ዘሪሁን ገሠሠ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Siyosat


በመረጃ እንቀራረብ! በመረጃ እንተሳሰር!

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Siyosat
Statistika
Postlar filtri


ተገቢና ለሌሎች አካባቢዎችም አርአያ የሚሆን መልእክት ነው!

👇👇👇

ከደብረታቦር ፋኖ - ለደ/ታቦር ከተማ ነዋሪዎች የተላለፈ መልእክት‼️

1.ማንኛውም የከተማው ነዋሪ በየሰፈሩ ጥይት የሚተኩስና አካባቢን የሚረብሽ አካል ላይ መሳሪያውን ከመውረስ ጀምሮ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ እንወስዳለን፡፡

2.ፋኖም ይሁን ሌላ ግለሰብ ሁኔታዎችን እንደአጋጣሚ ተጠቅሞ ፣ የመንግስት አመራር የነበሩ አካላትንና ሌሎችንም ሲሳደብ ፣ ሲያስፈራራ ፣ ሲያሸማቅቅና ተገቢ ያልሆኑ ተግባራትን ሲፈፅም ከተገኘ በተመሳሳይ መልኩ እርምጃ ይወሰድበታል።

3.የመንግስት ሰራተኛ የሆናችሁ ከቀን 27/11/2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደስራ ገበታችሁ እንድትመለሱ። ባንኮችና ሌሎች የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም በተመሳሳይ መልኩ መደበኛ የስራ እንቅስቃሴአችሁን ያለስጋት ማከናወን እንድትጀምሩ

4.የባጃጅ አገልግሎት እስከ በጌምድር ድረስ ባለው ቀጠና መደበኛ አገልግሎት መስጠት እንዲጀመር

5. በመንግስትም ሆነ በግል ተቋማት ላይ ''በፋኖ ስም'' ለመፈፀም የሚንቀሳቀስ ማንኛውንም ግለሰብ ላይ አስቸኳይና የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድበት ከወዲሁ በአንክሮ ለማስገንዘብ እንወዳለን!

//ሐምሌ 26/11/2015 ዓ.ም - ደብረታቦር //


ተስማምተው በህብረት ያበዱት ''መንግስት ነን'' የሚሉት አካላት ፦👇

ጧት ማታ የመከራና የችግር ድግስ ከመደገሳቸው በላይ ራሳቸው የፈጠሩትን ችግር ''እንፈታለን' ብለው የሚሄዱበትና ሌላ ተራራ የሚያህል ችግር የሚያበቅል መንገድ እጅግ ያናድደኛል!

ሰዎቹ የተለከፉት ምን አይነት አስከፊ ህመም እንደሆነ ከፈጣሪ ውጭ የሆነ ጠንቋይ ካልሆነ በስተቀር ለመረዳት ያዳግታል!

ሰው በዚህ ደረጃ እንዴት ይነቅዛል ? ይደነቁራል ? ይታወራል?

የራስን ንቅዘት እንኳ መለ'ስ ብሎ ለመፈተሽ የማያስችል ክፉ ቡድናዊ ህመም....!


መረጃ‼️

ደቡብ ወሎ_ደሴ

በትናንትናው እለት በከተማዋ በሚገኜው የ'ወሎ-ባሕል-አምባ' አዳራሽ አንድ ትልቅ ስብሰባ ተከናውኗል። ስብሰባው ከዞን ፣ እና ወረዳ ሚልሻ ጽ/ቤት ዘርፍ ኃላፊዎችን ያካተተ ሲሆን ፤ በክልሉ የሚሊሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ልጃለም ፣ በደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አሳመን ፣ እና በደሴ ከተማ ከቲባ ኃላፊ በሆኑት አቶ ሳሙኤል ጥምረት የተመራ ነበር።

ከአማራ ልዩ ኃይልነት ወደ መደበኛ ፓሊስነት የገቡ የቀድሞው የልዩ ኃይሉ አባላት ፣ እና በዞኑ ውስጥ ያሉ ወረዳዎችን የጸጥታ፣ እና ሚሊሻ ዘርፍ ቢሮዎችን በኃላፊነት የሚመሩ የብልጽግና ካድሬዎች ተሳታፊዎች የነበሩ ሲሆን ፤ የመድረኩ አላማም የልዩ ኃይል አባላቱን (ወደ ፖሊስነት የገቡ) በጥቅም በመደለል (አደራጅተን ቤት መስሪያ መሬት እንሰጣለን) እና በማሳመን ፤ ከየወረዳዎቹ ከሚገኙ ታጣቂ ሚሊሻዎች ጋር አቀናጂቶ በሰላም አስከባሪ ስም ወደ ወንድሞቻቼው (ፋኖ) መላክ ፣ እና እርስበርስ ማገዳደል ሲሆን ፤ መድረኩ ፍሪያማ ሳይሆን መቅረቱ ታውቋል።  በተለይ ከቀድሞዎቹ የአማራ ልዩ ኃይል አባላቱ በኩል፣ ያልተጠበቀ እና ከፍተኛ የሆነ ቅሬታ ተሰንዝሯል።

ብአዴን ልዩ ኃይሉን ከበተነ በኃላ ጭንቀት ውስጥ መግባቱ ግልጽ ሲሆን ፤ ይህንን ጭንቀቱን ለማቃለል "ሰላም አስከባሪ" የሚል ቡድን ለማዋቀር ወስኖ ወደ ስራ የገባ ሲሆን፤ በቅርቡ በክልል ም/ቤት ደረጃ የተወሰነ ሲሆን ፥ መዋቅሩም ከክልል እስከ ቀበሌ በየደረጃው የሚወርድ ሆኖ ፤ ያፈረሰውን የአማራ ልዩ ኃይልን ቦታ ተክቶ እንዲንቀሳቀስ የታለመለት ኃይል ሲሆን ፤ "የክልል ሰላም-አስከባሪ ዘርፍ" በመባል የሚጠራ መሆኑ ታውቋል።

//መረጃው ከምንጮቻችን እንደደረሰንን የቀረበ ነው።//


በድጋሜ የሚሰማኝን ለማጋራት ያህል ፦👇👇👇

በነፋስ ፍጥነት እየተጓዘ ያለውን ህዝባዊ ትግልና ቀጣይ ግቦችን ከህዝባችን ፍላጎት ጋር አሰናስኖ ለመጓዝ ፣ ትግሉ Urgent Strategic surgery and Leadership ይፈልጋል‼️

ባሻዬ! ከድል ዜናውና ከሙቀቱ ባሻገር ቅዝቃዜና በረዶ እንዳይከሰት እየተጠነቀቁና እያሰቡ መጓዝ ያስፈልጋል!

ከመነሻህ መድረሻህን ወስነህ መጓዝ ፣ ያለአንዳች ችግር ተጉዘህ በተገቢው ሰአት ላይ ከግብህ ለመድረስ ያስችልሃል!👍

መልካም ምሽት!


ማሳሰቢያ‼️

አንዳንድ በከፍተኛ ሙስና ውስጥ ተዘፍቀው ያሉ ካድሬዎች በምሽት ቢሮ ውስጥ ሰነድ በማቃጠል ''ፋኖ ነው ያረገው'' የሚል ጥላሸት ቀብተው ሰነድ በማጥፋት ፣ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ለመምታት እየሞከሩ መሆኑን ፣ ምንጮቻችን የቆቦ ማህበራት ሀላፊን ዋቢ አድርገው መረጃዎችን አድርሰውናል!

በመሆኑም ፦

ፋኖ ከህዝቡ ጋር ሆኖ የተቋማት ጥበቃና ደህንነትን ማረጋገጥ ብሎም ከተማ ውስጥ ያለን ወሮበላና አጋጣሚ ጠብቀው ለመዝረፍ ያሰፈሰፉ አንዳንድ ሀይሎች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ ተገቢውን የእርምት እርምጃ መውሰድ አለበት!


የአህያው ታሪክ..... !

//ለብአዴናዊነት የአስተሳሰብ ተሸካሚዎች በማዘኔ ምክንያት በድጋሜ የተለጠፈ//

….ከእለታት አንድ ቀን ንጉስ አንበሳ ቀበሮን ይጠራውና > ይለዋል። ቀበሮም ተደናግጦ ለአንበሳው ምግብ ፍለጋ ሲሄድ ከአህያ ጋር ይገናኛል፡፡

ይሄኔ አህያን የጦስ ዶሮ ለማድረግ የማታለያ ሀሳብ የመጣለት ቀበሮ ፥ > ብሎ በማሳመን አስከትሎት ይሄዳል፡፡

የተራበው አንበሳ አህያው ከአጠገቡ ሲደርስ ፥ ጊዜ ሳያጠፋ ተንደርድሮ ጆሮውን ግሽልጥ አድርጎ ይበላዋል፡፡ ይሄኔ አህያ ደሙን እያዘራ ሲሮጥ ከቀበሮ ጋር ይገናኛሉ፡፡

> ይለዋል፡፡

> ይልና አሳምኖ ይመልሰዋል፡፡

ድጋሜ አህያው ከአንበሳው ፊት ሲደርስ ተንደርድሮ ጭራውን ቆርጦ ይበላዋል፡፡ አሁንም አህያው ደሙን እያዘራ ሲሄድ ከደላላው ቀበሮ ጋር ይገናኛሉ፡፡

> ! >> ይለዋል፡፡

> ይልና በድጋሜ አሳምኖ ይወስደዋል፡፡

ይሄኔ አንበሳው አህያውን ደቋቁሶ ገደለው፡፡ ወደቀበሮውም ዘወር ብሎ > ሲል አዘዘው፡፡

ቀበሮ የታዘዘውን ፈፅሞ ለአንበሳው ይዞ ቀረበ፡፡ ነገርግን ይዞ ከመጣው ስጋ ውስጥ ጭንቅላቱን ስለበላው ሊገኝ አልቻለም፡፡ ይሄኔ አንበሳው በንዴት ጦፈ፡፡ > ሲልም አፈጠጠበት፡፡

ቀበሮም የዋዛ አልነበረም > ብሎ በብልሃት በማሳመን ራሱን ከሞት አዳነ ይባላል፡፡

የሠው ልጅም ህይወት ለአንድና ለሁለት ጊዜ ሲሳሳት እንዲታረም ከሰጠችው እድል መማር ካልቻለ ፥ ከውድቀቱ በኃላ የመማር እድሉ ጠባብና ከባድ ዋጋ የሚያስከፍል ሊሆን ይችላል!




የደብረ ማርቆስ ህዝብ አደባባይ ወጥቶ ፋኖን መደገፉ ያስበረገገው የደብረ ማርቆስ ብልፅግና ፅ/ቤት ኃላፊ ፥ በካድሬ ግሩፕ ያስተላለፈውን የጭንቀት መልእክት እዩልኝማ!

ለካ! አይኖቻችን ሁሉም ቦታ እንዳሉ ለመረዳት ብልጠት ይጠይቃል!😂


> ብሎ በጀት ከሚጨርስ እርባናቢስ በላይ ''ደደብ'' ተብሎ መገለፅ ያለበት ሰው ያለ አይመስለኝም!

ባሻዬ! ከኡጋንዳ ወይም ከሩዋንዳ ካልመለመልክ በስተቀር የአማራን ህዝብ የአብራክ ክፋዮች መልምለህ ሊታዘዝህ ትፈልጋለህ እንዴ ?

ስንት ጊዜ ''ትግሉ ህዝባዊ ሆኗል!'' እያልን እናስረዳችሁ?

ስለምን ወደሌሎች የምትጠቁሙትን ጣት ለአፍታ እንኳ ወደራሳችሁ ማመልከት ተሳናችሁ ?

ከቤታችሁ ውስጥ እንዴት አንድ የራሳችሁን ንቅዘትና የያዛችሁትን በእብሪት የተሞላ አደገኛ የጥፋት መንገድ የሚያሳይ መስታወት ሊጠፋ ቻለ ?

ኧረ የእናንተስ ከፋ!


የጥያቄው መልስ ይኸው ነው!

1ኛ. > ሲሉህ ፦👇

✅የአማራ ሕዝብ የኅልውና አደጋ የሆነውን ሕገ-መንግስትና ፌዴራላዊ አወቃቀር መከለስ

✅የአማራ ሕዝብ በአማራነቱ የሚደርስበትን የኅልውና አደጋ መቀልበስ

✅ የአማራ ሕዝብ ሥልታዊ ፖለቲካዊና ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ መገለል ማስቀረት

✅ የአማራን ህዝብ ተፈጥሯዊ የሆነውን የሕዝባዊና ግዛታዊ አንድነት መብት ማስከበር

✅የአማራን ህዝብ በሀገሪቱ የማህበራዊ ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የሚኖረውን ተሳትፎ ማሳደግ

✅አማራው ለአገር ልማት ባበረከተው አስተዋፅዖ እና በመልማት ፀጋው ልክ የልማት ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ ነው በላቸው።

2ኛ. > ሲሉህ ደግሞ ፦👇

> በላቸው!

3ተኛ. > የሚል ጥያቄ ከተከተለም ፦👇

> ትላቸዋለህ!

አዎ! የአማራ ህዝብ ትግል ግብ የአማራን ህዝባዊ መንግስት መመስረትን አስቀድሞ ፣ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን እኩል እናት የሆነች ፍትህና ርትእ የሰፈነባት በመከባበር ላይ የተገነባች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው!

✅ለመውጫ ያህል ፦ ዳር እስከዳር በፍጥነት እየተቀጣጠለ ያለው የአማራ ህዝብ ትግል ፍሰቱንና ግለቱን በሚመጥን ብሎም በውል የተለዩ መዳረሻ ግቦችን መሰረት ያደረገ ስትራቴጂክ ሰርጀሪ ያስፈልገዋል!

ያኮረፍክም ፣ የተደበክም ፣ ሜዳው ላይ ያለህም ኢሊት በዚህ ሰአት 'ሀሞትህን ኮስተር የግል ስሜትህን ሰተር ' አድርገህ ጧት ማታ ትግሉን ወደማገዝ ተሰማራ! ዳይ! ሰአት የለንም!

ይኸው ነው!


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
''የስንት ማእድ አጋራን'' ኢኮኖሚክ ፖሊሲ - የሠራተኛ ደመወዝ ለመክፈል እስከመቸገርና በዋጋ ግሽበት ስቃያችንን እያሳየን ያለው የገንዘብ ህትመት ...!


የመከላከያ ቃል አቀባዩ ኮረኔል ጌትነት ከወታደርነቱ ባሻገር አርቲስትም እንደሆኑ ይነገራል።

ታዲያ! ቢያንስ ፌልም ቀረፃ ላይ ተዋኒያኑ ከተሰጠው ስክሪፕት ውጭ ሲወጣ ወይም የተሳሳተ አክቲንግ ሲሰራ ''Cut'' ብለው ሲያስቆሙና ያንን ስህተት መልሶ እንዳይደግም ተነግሮት በድጋሜ ወደቀረፃ የሚመለስበትን ሂደት ጠንቅቀው ያውቃሉ።

ታዲያ ምነው ፦ ትናንት ከህወሓት ጋር ሲያዘንቡት የነበረውን መግለጫ ፣ የሚያስተላልፉትን ያልተገባ ፕሮፓጋንዳ እንዲሁም በመጨረሻም እውነት አይደበቅምና ተገልጦ የወጣውን ውድቀትና ውርደት ወደኃላ መልከት ብለው ፣ ለዛሬ መማሪያ ማድረግ ተሳናቸው ?

ስለምን ''መስሚያው ጥጥ'' ከሆነው የፖለቲካ አመራር ጋር ፣ ተመሳሳይ ውድቀትና ተመሳሳይ ስህተት እየደገሙ ሀገርን እጅግ ወደከፋ አዘቅት ውስጥ መክተትን ምርጫ አደረጉ?

ጠዋት ማታ በተመሳሳይ ድንጋይ የሚወድቅ ሰው ''እንቅፋቱ ራሱ መሆኑን ባይረዳም አንድ ቀን ግን ላይነሳ ወድቆ መቅረቱ የማይካድ ነው! ከትናንት መማር የተሳነው ዛሬ ላይ የህይወትን ሁለተኛ እድል ላያገኝ የመቻሉ ነገርም እሙን ነው!

ለሁሉም ጊዜ መልስ አለው!👍


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
እድለኞቹ!


🔥🔥🔥ሎቹ ሁለት ጊዜ ይማርኩሃል!

አንድ ጊዜ ''እጅ ወደላይ'' ብለው በአፈሙዝ ፣ ሁለተኛ ደግሞ ''እንካ በእጄ ጉረስ'' ብለው በፍቅር!❤❤❤


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
እህ አንጀቴ ተንሰፈሰፈላቸው!

'' እኛ ቂጣ በልተንና ሮጠን ያልጠገብን ህፃናት ነን! '' ሲሏቸው እንደምታዩት ቂጣውን አቅርበውላቸዋል!

ወላጆች የህፃናት ልጆቻችሁን አዋዋል ተቆጣጠሩ!


ጦርነት ሌሎች አማራጮች ሁሉ ሲዘጉብህና ህልውናህ አደጋ ላይ ሲወድቅ የምትገባበት የመጨረሻ ውሳኔ ነው!

እኔ በግሌ ዛሬም ሆነ ነገ በደም መፋሰስና በመገዳደል ፖለቲካ በፍፁም አላምንም ! እንደአለመታደል ሆነ እንጂ ለሀገሬም ፈፅሞ አልመኝላትም!

ነገርግን አማራጮችን ሁሉ ዘግቶብህ ፣ ትእግስትህን እንደፍርሃት መቻልህን እንደሽንፈት ቆጥሮ ፣ ከቃላት ይልቅ በጥይት ድምፅ መግባባትን በመምረጥ ፣ እዚህም እዚያም የጦርነትና የእልቂት ድግስ እየደገሰ ከሚጋብዝ ባላንጣ ጋር የሚደረግ ጦርነት '' ቅዱስ ጦርነት ነው!'' ብዬ አምናለሁ!


5ቱ የመንግስት ስትራቴጂዎች ፦👇

ስትራቴጂ 1 - የፋኖን ስም ማጠልሸትና ከህዝቡ መነጠል ተብሎም መከፋፈል

- ከሀይማኖት ፣ በዘረፋና በሽፍታ ተግባር ዙሪያ የተሰሩ ልብ ወለዳዊ ዶክመንተሪዎችን በማሰራትና በማሰራጨት ፣ በየመድረኩና ሚዲያዎች መጠነ ሰፊ ዘመቻ ማድረግ

ስትራቴጂ 2 - ሽምግልና

- በሽምግልና ስም የፋኖ መሪዎችን በማግባባትና ዳጎስ ያለ ገንዘብ (ቤተሰቦቻቸውን ጭምር) በአማራ ባለሀብቶች ስም በመስጠት ትጥቅ አስፈትቶ በመበታተን የተናጠል ጥቃት መፈፀም

ስትራቴጂ - 3
ስትራቴጂ - 4
ስትራቴጂ - 5

ፋኖ ራሱ ቀድሞ ደርሶባቸው አስፈላጊውን ስራ እየሰራባቸው በመሆኑ አይገለፁም!

የአማራ ህዝብ ምን አለ?👇


No_more ሿሿ😂


''አናጨው አጋጨው እንደነጋዴ ጨው!'' አለ ያገሬ ሰው!

> የሚል አቋም እየያዙ ያሉት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ቁጥር ፥ ከተራ ወታደሮች እስከ ከፍተኛ ባለማእረግ ድረስ በየጊዜው እየጨመረ ነው። ይህን ተከትሎም ''እንኳን ዘንቦብሽ እንደውም ጤዛ ነሽ'' የሆነው ተቋም ወደመከፋፈልና መካረር እያመራ ይገኛል!

እብሪተኛው ቡድን ይህን ለመቅረፍ እንደመፍትሄ አድርጎት የሰነበተው '' በማንነት እየመረጡ ማሰርን '' እልፍ ሲልም እርምጃ መውሰድን ቢሆንም ፤ አሁን ግን በማንነት አማራ የሆኑት ብቻ ሳይሆን ደቡብን ጨምሮ ከበርካታ ኢትዮጵያውያን ህዝቦች የወጡ የሰራዊቱ አባላቶች '' የመንግስትን እብደት ተከትለን አናብድም!'' እያሉ ይገኛሉ።

ከሰራዊቱ ያገኙትን አጋጣሚ ተጠቅመው የሚኮበልሉት ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ መጥቷል! በግዳጅ ላይ ሆነው ''የተሰጠንን ተልእኮ አንፈፅምም!'' የሚሉትም እየተበራከቱ ይገኛሉ! ዛሬ ወደ ራያ የተላከው የመንግስት ሀይል መካከል የተፈጠረው ሁነትም ከዚሁ ጋር የሚያያዝ ነው።

ምናልባትም በቅርብ ቀናት በሰራዊቱ ውስጥ ጎልቶ የሚወጣ አንዳች ሁነት ልንመልከት እንደምንችል በቀላሉ መገመት አያዳግትም!

መልካም ለሊት!


የምለው ለሚገባችሁ ብቻ!

በሊንጉስቲክና በፍልስፍና ትምህርት ውስጥ   '' Denotation &   Connotation '' የተለመዱ ቃላት ናቸው።

በንግግር የምንጠቀማቸው ቃላቶቻችን '' denotative and cannotative '' ትርጓሚ ሊኖራቸው ይችላል ፣ እንዲኖራቸው አድርገንም መጠቀም እንችላለን። በቀላሉ እነዚህን '' ቀጥተኛ የሆነና ቀጥተኛ ያልሆነ ትርጓሜ አለያም ''ሰምና ወርቅ'' ብለን ልንረዳቸው እንችላለን።

በዚህ ዘመን መረጃ የህይወታችንን አቅጣጫ በቅፅበት የመቀየርን ያህል አቅም ያለው እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው። በአስፈላጊነቱ ልክ ደግሞ ያለአግባብ ጥቅም ላይ ከዋለ የሚያስከትለው አደጋም የትየለሌ ነው። ስለዚህ መረጃ አሉታዊም አወንታዊም ተፅዕኖ ማሳረፍ የሚችል ፥ አለምን ያስተሳሰረ ፣ ከምንተነፍሰው ኦክስጅን በማይተናነስ መልኩ ፋይዳው የጎላ መሰረታዊ ነገር ነው።

የመረጃን አስፈላጊነት በጦርነት ውስጥ ብናየው ፦ የአሸናፊነት ደረጃውን የሚያገኘው የፕሮፓጋንዳና የመረጃ ክንፉን በሚገባ ተቆጣጥሮና መርቶ የስነልቦና ጦርነቱን ማሸነፍ የቻለው ሀይል ብቻ ነው። ከመሳሪያና ከፐርሶኔል ብዛት ይልቅ የስነ-ልቦና ጦርነቱና የመረጃ አጠቃቀም ላይ ብልጫ ያለው አሸናፊ ነው።

በመረጃ አማካኝነት ስነልቦናዊ ጦርነቱን/Psycho-Warfare  ማሸነፍ ይቻላል። ይህ ደግሞ በግንባር ከሚደረገው ጦርነት ከፍ ያለ ደረጃ ያለው የውጊያ ክንፍ ነው።

በአንፃሩ መረጃንና ፕሮፓጋንዳን በስልትና በጥበብ መምራትና ማስተላለፍ አለመቻል በራስ ላይ ከመተኮስ ያልተናነሰ ውጤትን ያስከትላል።

ለአብነት የራስህ ሀይል የሆነ አውደ-ውጊያ ላይ ከፍተኛ ጀብድ መፈፀሙን በሰማህ ቅፅበት ፣ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የቦታውን ፣ የድርጊቱንና የጊዜውን ሁኔታ ዘክዝከህ በማህበራዊ ሚዲያ ብታስተላልፍ ፣ ምናልባት የኔ የምትላቸው ሀይሎች ግዳጃቸውን ጨርሰው ከስፍራው ሳይወጡ ፣ የጠላት ሀይል እርምጃ እንዲወስድባቸው ምቹ ሁኔታ እየፈጠርክና ጥቆማ እየሰጠህ ነው ማለት ነው።

ከዚህ አኳያ ምናልባት ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ የጠላትን ስነልቦና ለማብረክረክ ፣ ለማስጨነቅና ለማስበርገግ በሚያስችል መልኩ የስነልቦና ጦርነቱን (ፕሮፓጋንዳውን) ከማስቀጠል ባለፈ ፤ በተማከለ የውሳኔ ሀሳብና የመረጃ ፍሰት ፣ መረጃዎች 'ከበሬው አፍ' ወጥተው እንዲተላለፉ ይሁንታ (የይለፍ ቃል) እስካላገኘህ ድረስ ፥ በግለሰብ ደረጃ እንኳ ምንም ማለት ላይጠበቅብህ ይችላል! ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግም ያሻል!

'' እና ምን ለማለት ነው?'' ካላችሁኝ ፦👇

በቃ!  ምንም ዝርዝር ሳያስፈልገው በአጭሩ የምላችሁ ከላይ ያነበባችሁትን ነው!

መልካም ቀን‼️


የጥንቃቄ መረጃ ‼️

ከ30 ደቂቃ በፊት በወልድያ በኩል አድርጎ ወደሳንቃ የሚጓዝ ከስድስት በላይ አይሱዙ እና ሁለት ኦራል የአብይ ሰራዊት አልፏል!

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

11 915

obunachilar
Kanal statistikasi