኑ ጳጉሜን 3 ዘመኑ ዘመነ ዮሐንስ ሊሆን የሚችለው ከ532 ዓመት በኋላ ነው።
.....ክፍል ሁለት ይቀጥላል።
ማሳሰቢያ
ለግሩፑ ተከታዮች በሙሉ ይህን ጽሑፍ በትኩረ

407 0 2
Katalog
Kanal va guruhlar katalogi Kanallar to‘plamlari Kanallar qidiruvi Kanal/guruh qo‘shish
Reytinglar
Telegram-kanallar reytingi Telegram-guruhlar reytingi Postlar reytingi Brendlar va shaxslar reytingi
API
Statistika API'si Postlar qidiruvi API'si API Callback
Kanallarimiz
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
O‘qish
Blogimiz Telegram tadqiqoti 2019 Telegram tadqiqoti 2021 Telegram tadqiqoti 2023
Kontaktlar
Справочный центр Qo‘llab-quvvatlash Email Vakansiyalar
Har xil narsalar
Foydalanuvchi shartnomasi Maxfiylik siyosati Ommaviy oferta
Botlarimiz
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot