TIKVAH-ETHIOPIA dan repost
" ወቅታዊ የሀገሪቱ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጠንካራ አመራር እና ውጤታማ የሰብአዊ መብቶች ሥራ የሚጠይቅ መሆኑን እያስታወስኩ መልካም የሥራ ዘመን እመኛለሁ " - ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ አቶ ብርሃኑ አዴሎን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር አድርጎ ሾሟል።
ኢሰመኮ ፥ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የተሾሙት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ያገለገሉ ?መሆኑን ከእነዚህም መካከል ፦
- የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር፣
- የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ ሚኒስትር
- የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እንደነበሩ አስታውሷል።
ተቋሙን በተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነርነት ሲመሩ የነበሩት ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ፥ ወቅታዊ የሀገሪቱ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጠንካራ አመራር እና ውጤታማ የሰብአዊ መብቶች ሥራ የሚጠይቅ መሆኑን አስታውሳዋል።
የኢሰመኮን ኮሚሽነሮች እና ባልደረባዎች በመወከል ለዋና ኮሚሽነር አቶ ብርሃኑ አዴሎ ከወዲሁ “ መልካም የሥራ ዘመን እመኝላቸዋለሁ ” ብለዋል።
@tikvahethiopia
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ አቶ ብርሃኑ አዴሎን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር አድርጎ ሾሟል።
ኢሰመኮ ፥ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የተሾሙት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ያገለገሉ ?መሆኑን ከእነዚህም መካከል ፦
- የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር፣
- የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ ሚኒስትር
- የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እንደነበሩ አስታውሷል።
ተቋሙን በተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነርነት ሲመሩ የነበሩት ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ፥ ወቅታዊ የሀገሪቱ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጠንካራ አመራር እና ውጤታማ የሰብአዊ መብቶች ሥራ የሚጠይቅ መሆኑን አስታውሳዋል።
የኢሰመኮን ኮሚሽነሮች እና ባልደረባዎች በመወከል ለዋና ኮሚሽነር አቶ ብርሃኑ አዴሎ ከወዲሁ “ መልካም የሥራ ዘመን እመኝላቸዋለሁ ” ብለዋል።
@tikvahethiopia