TIKVAH-ETHIOPIA dan repost
" ምርጫ ማሸነፌ እንደወንጀል ታይቶ 1 ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ያለአግባብ ታስሪያሁ " - አቶ አማንያስ ጉሹና
ከሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤዉን አካሂዶ ነበር።
በዚህም ጉባኤ ላይ የኢዜማው ተመራጭ ጉባኤ እንዳይሳተፉ መደረጋቸውን ገልጸዋል።
በክልሉ የዘይሴ ብሔረሰብ ተመራጭ የሆኑት አቶ አማንያስ ጉሹና " ያለአግባብ 4 ወራት ከታሰርኩ በኋላ ያለመከሰስ መብቴ ተነስቶ ለተጨማሪ 7 ወራት በእስር ላይ እንዲቆይና በምክር ቤት ጉባኤ እንዳልሳተፍና ከመንግስት ስራም እንዲሰናበት ተደርጌያለሁ " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ አማንያስ ፤ " ብሔረሰቡ ያለዉን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የመዋቅር ጥያቄ በተለያዩ ጊዜያት ሲጠይቅ የቆዬ ቢሆንም ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘቱ በ6ኛ ሀገራዊ ምርጫ የኢዜማ ፓርቲን በመምረጡ ከምርጫዉ ማግስት ጀምሮ በፓርቲው በአባላትና አመራሮች ላይ የእስርና የማሳደድ ተግባር በይፋ ማካሄድ ተጀምሯል " ብለዋል።
" በአሁኑ ሰዓት ከ2 መቶ በላይ የፓርቲዉ አባላትና አመራሮች በጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤት እየተመላለስን ነዉ " ሲሉ አስረድተዋል።
" ተወዳድረን ምርጫ ማሸነፋችን ሃጥያት ባልሆነበት በገዢዉ ፓርቲ አመራሮች በግልም ሆነ በብሔረሰቡ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እየደረሰብን ነዉ " የሚሉት አቶ አማንያስ " ለአብነትም የደቡብ ክልል ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደዉ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የዜይሴ ብሔረሰብ ያለተወከለበት እና ከሌሎች ብሔሮች ጋር በክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሌሎች ተሳታፊዎች ጋር ያልተሳተፈበት ጉባኤ ነዉ " ሲሉ ወቅሰዋል።
" በዚሁ የፖለቲካ ተፅእኖ ምክንያት ሀገሬን ለ17 ዓመታት ካገለገልኩበት የመምህርነት ሙያ እንድሰናበት ተደርጌያለሁ " ያሉት አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ ደጋግሜ ብጠይቅም 'ያለመከስ መብትህ ሳይነሳ መመለስ አትችልም' የሚል ምላሽ ከትምህርት አስተዳደር መዋቅሮች ተሰጥቶኛል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢዜማ ፓርቲ የሕግና አባላት ጉዳይ ደህንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስዩም መንገሻን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገራቸዉ ሲሆን " በዘይሴ ብሔረሰብ የሕዝብ ተመራጭ አቶ አማኒያስ ጉሹና ላይ የተፈፀመዉ ጉዳይ ኢ-ሕገመንግስታዊ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
በወቅቱ ያለመከሰስ መብታቸዉ ሳይነሳ ታስረዉ መቆየታቸዉንና በአካባቢዉ ያለዉን የሰብአዊ መብት ረገጣና የፖለቲካ ተፅእኖ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በፅሑፍ ማሳወቃቸዉንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደአከባቢዉ ማቅናቱንና የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ አንስተዋል።
" ከስራ የተሰናበቱበትና ወደ ስራ እንዳይመለሱ የሚደረግበት አግባብ ከፍተኛ የፖለቲካ ተፅእኖ ያለበት ነዉ " ያሉት አቶ ስዩም ፤ የኢዜማ ፓርቲ በአከባቢው ያለዉን የፖለቲካ ጫናና ተያያዥ ጉዳዮችን ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በጽሑፍ አቅርቦ ባለድርሻ አካላት የተካተቱበት ግብረሃይል ተዋቅሮ ቦታዉ ድረስ በመሄድ በሰጠዉ አቅጣጫ መሠረት አቶ አማንያስ በዋስ እንዲፈቱ መደረጉን ተናግረዋል።
አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ በተደጋጋሚ ብጠይቅም የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤትና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ' ያለመከሰስ መብትህ እስካልተነሳ ድረስ መመለስ አንችልም ' ተብያለሁ " በሚል ላነሱት ቅሬታ ከከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ጽ/ቤትና ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤዉን አካሂዶ ነበር።
በዚህም ጉባኤ ላይ የኢዜማው ተመራጭ ጉባኤ እንዳይሳተፉ መደረጋቸውን ገልጸዋል።
በክልሉ የዘይሴ ብሔረሰብ ተመራጭ የሆኑት አቶ አማንያስ ጉሹና " ያለአግባብ 4 ወራት ከታሰርኩ በኋላ ያለመከሰስ መብቴ ተነስቶ ለተጨማሪ 7 ወራት በእስር ላይ እንዲቆይና በምክር ቤት ጉባኤ እንዳልሳተፍና ከመንግስት ስራም እንዲሰናበት ተደርጌያለሁ " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አቶ አማንያስ ፤ " ብሔረሰቡ ያለዉን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የመዋቅር ጥያቄ በተለያዩ ጊዜያት ሲጠይቅ የቆዬ ቢሆንም ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘቱ በ6ኛ ሀገራዊ ምርጫ የኢዜማ ፓርቲን በመምረጡ ከምርጫዉ ማግስት ጀምሮ በፓርቲው በአባላትና አመራሮች ላይ የእስርና የማሳደድ ተግባር በይፋ ማካሄድ ተጀምሯል " ብለዋል።
" በአሁኑ ሰዓት ከ2 መቶ በላይ የፓርቲዉ አባላትና አመራሮች በጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤት እየተመላለስን ነዉ " ሲሉ አስረድተዋል።
" ተወዳድረን ምርጫ ማሸነፋችን ሃጥያት ባልሆነበት በገዢዉ ፓርቲ አመራሮች በግልም ሆነ በብሔረሰቡ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እየደረሰብን ነዉ " የሚሉት አቶ አማንያስ " ለአብነትም የደቡብ ክልል ምክር ቤት ሰሞኑን ባካሄደዉ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የዜይሴ ብሔረሰብ ያለተወከለበት እና ከሌሎች ብሔሮች ጋር በክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሌሎች ተሳታፊዎች ጋር ያልተሳተፈበት ጉባኤ ነዉ " ሲሉ ወቅሰዋል።
" በዚሁ የፖለቲካ ተፅእኖ ምክንያት ሀገሬን ለ17 ዓመታት ካገለገልኩበት የመምህርነት ሙያ እንድሰናበት ተደርጌያለሁ " ያሉት አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ ደጋግሜ ብጠይቅም 'ያለመከስ መብትህ ሳይነሳ መመለስ አትችልም' የሚል ምላሽ ከትምህርት አስተዳደር መዋቅሮች ተሰጥቶኛል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የኢዜማ ፓርቲ የሕግና አባላት ጉዳይ ደህንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ስዩም መንገሻን በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገራቸዉ ሲሆን " በዘይሴ ብሔረሰብ የሕዝብ ተመራጭ አቶ አማኒያስ ጉሹና ላይ የተፈፀመዉ ጉዳይ ኢ-ሕገመንግስታዊ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
በወቅቱ ያለመከሰስ መብታቸዉ ሳይነሳ ታስረዉ መቆየታቸዉንና በአካባቢዉ ያለዉን የሰብአዊ መብት ረገጣና የፖለቲካ ተፅእኖ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በፅሑፍ ማሳወቃቸዉንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት ግብረ ሃይል ተቋቁሞ ወደአከባቢዉ ማቅናቱንና የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ አንስተዋል።
" ከስራ የተሰናበቱበትና ወደ ስራ እንዳይመለሱ የሚደረግበት አግባብ ከፍተኛ የፖለቲካ ተፅእኖ ያለበት ነዉ " ያሉት አቶ ስዩም ፤ የኢዜማ ፓርቲ በአከባቢው ያለዉን የፖለቲካ ጫናና ተያያዥ ጉዳዮችን ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በጽሑፍ አቅርቦ ባለድርሻ አካላት የተካተቱበት ግብረሃይል ተዋቅሮ ቦታዉ ድረስ በመሄድ በሰጠዉ አቅጣጫ መሠረት አቶ አማንያስ በዋስ እንዲፈቱ መደረጉን ተናግረዋል።
አቶ አማንያስ " ወደ ስራ ገበታዬ እንዲመልሱኝ በተደጋጋሚ ብጠይቅም የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤትና የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ' ያለመከሰስ መብትህ እስካልተነሳ ድረስ መመለስ አንችልም ' ተብያለሁ " በሚል ላነሱት ቅሬታ ከከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ጽ/ቤትና ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia