.....ሁለት ገፅታ....(ክፍል አምስት)
(በኹሉድ ኑሪ)
ያሬድን ከአንዷ ሴት ጓደኛችን ጋር እርቃናቸውን ተኝተው ደረስኩባቸው።የማየውን ማመን አቃተኝ ኬኩን በቁም ስለቀው ሁለቱም ደንገጥ ብለው ተነስተው አዩኝ እና መደነባበር ጀመሩ ምንም ሳልተነፍስ ፊቴን አዙሬ ስሄድ ያሬድ ልብሱን ደርቦ ከኋላዬ መጥቶ ያዘኝ ዞሬ በጥፊ ብዬው እጄን አስለቀኩትና ወደ እናቴ ቤት ሄድኩኝ ቀጥታ መኝታ ቤት ገብቼ ዘጋሁትና ኮመዲና ውስጥ ያሉትን መድኃኒቶች በሙሉ ቃምኳቸው ኻዲማችን ሁኔታዬ ስላላማራት እናቴን ጠርታ ተከትላኝ ነበርና በሩ ቢያንኳኩ አልከፈት ሲላቸው ሰብረውት ገቡ። እኔ ወድቄ አረፋ ስደፍቅ አገኙኝ ተሸካክመው ሆስፒታል ወሰደው አሳከሙኝ።ከዛን ጊዜ በኋላ በተደጋጋሚ ራሴን ለማጥፋት ሞከርኩ አልተሳካልኝም፣ በተናደድኩኝ ቁጥር ይሄው እጄን ጠባሳዎችን እንዳየሽው ነው ሁሌ እተለትለዋለው፣ጊዜው ሄዶ ከያሬድ ጋር ከተለያየን ዓመታት ቢያልፉም እኔ ግን ውሎዬን በሌላ ጫትና መጠጥ ቤት ቀይሬ ሁሌ እየሰከርኩኝ ቤቴ ለአዳር ብቻ መምጣት ጀመርኩኝ በተከታታይ እንደዚህ ሳደርግ እጄ ላይያለው ብር እየተመናመነብኝ መጣ።ግድ ስለሆነብኝ ቀን ቤቴ እየተኛው ሊመሻሽ ሲል እዚህ ቦታ መጥቼ ሱሴን ለማስታገስ ሲጋራዬን አጭሼ ባለችኝ ትንሽ ገንዘብ እያበቃቃው መጠጣት ቀጠልኩኝ በስተመጨረሻም እጄ ላይ ያለው ብር አለቀብኝ ።ከዛሬ ሦስት ቀን በፊት በጠዋት ተነስቼ እናቴን ብር እንድትሰጠኝ ጠየቅኳት እሷ ግን አልሰጥም አለችኝ ከእናቴ ጋር በዚህ ምክንያት ብዙ ተጨቃጭቅንና ትቻት ወጣው እጄ ላይ ምንም ስለሌለ እና የምሔድበት ቦታ ስላልነበር ቀጥታ ኢምራን ጋር ነበር የሄድኩት። ለእሱ ከእናቴ ጋር ምን እንደተፈጠረ ነግሬው እና ለአንድ ቀን ብቻ እሱ ጋር ማደር እንደምችል ጠየቅኩት እሱም "በደስታ ነዋ" ብሎ መለሰልኝ እና "እንደውም ዛሬ አብረን ነው ዱዓ ምናደርገው" ብሎኝ ወጥቶ ጫት ይዞ መጣ።የኢምራን ለውጥ አስገረመኝ ጫትና እንደሚጠቅም የዛን ቀን ነበረ ያወቅኩት።የዛን እለት ሁለታችንም እየቃምን እና እያጨስን አመሸን እና ሰዓቱን ስናየው በጣም ሄዷል ነገ የሚሄድበት ስላለ መተኛት እንዳለብን ነገረኝ።እኔም እሺ ብዬ የቃምንበትን አነሳስቼ ጥጌን ይዤ ተሸፋፍኜ ተኛው የሆነ ሰዓት ላይ ግን ኢምራን ቀሰቀሰኝ እና አብሮኝ መተኛት እንደሚፈልግ ነገረኝ በመጀመርያ እየቀለደ ነበር የመሰለኝ ነገር ግን እየቆየ ኢምራን በፍጹም የማላውቀው እስኪመስለኝ ሌላ ሰው እየሆነብኝ መጣ ከመጠየቅ አልፎ እየታገለኝ መጣ እኔም አይሆንም ብዬ ስታገለው ይኸው እንደምታይው እንደዚህ አድርጎ ደበደበኝ እና ከቤቱ ውሻ አድርጎ በዛ ለሊት አባረረኝ።ግራ ገባኝ መሔጂያ አጣሁኝ አንድ ጥግ ላይ ፌስታል ለብሼ ተጠቅልዬ አደርኩ።ማይነጋ የለ ነግቶልኝ ወደቤቴ ሄድኩኝ እና ክፍሌ ገብቼ ቀኑን ሙሉ ኀይለኛ እንቅልፍ ተኛው።የሆነ ሰዓት ላይ ስነቃ የሰዎች ድምፅ ተሰማኝ ማን እንደሆነ ለማየት ወደ ሳሎን ስሄድ ኢምራን እና እናቴ ቁጭ ብለው እዬተሳሳቁ ነው።በጣም ተናደድኩ ውስጤ አረረ "ፍርዲ" ብሎ ሰላም ሊለኝ ሲነሳ ተመልሼ ወደ መኝታ ገብቼ ጃኬቴን ደርቤ ወጣው እና እግሬ ወዳመራኝ ሄድኩ ግን መሄጅያ እንደሌለኝ ሳውቅ ተመለስኩ በቃ በሁሉም ነገር ተዳከምኩ መኖር ሰለቸኝ ደከመኝ ካለሁበት ስሜት መውጣት ከበደኝ ተስፋ ቆረጥኩ ለሕይወቴ መፍትሔ ሞት ብቻ እንደሆነ ተሰማኝ ካለሁበት ደቂቃ ሽራፏን በዚ ዓለም ላይ ማሳለፍ አልፈለኩም አልቅሼ እንዳይወጣልኝ የዓይኔ የእንባ ከረጢት ደርቆአል ወደ ሱቅ ሄጄ እጄ ላይ ባለው ብር ምላጭ ገዛሁና እዚው በራቹ ጋር መጥቼ ሕይወቴን ለማቆም የደም ስሬን ቆረጥኩት ግን በድጋሚ እናንተ አዳናቹኝ ይሄውልሽ ሰብሪን የኔ ሕይወት ድቅድቅ ጨለማ ነው አላህ እኔን ረስቶኛል የምኖርበት ምንም ምክንያት አልታየኝም ተስፋ ሚባል ነገር እኔ ጋር የለም ታውቂያለሽ ብዙ ጊዜ ወደ አላህ ለመመለስ እፈልግና የአብዛኞቹን የወጣት ሙስሊሞችን ነገር ሳይ ከሩቅ እሸሻለው ለምን እንደሆነ ታውቂያለሽ ሁሉም ይንቅሻል፣ይጠቋቆሙብሻል፣ቀርቦ ዳዕዋ እንደማድረግ ከሩቅ ያንጓጥጡብሻል፣የጀሀነብ መሆንሽን ቀድመው ወስነው ይነግሩሻል እና አንቺ በየት በኩል ትለወጫለሽ? ብዙ ጊዜ መንፈሴን ለማረጋጋትና ከአላህ ጋር ለማውራት ሂጃብና ቀሚስ አድርጌ ስገባ ወይ በቀሚሴ ጥበት ወይ ደግሞ የድሮ ስለሆኑ ትንሽ ያጥረኛል እናም ወይ በእጥረቱ ይጠቋቆሙብኛል በፌዝ መልክ አድርገው አላህ ተቀልብሶ ይስጥሽ ተብለው ተሳስቀው ይሄዳሉ ግማሾቹ አንቺ ሙስሊም ነሽ እንዴ ብለው አፌዘውብኝ ይሄዳሉ በቃ ከመስጂድ ከነጭራሹ ሸሸውኛ። እንግዲህ ሰብሪን የኔ ሕይወት ይሄን ይመስላል ስላዳመጥሽኝ አመሰግናለሁ" ብላ በእንባ የራሰው ፊቷ ስጠራርገው ወደ እሷ ዞሬ አቅፍኳትና ለረጅም ሰዓት አብረን ተላቀስን።በፍርዲ ቦታው እራሴን አሰብኩት ከባድ ነው በጣም ከባድ እኔ ሳስበው እንደዚህ የከበደኝ እሷ የምትኖረው እንዴት ትሁን? በቃ ሁላችንም መፅሐፍ ነን በውስጣችን ማብቂያ የሌለው የኑሮ መሰናክል፣ደስታ፣ሐዘንና፣የፌሽታ፣ለቅሶ የተቀላቀለበት ሙሉ የየራሳችን ታሪክ ያለበት መፅሐፍ ለዛ ነው አንድን መጽሐፍ በሽፋኑ አትፍረዱ ሚባለው የሰው ልጅንም ቀርበን ሳናይ ከላይ በሚታየው ገፅታ ብቻ መፍረድ ከባድ ነው።የሰው ልጅ ለሰው መድኃኒቱም መሆን ይችላል ማጥፊያ መርዙም መሆን ይችላል።
ለፍርዲ ትንሽም ቢሆን ተስፋ መስጠትልቅ እንዳለብኝ አሰብኩኝና እንዲህ አልኳት "ፍርዲ ወላሂ አንቺ ጠንካራ እሴት ነሽ እኔ አንቺን የምንመክርበት ወኔው የለኝም ግን ልልሽ የምፈልገው ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ አላህ አንቺን በጣም ይወድሻል ለዛም ነው ብዙ እድሎችን የሰጠሽ ብዙ ጊዜ እራስሽን ለማጥፋት ሞክረሽ አልተሳካልሽም አደል ለምን? ምክንያቱም እራሳቸውን ያጠፉ ሰዋች በአኼራ ከባድ ቅጣት ስለሚጠብቃቸው ምክንያቱም አላህ የሰጠሽን ሩሕ አንቺ በፍላጐትሽ ለመቋጨት ስበብያውን ስለፈጠርሽ ነው። ከያሬድ ጋር የተፈጠረው ነገር አላህ ለሁሉም ነገር ምክንያት አለው በአላህ ዘንድ የፍቅር ግንኙነት የተጠላም የማይፈቀድም ነገር ነው አደል ስለዚህ አንቺ እና እሱ እንድትለያዩ ወሰነ።ሌላው ደግሞ ከኢምራን ጋር የተፈጠረው አንቺ እና እሱ ብቻ ናቹ አደል ቤት ውስጥ ብትጮሂ ሰው አይሰማሽም ቢሰማም ወዳ ገብታ ነው ከሚል ማሕበረሰብ ጋር ነው ምንኖረው እንግዲህ አስቢው በዛን ሰዓት አንቺን መድፈር ይችል ነበር እኮ ግን አላህ ስላላለው ከቤት ደብድቦሽ ብቻ አሶጣሽ ከዛም መንገድ ላይ አደለም ለሴት ለወንድ ከባድ በሆነበት ወቅት አላህ ጠብቆሽ ቤትሽ አስገባሽ አየሽ አላህ ለሁሉም ነገር ምክንያት አለው ያልኩሽ ለዚህ ነው ምክንያቱም ላንቺ የመረጠልሽም ኸይርሽም ቤትሽ ብትኖሪ ነው ስለዚህ አላህ ውጪ የመኖር መንገዱን እንዳለ ዘጋብሽ በቃ እኮ አባትሽንም አላህ ጀነተል ፊርዶስን ይወፍቃቸው እና ኸይር ነገር እንደሰሩ ነው የሞቱት ሱብኃነክ ለዛው ያማረ አሟሟት ሸኻዳ ይዘው እስቲግፋር አድርገው ሁሉንም አፉ ብለው አደል ይኼን ሞት ስንቱ እንደሚመኘው ብታቂ እኛ የአላህ ነን ወደ እሱም ተመላሾች ነን ፍርዲ ወላሂ አላህ የሚወደውን ነው ሚፈትነው ሕይወትሽ አላበቃለትም ይሄ ገና መጀመርያው ነው ደግሞ አላህ በቁርዓኑ "ሰብረኞችን አብስሯቸው"ብሎ አደል ከአሁን ጀምረን ከአላህ እርዳታ የድሮዋን ፍርዲ ያንን ገፅታሽን ደግመን እንገነባታለን ጥርት ያለ ተውበትም እናደርጋለን እእእ ትስማሚያለሽ" ብዬ ፈገግ ብዬ ሳያት ጭንቅላቷን በአወንታ ነቀነቀችው "እሺ በይ ተነሽ አሁን እጅሽን ሳይነካው ቀስብለን ገላችንን ከመታጠብ እንጀምራለን ልብሶች እኔ ጋ
(በኹሉድ ኑሪ)
ያሬድን ከአንዷ ሴት ጓደኛችን ጋር እርቃናቸውን ተኝተው ደረስኩባቸው።የማየውን ማመን አቃተኝ ኬኩን በቁም ስለቀው ሁለቱም ደንገጥ ብለው ተነስተው አዩኝ እና መደነባበር ጀመሩ ምንም ሳልተነፍስ ፊቴን አዙሬ ስሄድ ያሬድ ልብሱን ደርቦ ከኋላዬ መጥቶ ያዘኝ ዞሬ በጥፊ ብዬው እጄን አስለቀኩትና ወደ እናቴ ቤት ሄድኩኝ ቀጥታ መኝታ ቤት ገብቼ ዘጋሁትና ኮመዲና ውስጥ ያሉትን መድኃኒቶች በሙሉ ቃምኳቸው ኻዲማችን ሁኔታዬ ስላላማራት እናቴን ጠርታ ተከትላኝ ነበርና በሩ ቢያንኳኩ አልከፈት ሲላቸው ሰብረውት ገቡ። እኔ ወድቄ አረፋ ስደፍቅ አገኙኝ ተሸካክመው ሆስፒታል ወሰደው አሳከሙኝ።ከዛን ጊዜ በኋላ በተደጋጋሚ ራሴን ለማጥፋት ሞከርኩ አልተሳካልኝም፣ በተናደድኩኝ ቁጥር ይሄው እጄን ጠባሳዎችን እንዳየሽው ነው ሁሌ እተለትለዋለው፣ጊዜው ሄዶ ከያሬድ ጋር ከተለያየን ዓመታት ቢያልፉም እኔ ግን ውሎዬን በሌላ ጫትና መጠጥ ቤት ቀይሬ ሁሌ እየሰከርኩኝ ቤቴ ለአዳር ብቻ መምጣት ጀመርኩኝ በተከታታይ እንደዚህ ሳደርግ እጄ ላይያለው ብር እየተመናመነብኝ መጣ።ግድ ስለሆነብኝ ቀን ቤቴ እየተኛው ሊመሻሽ ሲል እዚህ ቦታ መጥቼ ሱሴን ለማስታገስ ሲጋራዬን አጭሼ ባለችኝ ትንሽ ገንዘብ እያበቃቃው መጠጣት ቀጠልኩኝ በስተመጨረሻም እጄ ላይ ያለው ብር አለቀብኝ ።ከዛሬ ሦስት ቀን በፊት በጠዋት ተነስቼ እናቴን ብር እንድትሰጠኝ ጠየቅኳት እሷ ግን አልሰጥም አለችኝ ከእናቴ ጋር በዚህ ምክንያት ብዙ ተጨቃጭቅንና ትቻት ወጣው እጄ ላይ ምንም ስለሌለ እና የምሔድበት ቦታ ስላልነበር ቀጥታ ኢምራን ጋር ነበር የሄድኩት። ለእሱ ከእናቴ ጋር ምን እንደተፈጠረ ነግሬው እና ለአንድ ቀን ብቻ እሱ ጋር ማደር እንደምችል ጠየቅኩት እሱም "በደስታ ነዋ" ብሎ መለሰልኝ እና "እንደውም ዛሬ አብረን ነው ዱዓ ምናደርገው" ብሎኝ ወጥቶ ጫት ይዞ መጣ።የኢምራን ለውጥ አስገረመኝ ጫትና እንደሚጠቅም የዛን ቀን ነበረ ያወቅኩት።የዛን እለት ሁለታችንም እየቃምን እና እያጨስን አመሸን እና ሰዓቱን ስናየው በጣም ሄዷል ነገ የሚሄድበት ስላለ መተኛት እንዳለብን ነገረኝ።እኔም እሺ ብዬ የቃምንበትን አነሳስቼ ጥጌን ይዤ ተሸፋፍኜ ተኛው የሆነ ሰዓት ላይ ግን ኢምራን ቀሰቀሰኝ እና አብሮኝ መተኛት እንደሚፈልግ ነገረኝ በመጀመርያ እየቀለደ ነበር የመሰለኝ ነገር ግን እየቆየ ኢምራን በፍጹም የማላውቀው እስኪመስለኝ ሌላ ሰው እየሆነብኝ መጣ ከመጠየቅ አልፎ እየታገለኝ መጣ እኔም አይሆንም ብዬ ስታገለው ይኸው እንደምታይው እንደዚህ አድርጎ ደበደበኝ እና ከቤቱ ውሻ አድርጎ በዛ ለሊት አባረረኝ።ግራ ገባኝ መሔጂያ አጣሁኝ አንድ ጥግ ላይ ፌስታል ለብሼ ተጠቅልዬ አደርኩ።ማይነጋ የለ ነግቶልኝ ወደቤቴ ሄድኩኝ እና ክፍሌ ገብቼ ቀኑን ሙሉ ኀይለኛ እንቅልፍ ተኛው።የሆነ ሰዓት ላይ ስነቃ የሰዎች ድምፅ ተሰማኝ ማን እንደሆነ ለማየት ወደ ሳሎን ስሄድ ኢምራን እና እናቴ ቁጭ ብለው እዬተሳሳቁ ነው።በጣም ተናደድኩ ውስጤ አረረ "ፍርዲ" ብሎ ሰላም ሊለኝ ሲነሳ ተመልሼ ወደ መኝታ ገብቼ ጃኬቴን ደርቤ ወጣው እና እግሬ ወዳመራኝ ሄድኩ ግን መሄጅያ እንደሌለኝ ሳውቅ ተመለስኩ በቃ በሁሉም ነገር ተዳከምኩ መኖር ሰለቸኝ ደከመኝ ካለሁበት ስሜት መውጣት ከበደኝ ተስፋ ቆረጥኩ ለሕይወቴ መፍትሔ ሞት ብቻ እንደሆነ ተሰማኝ ካለሁበት ደቂቃ ሽራፏን በዚ ዓለም ላይ ማሳለፍ አልፈለኩም አልቅሼ እንዳይወጣልኝ የዓይኔ የእንባ ከረጢት ደርቆአል ወደ ሱቅ ሄጄ እጄ ላይ ባለው ብር ምላጭ ገዛሁና እዚው በራቹ ጋር መጥቼ ሕይወቴን ለማቆም የደም ስሬን ቆረጥኩት ግን በድጋሚ እናንተ አዳናቹኝ ይሄውልሽ ሰብሪን የኔ ሕይወት ድቅድቅ ጨለማ ነው አላህ እኔን ረስቶኛል የምኖርበት ምንም ምክንያት አልታየኝም ተስፋ ሚባል ነገር እኔ ጋር የለም ታውቂያለሽ ብዙ ጊዜ ወደ አላህ ለመመለስ እፈልግና የአብዛኞቹን የወጣት ሙስሊሞችን ነገር ሳይ ከሩቅ እሸሻለው ለምን እንደሆነ ታውቂያለሽ ሁሉም ይንቅሻል፣ይጠቋቆሙብሻል፣ቀርቦ ዳዕዋ እንደማድረግ ከሩቅ ያንጓጥጡብሻል፣የጀሀነብ መሆንሽን ቀድመው ወስነው ይነግሩሻል እና አንቺ በየት በኩል ትለወጫለሽ? ብዙ ጊዜ መንፈሴን ለማረጋጋትና ከአላህ ጋር ለማውራት ሂጃብና ቀሚስ አድርጌ ስገባ ወይ በቀሚሴ ጥበት ወይ ደግሞ የድሮ ስለሆኑ ትንሽ ያጥረኛል እናም ወይ በእጥረቱ ይጠቋቆሙብኛል በፌዝ መልክ አድርገው አላህ ተቀልብሶ ይስጥሽ ተብለው ተሳስቀው ይሄዳሉ ግማሾቹ አንቺ ሙስሊም ነሽ እንዴ ብለው አፌዘውብኝ ይሄዳሉ በቃ ከመስጂድ ከነጭራሹ ሸሸውኛ። እንግዲህ ሰብሪን የኔ ሕይወት ይሄን ይመስላል ስላዳመጥሽኝ አመሰግናለሁ" ብላ በእንባ የራሰው ፊቷ ስጠራርገው ወደ እሷ ዞሬ አቅፍኳትና ለረጅም ሰዓት አብረን ተላቀስን።በፍርዲ ቦታው እራሴን አሰብኩት ከባድ ነው በጣም ከባድ እኔ ሳስበው እንደዚህ የከበደኝ እሷ የምትኖረው እንዴት ትሁን? በቃ ሁላችንም መፅሐፍ ነን በውስጣችን ማብቂያ የሌለው የኑሮ መሰናክል፣ደስታ፣ሐዘንና፣የፌሽታ፣ለቅሶ የተቀላቀለበት ሙሉ የየራሳችን ታሪክ ያለበት መፅሐፍ ለዛ ነው አንድን መጽሐፍ በሽፋኑ አትፍረዱ ሚባለው የሰው ልጅንም ቀርበን ሳናይ ከላይ በሚታየው ገፅታ ብቻ መፍረድ ከባድ ነው።የሰው ልጅ ለሰው መድኃኒቱም መሆን ይችላል ማጥፊያ መርዙም መሆን ይችላል።
ለፍርዲ ትንሽም ቢሆን ተስፋ መስጠትልቅ እንዳለብኝ አሰብኩኝና እንዲህ አልኳት "ፍርዲ ወላሂ አንቺ ጠንካራ እሴት ነሽ እኔ አንቺን የምንመክርበት ወኔው የለኝም ግን ልልሽ የምፈልገው ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ አላህ አንቺን በጣም ይወድሻል ለዛም ነው ብዙ እድሎችን የሰጠሽ ብዙ ጊዜ እራስሽን ለማጥፋት ሞክረሽ አልተሳካልሽም አደል ለምን? ምክንያቱም እራሳቸውን ያጠፉ ሰዋች በአኼራ ከባድ ቅጣት ስለሚጠብቃቸው ምክንያቱም አላህ የሰጠሽን ሩሕ አንቺ በፍላጐትሽ ለመቋጨት ስበብያውን ስለፈጠርሽ ነው። ከያሬድ ጋር የተፈጠረው ነገር አላህ ለሁሉም ነገር ምክንያት አለው በአላህ ዘንድ የፍቅር ግንኙነት የተጠላም የማይፈቀድም ነገር ነው አደል ስለዚህ አንቺ እና እሱ እንድትለያዩ ወሰነ።ሌላው ደግሞ ከኢምራን ጋር የተፈጠረው አንቺ እና እሱ ብቻ ናቹ አደል ቤት ውስጥ ብትጮሂ ሰው አይሰማሽም ቢሰማም ወዳ ገብታ ነው ከሚል ማሕበረሰብ ጋር ነው ምንኖረው እንግዲህ አስቢው በዛን ሰዓት አንቺን መድፈር ይችል ነበር እኮ ግን አላህ ስላላለው ከቤት ደብድቦሽ ብቻ አሶጣሽ ከዛም መንገድ ላይ አደለም ለሴት ለወንድ ከባድ በሆነበት ወቅት አላህ ጠብቆሽ ቤትሽ አስገባሽ አየሽ አላህ ለሁሉም ነገር ምክንያት አለው ያልኩሽ ለዚህ ነው ምክንያቱም ላንቺ የመረጠልሽም ኸይርሽም ቤትሽ ብትኖሪ ነው ስለዚህ አላህ ውጪ የመኖር መንገዱን እንዳለ ዘጋብሽ በቃ እኮ አባትሽንም አላህ ጀነተል ፊርዶስን ይወፍቃቸው እና ኸይር ነገር እንደሰሩ ነው የሞቱት ሱብኃነክ ለዛው ያማረ አሟሟት ሸኻዳ ይዘው እስቲግፋር አድርገው ሁሉንም አፉ ብለው አደል ይኼን ሞት ስንቱ እንደሚመኘው ብታቂ እኛ የአላህ ነን ወደ እሱም ተመላሾች ነን ፍርዲ ወላሂ አላህ የሚወደውን ነው ሚፈትነው ሕይወትሽ አላበቃለትም ይሄ ገና መጀመርያው ነው ደግሞ አላህ በቁርዓኑ "ሰብረኞችን አብስሯቸው"ብሎ አደል ከአሁን ጀምረን ከአላህ እርዳታ የድሮዋን ፍርዲ ያንን ገፅታሽን ደግመን እንገነባታለን ጥርት ያለ ተውበትም እናደርጋለን እእእ ትስማሚያለሽ" ብዬ ፈገግ ብዬ ሳያት ጭንቅላቷን በአወንታ ነቀነቀችው "እሺ በይ ተነሽ አሁን እጅሽን ሳይነካው ቀስብለን ገላችንን ከመታጠብ እንጀምራለን ልብሶች እኔ ጋ