ትምህርተ ሃይማኖት
ክፍል 4
የእግዚአብሔር የባህርይ ቅጽል ስሞች
በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እግዚአብሔር መኖር በብዛት ከመጻፍም በላይ ስለ እርሱ የተሰጡ ባሕርዩን የሚገልጡ ቅጽል ስሞች አሉት፡፡እነሱም የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. ቅዱስ፡-
እግዚአብሔር በባህርዩ ቅዱስ ነው፡፡እርሱ ራሱ (እኔ ቅዱስ እንደሆንሁ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ፡፡) ሲል ተናግሯል፡፡ዘሌ 19፥2 1ኛ ጴጥ 1፥16 ኢሳ 6፥3 ሉቃ 1፥35
2.ጻድቅ፡- ማለት እውነተኛ ማለት ነው
እግዚአብሔር በሁሉ እውነተኛ ነው፡፡በእውነተኛነቱ ለሁሉ በትክክል ይፈርዳል፡፡1ኛ ሳሙ 2፥2 2ኛጢሞ4፥8 መዝ 114፡5 መዝ11:7 ዮሐንስ አቡቀለምሲስም
/በራዕዩ 16:7/ አዎን አቤቱ ሁሉን የምትገዛ እግዚአብሔር ሆይ ፍርድህ እውነትና ቅንነት ነው ብሏል፡፡
3. አኃዜ ኩሉ፡- /ሁሉን ያዥ/
ሰው እንቁላልን በመዳፉ እንደሚይዝ እግዚአብሔር አለምን በመዳፉ የያዘ የሁሉ ገዥ ሁሉን የሚያውቅ ሁሉን የሚችል በሁሉ ቦታ የሚኖር አምላክ ነው፡፡ሐዋርያት አመክንዮ በተባለው ቀኖና ሃይማኖት
(አእመርናሁ በኦሪት ወበነቢያት ከመ ውእቱ አኃዜ ኩሉ ወሥሉጥ ላዕለ ኩሉ ፍጥረት ) ብለዋል፡፡
4. አምላከ አማልክት ፡/የአማልክት አምላክ/ እግዚአብሔር አምላክነቱ የባሕርዩ ነው፡፡የሰዎች አማልክት መባል ግን የጸጋ ነው፡፡የጸጋ አማልክት የሚባሉትም የእግዚአብሔርን ቃል ለህዝቡ የሚያስተምሩ መምህራን ካህናት ናቸው እንጂ ጣዖታት አይደለም፡፡መዝ 81:6 ዮሐ 10፥34-36
5. እግዚአ አጋእዝት፡-የጌቶች ጌታ ፡
እግዚአብሔር ጌትነቱ የባሕርዩ ነው የሰዎች ጌቶች መባል ግን የጸጋ ነው፡፡ጌቶች የሚባሉትም መምህራን ናቸው፡፡
ስለ እግዚአብሔር የባህርይ ጌትነት ነብዩ ዳዊት (እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ)ይላል፡፡ መዝ117፥27 ዮሐ20፥28 1ኛጢሞ 6፥15 ዕብ 13፥17
6. ኤልሻዳይ፡- ሁሉን ቻይ
ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር ፈጽሞ የለም ሁሉን ማድረግ ይቻላል እግዚአብሔረ ራሱ ለአብርሃም (ሁሉን ቻይ ነኝ፡፡)/ኤልሻዳይ/ነኝ ብሎ ገልጦለታል/ዘፍ17፥1 , 18፥14 ሉቃ 1፥13 ኢሳ 40፥26 ዳን 4፥35 ኢዮ42፥2
7 ንጉሠ ነገሥት፡- የነገሥታት ንጉሥ፡ እግዚአብሔር ንጉሥነቱ /መንግስቱ/ የባህርዩ ነው የሰዎች ነገሥታት መባል ግን የጸጋ ነው፡፡ዳን 4፥3 መዝ 23፥7 ኢሳ 9፥7
8. በሁሉ ቦታ ምሉዕ፡-
እግዚአብሔር በዚህ አለ በዚህ የለም የማይባል በመለኮታዊ ሥልጣኑ ምሉዕ ሰፉህ ነው፡፡እግዚአብሔር በሚታየውም በማይታየውም ዓለም አለ ቅዱስ ዳዊት /ከመንፈስህ ወዴት እሔዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?/ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ ነህ ወደ ሲዖልም ብወረድ በዚያ አለህ እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ እስከ ባህር መጨረሻ ብበር በዚያ እጂህ ትመራለች ቀኝህም ትይዘናለች ብሏል፡፡መዝ138፥1-10 1ኛነገ 8፥27 2ኛ ዜ ና6፥18 ኢሳ 66፥1
9. ሁሉን አዋቂ፡-
እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ከመሆኑ በፊት ያውቃል። ነገሮችን ሁሉ ከመታሰባቸው ከመመሥረታቸው በፊት ያውቃቸዋል።
መዝ 138፥1-5 ዮሐ 2፥25 ኤር 17፥10 1ኛ ቆሮ 2፥11 ሕዝ 11፥5 1ኛ ሳሙ 16፥6
10. አልፋ ወዖ፡- ዘለዓለማዊ
እግዚአብሔር ከዘመን በፊት ነበር ዘመናትንም አሳልፎ የሚኖር ነው መዝ 89፥1
በአጠቃላይ እግዚአብሔር መጀመሪያ እና መጨረሻ የለውም ራሱ አነ ውእቱ አልፋ ወዖ
ቀዳማዊና ደኃራዊ እኔ ነኝ ራዕ 22፥13
አንተሰ አንተ ክመ አንተ ግን አንተ ነህ ወአመቲከኒ ዘኢየሀልቅ መዝ 101፥27
ማሳሰቢያ
ለመደበኛ ኮርስ ተማሪዎች ነገ ማክሰኞ የሚሰጠው ትምህርት ይህ ስለ ሆነ ኖት ጽፋችሁ እና አንባችሁ እንድትመጡ በጥብቅ ማስገንዘብ እወዳለሁ
ሊቀ ማዕምራን መዓዛ ፈንታሁን
የባሶ ሊበን ወረዳ ቤተ ክህነት
የስብከተ ወንጌል ልፍል ኃላፊ
የጁቤ
ክፍል 4
የእግዚአብሔር የባህርይ ቅጽል ስሞች
በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እግዚአብሔር መኖር በብዛት ከመጻፍም በላይ ስለ እርሱ የተሰጡ ባሕርዩን የሚገልጡ ቅጽል ስሞች አሉት፡፡እነሱም የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. ቅዱስ፡-
እግዚአብሔር በባህርዩ ቅዱስ ነው፡፡እርሱ ራሱ (እኔ ቅዱስ እንደሆንሁ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ፡፡) ሲል ተናግሯል፡፡ዘሌ 19፥2 1ኛ ጴጥ 1፥16 ኢሳ 6፥3 ሉቃ 1፥35
2.ጻድቅ፡- ማለት እውነተኛ ማለት ነው
እግዚአብሔር በሁሉ እውነተኛ ነው፡፡በእውነተኛነቱ ለሁሉ በትክክል ይፈርዳል፡፡1ኛ ሳሙ 2፥2 2ኛጢሞ4፥8 መዝ 114፡5 መዝ11:7 ዮሐንስ አቡቀለምሲስም
/በራዕዩ 16:7/ አዎን አቤቱ ሁሉን የምትገዛ እግዚአብሔር ሆይ ፍርድህ እውነትና ቅንነት ነው ብሏል፡፡
3. አኃዜ ኩሉ፡- /ሁሉን ያዥ/
ሰው እንቁላልን በመዳፉ እንደሚይዝ እግዚአብሔር አለምን በመዳፉ የያዘ የሁሉ ገዥ ሁሉን የሚያውቅ ሁሉን የሚችል በሁሉ ቦታ የሚኖር አምላክ ነው፡፡ሐዋርያት አመክንዮ በተባለው ቀኖና ሃይማኖት
(አእመርናሁ በኦሪት ወበነቢያት ከመ ውእቱ አኃዜ ኩሉ ወሥሉጥ ላዕለ ኩሉ ፍጥረት ) ብለዋል፡፡
4. አምላከ አማልክት ፡/የአማልክት አምላክ/ እግዚአብሔር አምላክነቱ የባሕርዩ ነው፡፡የሰዎች አማልክት መባል ግን የጸጋ ነው፡፡የጸጋ አማልክት የሚባሉትም የእግዚአብሔርን ቃል ለህዝቡ የሚያስተምሩ መምህራን ካህናት ናቸው እንጂ ጣዖታት አይደለም፡፡መዝ 81:6 ዮሐ 10፥34-36
5. እግዚአ አጋእዝት፡-የጌቶች ጌታ ፡
እግዚአብሔር ጌትነቱ የባሕርዩ ነው የሰዎች ጌቶች መባል ግን የጸጋ ነው፡፡ጌቶች የሚባሉትም መምህራን ናቸው፡፡
ስለ እግዚአብሔር የባህርይ ጌትነት ነብዩ ዳዊት (እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ)ይላል፡፡ መዝ117፥27 ዮሐ20፥28 1ኛጢሞ 6፥15 ዕብ 13፥17
6. ኤልሻዳይ፡- ሁሉን ቻይ
ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር ፈጽሞ የለም ሁሉን ማድረግ ይቻላል እግዚአብሔረ ራሱ ለአብርሃም (ሁሉን ቻይ ነኝ፡፡)/ኤልሻዳይ/ነኝ ብሎ ገልጦለታል/ዘፍ17፥1 , 18፥14 ሉቃ 1፥13 ኢሳ 40፥26 ዳን 4፥35 ኢዮ42፥2
7 ንጉሠ ነገሥት፡- የነገሥታት ንጉሥ፡ እግዚአብሔር ንጉሥነቱ /መንግስቱ/ የባህርዩ ነው የሰዎች ነገሥታት መባል ግን የጸጋ ነው፡፡ዳን 4፥3 መዝ 23፥7 ኢሳ 9፥7
8. በሁሉ ቦታ ምሉዕ፡-
እግዚአብሔር በዚህ አለ በዚህ የለም የማይባል በመለኮታዊ ሥልጣኑ ምሉዕ ሰፉህ ነው፡፡እግዚአብሔር በሚታየውም በማይታየውም ዓለም አለ ቅዱስ ዳዊት /ከመንፈስህ ወዴት እሔዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?/ወደ ሰማይ ብወጣ አንተ በዚያ ነህ ወደ ሲዖልም ብወረድ በዚያ አለህ እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ እስከ ባህር መጨረሻ ብበር በዚያ እጂህ ትመራለች ቀኝህም ትይዘናለች ብሏል፡፡መዝ138፥1-10 1ኛነገ 8፥27 2ኛ ዜ ና6፥18 ኢሳ 66፥1
9. ሁሉን አዋቂ፡-
እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ከመሆኑ በፊት ያውቃል። ነገሮችን ሁሉ ከመታሰባቸው ከመመሥረታቸው በፊት ያውቃቸዋል።
መዝ 138፥1-5 ዮሐ 2፥25 ኤር 17፥10 1ኛ ቆሮ 2፥11 ሕዝ 11፥5 1ኛ ሳሙ 16፥6
10. አልፋ ወዖ፡- ዘለዓለማዊ
እግዚአብሔር ከዘመን በፊት ነበር ዘመናትንም አሳልፎ የሚኖር ነው መዝ 89፥1
በአጠቃላይ እግዚአብሔር መጀመሪያ እና መጨረሻ የለውም ራሱ አነ ውእቱ አልፋ ወዖ
ቀዳማዊና ደኃራዊ እኔ ነኝ ራዕ 22፥13
አንተሰ አንተ ክመ አንተ ግን አንተ ነህ ወአመቲከኒ ዘኢየሀልቅ መዝ 101፥27
ማሳሰቢያ
ለመደበኛ ኮርስ ተማሪዎች ነገ ማክሰኞ የሚሰጠው ትምህርት ይህ ስለ ሆነ ኖት ጽፋችሁ እና አንባችሁ እንድትመጡ በጥብቅ ማስገንዘብ እወዳለሁ
ሊቀ ማዕምራን መዓዛ ፈንታሁን
የባሶ ሊበን ወረዳ ቤተ ክህነት
የስብከተ ወንጌል ልፍል ኃላፊ
የጁቤ