ትምህርተ ሃይማኖት
ክፍል 3
ሀልወተ እግዚአብሔር/ የእግዚአብሔር አኗኗር
ሃይማኖት ያላቸው ፍጥረታት ሰው እና
መላእክት ብቻ ሲሆኑ እነርሱም ስሙን ለመቀደስ እና ክብሩን ለመውረስ ተፈጥረዋል። ስለዚህ የእግዚአብሔርን መኖር በምን እናውቃለን???
# የፈጣሪን መኖር የሚያስረዱን የሚከተሉት ናቸው ።
1ኛ ሥነ ፍጥረት
ሕንጻ ካለ አናጺ ፣ስዕል ካለ ሰዓሊ ፣ፍጡር ካለ ፈጣሪ አለ ።
ያለ ሰዓሊ ስዕል ፣ያለ አናጺ ሕንጻ ፣ያፈጣሪ ፍጡር አይኖርም ።ስለዚህ ፈጣሪ
አለ? ብለን ከምንጠይቅ ፍጡር አለ?ብለን ብንጠይቅ ይቀላል ፍጡር ካለ
ፈጣሪም አለ ማለት ነው ፍጡር መኖሩን ለማወቅ ደግሞ ፊደል መቁጠር
አይጠይቅም ።
ሌላው ሥነ ፍጥረትን ብንመለከት ብዙ የሚነግሩን ነገር አለ ።
ለምሳሌ ፦አራዊት በሌሊት ፣ሰው በቀን እንዲሰለጥን ሰው እና አራዊት በዚህ
ጉዳይ ላይ አልተፈራረሙም ግን ይኸንን ሥርዓት ጠብቀው ለዘለዓም ይኖራሉ ።
መጽ ምሳ 30 ፥27 ይላል ።
በተጨማሪም ፦ሰው እና እፅዋት ምንም ሳይፈራረሙ በመለኮታዊ ቃል ኪዳን
ብቻ የሰውን የተቃጠለ አየር እፅዋት ይወስዳሉ ፣ የእፅዋትን ደግሞ የሰው ልጅ
ይወስዳል ።
እንዲያውም ይህንን ሰጥቶ የመቀበል ሕግ እምቢ ብሎ የሚያምጽ እንዳይኖር
እግዚያብሔር በአምላካዊ ጥበቡ የሕይወት ጉዳይ አድርጎታል ።አንድ ሰው
የእኔን ለእፅዋት አልሠጥም ፣የእፅዋትንም መቀበል አልፈልግም ቢል በራሱ ላይ
የግድያ ሙከራ እያደረገ (እያመፀ )ነው ማለት ነው ።
ስለዚህ ይህንን ሁሉ የፈጠረ ፣ የሚያስተዳድር አንድ አምላክ (ፈጣሪ) እንዳለ
ግልፅ ነው ።የማይታየው እግዚያብሔር በሥራው ይታያል ።እሱ አይታይም
ጨለማን እና ብርሃንን ሲያፈራርቅ ግን በሥራው አይተነዋል ።
ስለዚህ ፍጥረታት የፈጣሪን መኖር ያስተምሩናል መዝ 18 ፥1
2ኛ መጽሐፍ ቅዱስ
ቅዱሱ መጽሐፍ ሥራውን የሚጀምረው የፈጣሪን መኖር በማስረዳት ነው። ዘፍ 1፥1
3ኛ የኅሊና ምሥክርነት ነው
ኅሊና ማለት ፦ነፋስ ምርቱን ከገለባ እንደሚለይ የሚጠቅም እና የሚጎዳውን
የምንለይበት በተፈጥሮ የተሰጠን ታላቅ ፀጋ ነው ።
ለምሳሌ አንድ ህጻን እንደተወለደ ከእናቱ ጋር በቋንቋ አይግባባም ።
የጡትን ጥቅም ማንም ሳይነግረው ይጠባል እንደተወለደ ማንኛውም ህጻን
ዐይኑን አይጠነቁልም ይልቁንም በመዳፉ ያሸዋል እንጅ ።ታዲያ ይኸ በተፈጥሮ
የተሰጠን የኅሊና ኅግ ነው በመጽሐፍ ሳይጻፍ ጠብቀነው የምንኖር ነው ።
ዘፍ 4 ÷4 ቃኤል አትግደል የሚለው ሕግ ሳይሰራ ነው ወንድሙን የገደለው ግን
የመጽሐፍ ሕግ ባይሰጥም ኅሊና እግዚያብሔር የሰዎችን ልብ ብራና አድርጎ
የሚጽፍበት የተፈጥሮ ሕግ ስለሆነ ቃኤል ተቅበዝባዥ ሆነ ።
ኅሊናው አሳደደው ።
ኅሊና ፦ብቻውን ይከሳል፣ይመሠክራል፣ይፈርዳል።
ይ.ቀ.ጥ.ላ.ል
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ይቆየን
ማሳሰቢያ
ለአንባብያን በትኩረት እንድትከታተሉት እና ከቻላችሁ ባላችሁበት ቦታ በማስታወሻ ማለትም በኖት ቡክ ኮፒ እያደረጋችሁ በትኩረት እንድታነቡ በጥብቅ ማስገንዘብ እወዳለሁ
ሊቀ ማዕምራን መዓዛ ፈንታሁን
የባሶ ሊበን ወረዳ ቤተ ክህነት
የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ
ክፍል 3
ሀልወተ እግዚአብሔር/ የእግዚአብሔር አኗኗር
ሃይማኖት ያላቸው ፍጥረታት ሰው እና
መላእክት ብቻ ሲሆኑ እነርሱም ስሙን ለመቀደስ እና ክብሩን ለመውረስ ተፈጥረዋል። ስለዚህ የእግዚአብሔርን መኖር በምን እናውቃለን???
# የፈጣሪን መኖር የሚያስረዱን የሚከተሉት ናቸው ።
1ኛ ሥነ ፍጥረት
ሕንጻ ካለ አናጺ ፣ስዕል ካለ ሰዓሊ ፣ፍጡር ካለ ፈጣሪ አለ ።
ያለ ሰዓሊ ስዕል ፣ያለ አናጺ ሕንጻ ፣ያፈጣሪ ፍጡር አይኖርም ።ስለዚህ ፈጣሪ
አለ? ብለን ከምንጠይቅ ፍጡር አለ?ብለን ብንጠይቅ ይቀላል ፍጡር ካለ
ፈጣሪም አለ ማለት ነው ፍጡር መኖሩን ለማወቅ ደግሞ ፊደል መቁጠር
አይጠይቅም ።
ሌላው ሥነ ፍጥረትን ብንመለከት ብዙ የሚነግሩን ነገር አለ ።
ለምሳሌ ፦አራዊት በሌሊት ፣ሰው በቀን እንዲሰለጥን ሰው እና አራዊት በዚህ
ጉዳይ ላይ አልተፈራረሙም ግን ይኸንን ሥርዓት ጠብቀው ለዘለዓም ይኖራሉ ።
መጽ ምሳ 30 ፥27 ይላል ።
በተጨማሪም ፦ሰው እና እፅዋት ምንም ሳይፈራረሙ በመለኮታዊ ቃል ኪዳን
ብቻ የሰውን የተቃጠለ አየር እፅዋት ይወስዳሉ ፣ የእፅዋትን ደግሞ የሰው ልጅ
ይወስዳል ።
እንዲያውም ይህንን ሰጥቶ የመቀበል ሕግ እምቢ ብሎ የሚያምጽ እንዳይኖር
እግዚያብሔር በአምላካዊ ጥበቡ የሕይወት ጉዳይ አድርጎታል ።አንድ ሰው
የእኔን ለእፅዋት አልሠጥም ፣የእፅዋትንም መቀበል አልፈልግም ቢል በራሱ ላይ
የግድያ ሙከራ እያደረገ (እያመፀ )ነው ማለት ነው ።
ስለዚህ ይህንን ሁሉ የፈጠረ ፣ የሚያስተዳድር አንድ አምላክ (ፈጣሪ) እንዳለ
ግልፅ ነው ።የማይታየው እግዚያብሔር በሥራው ይታያል ።እሱ አይታይም
ጨለማን እና ብርሃንን ሲያፈራርቅ ግን በሥራው አይተነዋል ።
ስለዚህ ፍጥረታት የፈጣሪን መኖር ያስተምሩናል መዝ 18 ፥1
2ኛ መጽሐፍ ቅዱስ
ቅዱሱ መጽሐፍ ሥራውን የሚጀምረው የፈጣሪን መኖር በማስረዳት ነው። ዘፍ 1፥1
3ኛ የኅሊና ምሥክርነት ነው
ኅሊና ማለት ፦ነፋስ ምርቱን ከገለባ እንደሚለይ የሚጠቅም እና የሚጎዳውን
የምንለይበት በተፈጥሮ የተሰጠን ታላቅ ፀጋ ነው ።
ለምሳሌ አንድ ህጻን እንደተወለደ ከእናቱ ጋር በቋንቋ አይግባባም ።
የጡትን ጥቅም ማንም ሳይነግረው ይጠባል እንደተወለደ ማንኛውም ህጻን
ዐይኑን አይጠነቁልም ይልቁንም በመዳፉ ያሸዋል እንጅ ።ታዲያ ይኸ በተፈጥሮ
የተሰጠን የኅሊና ኅግ ነው በመጽሐፍ ሳይጻፍ ጠብቀነው የምንኖር ነው ።
ዘፍ 4 ÷4 ቃኤል አትግደል የሚለው ሕግ ሳይሰራ ነው ወንድሙን የገደለው ግን
የመጽሐፍ ሕግ ባይሰጥም ኅሊና እግዚያብሔር የሰዎችን ልብ ብራና አድርጎ
የሚጽፍበት የተፈጥሮ ሕግ ስለሆነ ቃኤል ተቅበዝባዥ ሆነ ።
ኅሊናው አሳደደው ።
ኅሊና ፦ብቻውን ይከሳል፣ይመሠክራል፣ይፈርዳል።
ይ.ቀ.ጥ.ላ.ል
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ይቆየን
ማሳሰቢያ
ለአንባብያን በትኩረት እንድትከታተሉት እና ከቻላችሁ ባላችሁበት ቦታ በማስታወሻ ማለትም በኖት ቡክ ኮፒ እያደረጋችሁ በትኩረት እንድታነቡ በጥብቅ ማስገንዘብ እወዳለሁ
ሊቀ ማዕምራን መዓዛ ፈንታሁን
የባሶ ሊበን ወረዳ ቤተ ክህነት
የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ