....ሁለት ገፅታ....(ክፍል ሰባት)
(በኹሉድ ኑሪ)
እኔ እና ፊርዲ እምቢ ብንልም ከረጅም ውትወታቸው በኋላ ተስማማን የምንሄድበት ቦታም ከኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢዎች አንዷ ወደሆነችው በስተምሥራቅ ወደምትገኘው ወደ ውቢቷ የፍቅር ሀገር ሀረር እንዲሆን ወስነን መንገድ ጀመርን ከረጅም ሰዓት ጉዞ በኋላ ወደ የብሄር ብሄረሰቦች መገኛ የዐማራ ፣ የኦሮሞ ፣ የሐረሪ ፣ የጉራጌና የሶማሌ እና የበርካታ ጎሳዎች ቤታችን ብለው ወደሚጠሯት በሕብረ ቀለም ወዳሸበረቀችው ውቢቷ ከተማ በሰላም ደረስን።ኢምራን ሀረር በደምብ አድርጎ ያውቃት ስለነበር ሁሉንም ቦታ ያውቅ ነበር።እዛ እንደደረስን በ ረውዳ ዋበር በሚባል ባህላዊው የሐረሪ እንግዳ ማረፊያ አረፍን በሀረሪ ለአራት በቆየንባቸው አራት ቀናቶች የሀረርን ሱስ የሚያሲዝ ቡና እየጠጣን፣የተለያዩ ሃላዋዎችን እያጣጣምን፣በሐረር የጎዳናዎች ላይ በምናያቸው ምርጥ ምርጥ ነገሮችን በ ፎቶግራፍ አንስተን ለታሪክ እያስቀመጥን፣ በአሮጌዋ ከተማ መሃል ላይ በሚገኝ ቆንጆ የህንድ ነጋዴ ቤት ውስጥ የሚገኘውን አርተር ሪምቡድ የሚባለውን ሙዚየም፣የራስ ተፈሪ ቤት ሸሪፍ ተብሎ የሚጠራው ኃይለ ሥላሴ (ራስ ተፈሪ) የጫጉላ ሽርሽራቸው ያደረጉበትን ሀረር ከተማ ሙዚየም፣ግድግዳው በቀስተ ዳመና ቀለም የጌጠውን ሐረር ጁጎልን፣በባቢሌ የሚገኘውን የሶማሊያዎች የግመል መሸጫንና በተለያዩ ስሞች የሚጠሩ የሃረር ገበያዎችን እስኪበቃን ጎበኘናቸው በስተመጨረሻም የሐረር የዱር ጅቦችን መግበን ምርጥ አይረሴ ጊዝያቶችን አሳልፈን ወደቤታችን መጣን።
ፊርዲ በጣም ደስተኛ ሆናለች እሷ ብቻ ሳትሆን ሁላችንም ነን ደስተኞች የሆነዉ አንድ ቀን እሁድ ጠዋት ላይ እኔ እና ዓሊ ቁርስ እየበላን የቤታችን በር ተንኳኳ በሩን ለመክፈት እኔ ነበር የሄድኩት ፊርዲ እና ኢምራን ነበሩ "እንዴ አሰላሙ አሌይኩም ወራኽመቱላሂ ሰዎች በሰላም ነው?" አልኳቸው
"እእ ወአለይኩም ሰለም ወራኽመቱላህ"አሉኝ በአንድ ላይ ፊርዲም"ምንድ ነው ቤታችን በፈለግነው ሰዓት መምጣት አንችልም እንዴ" አለችኝ እና ሁለታችንን ጥላን ወደውስጥ ገባች እኔም ተከትያት ልገባ ስል ኢምራን "ሰቡሪ አንዴ ላናግርሽ?" ብሎ አንገቱን በእፍረት አጎነበሰ ግራ እየገባኝ ዞርኩኝ እና"ወዬ ኢምሩ ምነው ችግር አለ እንዴ?"አልኩት"ኧረ ምንም የለም አንዴ ብቻሽን ማወራሽ ጉዳይ ነበረኝ እእ ይኸውልሽ ሰብሪኔ እእ ምን ነበር ሁፍፍ" ሲል አሳቀኝ"እንዴ ኢምሩ ምንድነው እስኪ ተረጋግተክ ንገረኝ"አልኩት "እሺ ምን መሰለሽ ሰቡሪ እእ እኔ አንቺን ማግባት እፈልጋለሁ ማለት አፈቅርሻለሁ እእ እና ማለት አለ አደል በስርዓቱ ዓሊን ጠይቄ አንቺን ሃላሌ ማድረግ እፈልጋለሁ ማለት እሱ ከማወቁ በፊት ፍቃደኝነትሽን ልወቀው ብዬ ነው"አለኝ አላውቅም ድንጋጤ ይሁን ደስታ ለረጅም ሰዓት ደንዝዤ ቀረው "ማለት ተንበርክኬ ምናምን መጠየቅ እችል ነበር ግን ያው በሸሪዓው መንገድ በስርዓቱ ልጠይቅ ብዬ ነው ማለት መብትሽ ነው ምንም ብትወስኚ እኔ አላዝንብሽም" አለኝ እኔም ከፈዘዝኩበት ብንን አልኩና በደስታ እንደምስማማ ነገርኩት በጣም ደስተኛ ሆነ ግን ከዛ በፊት ለጋብቻው እኔ ወንድሜን ማማከር እንዳለብኝ ነገርኩት በጣም ደስ ብሎኛል ነገር ግን ከዓሊ በፊት ማግባቴ እና ብቻውን ጥዬው ልወጣ እንደሆነ ሳስብ ውስጤ ተረበሸ።ሁለታችንም ተከታትለን ገባን ዓሊ ኢምራንን ተነስቶ ሰላም ብሎት ቁጭ አለ።ፊርዲ ፊት ፊታችንን መልስ ፍለጋ ታያለች ወድያሁኑ እሷ እንደሰማች ገባኝ ኢምራን ጠቀሳትና ፈገግ አለ እኔንም ስታየኝ ጭንቅላቴን በአወንታ ስነቀንቀው መልሱ ምን እንደሆነ አወቀች በጣም ደስ አላት በቃ ቡና ላፍላ እኔ ብላ ፍንጥር ብላ ተነሳች ዓሊ"እንዴ ይቺ ልጅ ዛሬ ምንሆና ነው ምትቁነጠነጠው እናንተ እስክትመጡ እኮ ስንቴ ቁጭ ብድግ እንደሰራችብኝ" ብሎ በግርምት ሲያያት እኔ እና ኢምራን ተያይተን ሳቅን የዛን ቀንን ስንጫወት አምሽተን ፊርዲ እና ኢምሩ ወደቤታቸው ሄዱ።ዓሊ ሊተኛ ሊገባ ሲል ማናግረው ነገር እንዳለ ነገርኩት ሊሰማኝ ቁጭ ሲል እየፈራው እየተንተባተብኩኝ እኔ እና ኢምራን ያወራነውን ነገርኩት እሱም በጣም ደስተኛ እንደሆነ ነገረኝ ነገር ግን "ከእናትና አባትሽ ማስታወሻ ከሆነው ቤት ወጥተሽ የኪራይ እንድትኖሪ ስለማልፈልግ ትልቁን መኝታ ቤት እለቅላቹአለው ከእዛ እኔ አንቺ ክፍል እተኛለሁ"አለኝ በአንዴ ሸክሜ ሲቀል ታየኝ ተነስቼ አቀፍኩት እሱም "እህቴ ለካ አድገሽልኛል"ብሎ አቀፈኝ ለኢምራን ዓሊ መስማማቱን እና ያቀረበውን ሃሳብ ነገርኩት መጀመሪያ ላይ ትንሽ ቢያንገራግርም በመጨረሻም ተስማማ።
በስርዓቱ ሽማግሌ ልኮ እኔን እንዲሰጠው ጠየቀ ዓሊም ከ ሁለተኛ ቀጠሮ በኋላ እሺታውን ገለፆ የሰርጉን ቀን ቆረጡ።ሰርጌ 1 ሳምንት ሲቀረው ነጅዋ ከልጆቿ እና ከባለቤቷ ጋር መጣች ደስታዬ እጥፍ ድርብ ሆነ ስለ ፊርዲ እና ኢምራንን ሁሉንም ነገር አጫውታት ስለነበር አዲስ አሎኑባትም።ከሳምንት በኋላ ሰርጉ ተደግሶ ኢምራንን የግሌ አደረግኩት አልሃምዱሊላህ ሁሉ ሃሳቤ ተሳካልኝ ነገር ግን የፊርዲ እና የዓሊ ነገር ያሳስበኝ ነበር ሁለቱን ብድራቸው ጭንቀቴ ይቀልልኝ ነበር።ጊዜ ሄደ ነጅዋም የእረፍት ቀኗን ጨርሳ የልጆቿ ትምህርት ሊጀመር ስለነበር ወደ ሀገሯ ተመለሰች።ከወራቶች በኋላ ፊርዲ የራሷን የልብስ መሸጫ ሱቅ ከፍታ አብረን እዛው መዋል ጀመርን በትርፍ ሰዓታችን ደግሞ ልጇቹን ቁርአን ማስቀራታችንን ቀጠልን አንድቀን በጣም አሞኝ ከፊርዲ ጋር ሐኪም ቤት ስንሄድ የ2ወር ነብሰጡር መሆኔን ነገሩኝ እኔ እና ፊርዶስ በጣም ተደሰትን ቤት ሄደን ለነዓሊ እና ኢምራን ነግረናቸው ቤት ውስጥ ከቆንጆ እራት ጋር የደስታችንኝ ቀን አከበርን።
ጊዜያቶች እየሄዱ ወራቶች እየተተኩ መጡ የእኔም መውለጃ እየተቃረበ መጣ። ፊርዲ ግን ልክ አደለችም ከቀን ወደቀን ብዙ የእመም አይነቶችን ማስተናገድ ጀመረች ሆስፒታል ብንሄድም አንዴ ጨጓራ አንዴ ኩላሊት እያሉ የመድኃኒት መዓት ማቃም ጀመሩ።ከጊዜ ወደጊዜ ግን የፊርዲ የሕመም ስሜቶች እየጨመሩ የአልጋ ቁራኛ አደረጋት።ፊርዲ በኃይለኛው ያሥላታል፣አተነፋፈሷ እየተለየ ፣ ሰውነቷ እያበጠ ፣የምግብ ፍላጎቷ እየጠፋ ፣በየጊዜው እያቅለሸለሻት ፣የልብ ምቷ በከፍተኛ እየጨመረ ደረቷ ላይ በጣም እያመማት እና በነገሮች ግራ መጋባት ወይም የተሳሳተ ነገሮችን እያሰበች መጣች ፡፡ ሁላችንም ግራ ተጋባን እኔ ኢምራንና ዓሊ ቤታችንን ጥለን ከእናቷ ጋር ፊርዲን ማስታመም ቀጠልን።ዓሊ በወጣበት ከጓደኞቹ አንድ ታዋቂ እና ጎበዝ ዶ/ር እንዳለ ሰምቶ በዛው ሆስፒታሉ ሄዶ አናግሯቸው ባስቸኳይ እንዲያመጣት ነግረውት ወደ ቤት መጥቶ የፊርዶስን እናት ቤት እንዲቀመጡ አሳምነናቸው ለሦስት ይዘናት ሄድን።ወደውስጥ አስገብተው የመጀመሪያ እርዳ ሰጥተዋት በዛውም መረመሯት ዶ/ሩ የፊርዲ ውጤት ያስደነገጠው ይመስላል ።ሦስታችንንም ቢሮው አስጠራን ፊቱ ተለዋውጧል እና የፊርዶስ ምኗ እንደሆንን ካጣራ በኋላ እኔ ነብሰጡር ስለሆንኩኝ ውጪ እንድቆይ ቢነግሩኝም እምቢ አልኳቸው...........ይቀጥላል
(በኹሉድ ኑሪ)
እኔ እና ፊርዲ እምቢ ብንልም ከረጅም ውትወታቸው በኋላ ተስማማን የምንሄድበት ቦታም ከኢትዮጵያ ቆላማ አካባቢዎች አንዷ ወደሆነችው በስተምሥራቅ ወደምትገኘው ወደ ውቢቷ የፍቅር ሀገር ሀረር እንዲሆን ወስነን መንገድ ጀመርን ከረጅም ሰዓት ጉዞ በኋላ ወደ የብሄር ብሄረሰቦች መገኛ የዐማራ ፣ የኦሮሞ ፣ የሐረሪ ፣ የጉራጌና የሶማሌ እና የበርካታ ጎሳዎች ቤታችን ብለው ወደሚጠሯት በሕብረ ቀለም ወዳሸበረቀችው ውቢቷ ከተማ በሰላም ደረስን።ኢምራን ሀረር በደምብ አድርጎ ያውቃት ስለነበር ሁሉንም ቦታ ያውቅ ነበር።እዛ እንደደረስን በ ረውዳ ዋበር በሚባል ባህላዊው የሐረሪ እንግዳ ማረፊያ አረፍን በሀረሪ ለአራት በቆየንባቸው አራት ቀናቶች የሀረርን ሱስ የሚያሲዝ ቡና እየጠጣን፣የተለያዩ ሃላዋዎችን እያጣጣምን፣በሐረር የጎዳናዎች ላይ በምናያቸው ምርጥ ምርጥ ነገሮችን በ ፎቶግራፍ አንስተን ለታሪክ እያስቀመጥን፣ በአሮጌዋ ከተማ መሃል ላይ በሚገኝ ቆንጆ የህንድ ነጋዴ ቤት ውስጥ የሚገኘውን አርተር ሪምቡድ የሚባለውን ሙዚየም፣የራስ ተፈሪ ቤት ሸሪፍ ተብሎ የሚጠራው ኃይለ ሥላሴ (ራስ ተፈሪ) የጫጉላ ሽርሽራቸው ያደረጉበትን ሀረር ከተማ ሙዚየም፣ግድግዳው በቀስተ ዳመና ቀለም የጌጠውን ሐረር ጁጎልን፣በባቢሌ የሚገኘውን የሶማሊያዎች የግመል መሸጫንና በተለያዩ ስሞች የሚጠሩ የሃረር ገበያዎችን እስኪበቃን ጎበኘናቸው በስተመጨረሻም የሐረር የዱር ጅቦችን መግበን ምርጥ አይረሴ ጊዝያቶችን አሳልፈን ወደቤታችን መጣን።
ፊርዲ በጣም ደስተኛ ሆናለች እሷ ብቻ ሳትሆን ሁላችንም ነን ደስተኞች የሆነዉ አንድ ቀን እሁድ ጠዋት ላይ እኔ እና ዓሊ ቁርስ እየበላን የቤታችን በር ተንኳኳ በሩን ለመክፈት እኔ ነበር የሄድኩት ፊርዲ እና ኢምራን ነበሩ "እንዴ አሰላሙ አሌይኩም ወራኽመቱላሂ ሰዎች በሰላም ነው?" አልኳቸው
"እእ ወአለይኩም ሰለም ወራኽመቱላህ"አሉኝ በአንድ ላይ ፊርዲም"ምንድ ነው ቤታችን በፈለግነው ሰዓት መምጣት አንችልም እንዴ" አለችኝ እና ሁለታችንን ጥላን ወደውስጥ ገባች እኔም ተከትያት ልገባ ስል ኢምራን "ሰቡሪ አንዴ ላናግርሽ?" ብሎ አንገቱን በእፍረት አጎነበሰ ግራ እየገባኝ ዞርኩኝ እና"ወዬ ኢምሩ ምነው ችግር አለ እንዴ?"አልኩት"ኧረ ምንም የለም አንዴ ብቻሽን ማወራሽ ጉዳይ ነበረኝ እእ ይኸውልሽ ሰብሪኔ እእ ምን ነበር ሁፍፍ" ሲል አሳቀኝ"እንዴ ኢምሩ ምንድነው እስኪ ተረጋግተክ ንገረኝ"አልኩት "እሺ ምን መሰለሽ ሰቡሪ እእ እኔ አንቺን ማግባት እፈልጋለሁ ማለት አፈቅርሻለሁ እእ እና ማለት አለ አደል በስርዓቱ ዓሊን ጠይቄ አንቺን ሃላሌ ማድረግ እፈልጋለሁ ማለት እሱ ከማወቁ በፊት ፍቃደኝነትሽን ልወቀው ብዬ ነው"አለኝ አላውቅም ድንጋጤ ይሁን ደስታ ለረጅም ሰዓት ደንዝዤ ቀረው "ማለት ተንበርክኬ ምናምን መጠየቅ እችል ነበር ግን ያው በሸሪዓው መንገድ በስርዓቱ ልጠይቅ ብዬ ነው ማለት መብትሽ ነው ምንም ብትወስኚ እኔ አላዝንብሽም" አለኝ እኔም ከፈዘዝኩበት ብንን አልኩና በደስታ እንደምስማማ ነገርኩት በጣም ደስተኛ ሆነ ግን ከዛ በፊት ለጋብቻው እኔ ወንድሜን ማማከር እንዳለብኝ ነገርኩት በጣም ደስ ብሎኛል ነገር ግን ከዓሊ በፊት ማግባቴ እና ብቻውን ጥዬው ልወጣ እንደሆነ ሳስብ ውስጤ ተረበሸ።ሁለታችንም ተከታትለን ገባን ዓሊ ኢምራንን ተነስቶ ሰላም ብሎት ቁጭ አለ።ፊርዲ ፊት ፊታችንን መልስ ፍለጋ ታያለች ወድያሁኑ እሷ እንደሰማች ገባኝ ኢምራን ጠቀሳትና ፈገግ አለ እኔንም ስታየኝ ጭንቅላቴን በአወንታ ስነቀንቀው መልሱ ምን እንደሆነ አወቀች በጣም ደስ አላት በቃ ቡና ላፍላ እኔ ብላ ፍንጥር ብላ ተነሳች ዓሊ"እንዴ ይቺ ልጅ ዛሬ ምንሆና ነው ምትቁነጠነጠው እናንተ እስክትመጡ እኮ ስንቴ ቁጭ ብድግ እንደሰራችብኝ" ብሎ በግርምት ሲያያት እኔ እና ኢምራን ተያይተን ሳቅን የዛን ቀንን ስንጫወት አምሽተን ፊርዲ እና ኢምሩ ወደቤታቸው ሄዱ።ዓሊ ሊተኛ ሊገባ ሲል ማናግረው ነገር እንዳለ ነገርኩት ሊሰማኝ ቁጭ ሲል እየፈራው እየተንተባተብኩኝ እኔ እና ኢምራን ያወራነውን ነገርኩት እሱም በጣም ደስተኛ እንደሆነ ነገረኝ ነገር ግን "ከእናትና አባትሽ ማስታወሻ ከሆነው ቤት ወጥተሽ የኪራይ እንድትኖሪ ስለማልፈልግ ትልቁን መኝታ ቤት እለቅላቹአለው ከእዛ እኔ አንቺ ክፍል እተኛለሁ"አለኝ በአንዴ ሸክሜ ሲቀል ታየኝ ተነስቼ አቀፍኩት እሱም "እህቴ ለካ አድገሽልኛል"ብሎ አቀፈኝ ለኢምራን ዓሊ መስማማቱን እና ያቀረበውን ሃሳብ ነገርኩት መጀመሪያ ላይ ትንሽ ቢያንገራግርም በመጨረሻም ተስማማ።
በስርዓቱ ሽማግሌ ልኮ እኔን እንዲሰጠው ጠየቀ ዓሊም ከ ሁለተኛ ቀጠሮ በኋላ እሺታውን ገለፆ የሰርጉን ቀን ቆረጡ።ሰርጌ 1 ሳምንት ሲቀረው ነጅዋ ከልጆቿ እና ከባለቤቷ ጋር መጣች ደስታዬ እጥፍ ድርብ ሆነ ስለ ፊርዲ እና ኢምራንን ሁሉንም ነገር አጫውታት ስለነበር አዲስ አሎኑባትም።ከሳምንት በኋላ ሰርጉ ተደግሶ ኢምራንን የግሌ አደረግኩት አልሃምዱሊላህ ሁሉ ሃሳቤ ተሳካልኝ ነገር ግን የፊርዲ እና የዓሊ ነገር ያሳስበኝ ነበር ሁለቱን ብድራቸው ጭንቀቴ ይቀልልኝ ነበር።ጊዜ ሄደ ነጅዋም የእረፍት ቀኗን ጨርሳ የልጆቿ ትምህርት ሊጀመር ስለነበር ወደ ሀገሯ ተመለሰች።ከወራቶች በኋላ ፊርዲ የራሷን የልብስ መሸጫ ሱቅ ከፍታ አብረን እዛው መዋል ጀመርን በትርፍ ሰዓታችን ደግሞ ልጇቹን ቁርአን ማስቀራታችንን ቀጠልን አንድቀን በጣም አሞኝ ከፊርዲ ጋር ሐኪም ቤት ስንሄድ የ2ወር ነብሰጡር መሆኔን ነገሩኝ እኔ እና ፊርዶስ በጣም ተደሰትን ቤት ሄደን ለነዓሊ እና ኢምራን ነግረናቸው ቤት ውስጥ ከቆንጆ እራት ጋር የደስታችንኝ ቀን አከበርን።
ጊዜያቶች እየሄዱ ወራቶች እየተተኩ መጡ የእኔም መውለጃ እየተቃረበ መጣ። ፊርዲ ግን ልክ አደለችም ከቀን ወደቀን ብዙ የእመም አይነቶችን ማስተናገድ ጀመረች ሆስፒታል ብንሄድም አንዴ ጨጓራ አንዴ ኩላሊት እያሉ የመድኃኒት መዓት ማቃም ጀመሩ።ከጊዜ ወደጊዜ ግን የፊርዲ የሕመም ስሜቶች እየጨመሩ የአልጋ ቁራኛ አደረጋት።ፊርዲ በኃይለኛው ያሥላታል፣አተነፋፈሷ እየተለየ ፣ ሰውነቷ እያበጠ ፣የምግብ ፍላጎቷ እየጠፋ ፣በየጊዜው እያቅለሸለሻት ፣የልብ ምቷ በከፍተኛ እየጨመረ ደረቷ ላይ በጣም እያመማት እና በነገሮች ግራ መጋባት ወይም የተሳሳተ ነገሮችን እያሰበች መጣች ፡፡ ሁላችንም ግራ ተጋባን እኔ ኢምራንና ዓሊ ቤታችንን ጥለን ከእናቷ ጋር ፊርዲን ማስታመም ቀጠልን።ዓሊ በወጣበት ከጓደኞቹ አንድ ታዋቂ እና ጎበዝ ዶ/ር እንዳለ ሰምቶ በዛው ሆስፒታሉ ሄዶ አናግሯቸው ባስቸኳይ እንዲያመጣት ነግረውት ወደ ቤት መጥቶ የፊርዶስን እናት ቤት እንዲቀመጡ አሳምነናቸው ለሦስት ይዘናት ሄድን።ወደውስጥ አስገብተው የመጀመሪያ እርዳ ሰጥተዋት በዛውም መረመሯት ዶ/ሩ የፊርዲ ውጤት ያስደነገጠው ይመስላል ።ሦስታችንንም ቢሮው አስጠራን ፊቱ ተለዋውጧል እና የፊርዶስ ምኗ እንደሆንን ካጣራ በኋላ እኔ ነብሰጡር ስለሆንኩኝ ውጪ እንድቆይ ቢነግሩኝም እምቢ አልኳቸው...........ይቀጥላል