ታምሪን ሚዲያ(Tamrin Media)✍✍✍✍✍


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


Introducing daily news and information all over the world including our country ethiopia
ለፈጣን እና ተዓማኒ መረጃዎች ቻናላችንን ይቀላቀሉ። 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ቻናላችንን በመቀለቀል ወቅታዊ መረጃዎቸችን በፍጥነት ያግኙ👇👇👇
https://t.me/Tamrinmedia
✉️inbox 👉 @tamrin_bot

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


"የፈጠራ ክስ ቀርቦብኛል"- ኤርትራ‼️
ተመድ እና የአውሮፓ ህብረት የኤርትራ ወታደሮች በኢትዮጵያ ድንበር ገብተው ጥቃት እየፈፀሙ መሆናቸውን ተከትሎ ያቀረበባትን ክስ ኤርትራ አስተባበለች።

የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስቴር የማነ ገ/መስቀል በx ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ አውሮፓ ህብረት እና ተመድ እንደዚህ ቀደሙ ሁሉ ተመሳሳይ እና የፈጠራ ክስ በኤርትራ ላይ መስርቷል ሲሉ ገልፀዋል።

በጄኔቫው ስብሰባ ላይ ኤርትራ በትግራይ ክልል ወረዳዎች ውስጥ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እየፈፀመች መሆኑ የተገለፀ ሲሆን የኤርትራ ወታደሮች በአስቸኳይ ከትግራይ ክልል ለቀው እንዲወጡም ጥሪ አቅርቧል፡፡
ይሁንና ኤርትራ ክሱን የፈጠራ ክስ ነው ስትል አስተባብላለች።
https://t.me/Tamrinmedia
====================


ካናዳ የአሜሪካ 51ኛዋ ግዛት እንድትሆን የቀረበዉን ሀሳብ በመቃወም ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ነፃነታችንን ማስጠበቅ ቀዳሚ ስራችን ነው አሉ

የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ከንጉሥ ቻርልስ ጋር ካደረጉት ውይይት አስቀድመዉ እንደተናገሩት ቅድሚያ የሚሰጧቸው ጉዳዮች የሀገራቸውን ሉዓላዊነት ማስጠበቅ ነው ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ካናዳ 51ኛው የአሜሪካ ግዛት እንድትሆን በቅርቡ ሀሳብ ካቀረቡ በኋላ ነዉ፡፡

ትሩዶ የካናዳ ርዕሰ መስተዳድር ከሆኑት ቻርለስ ጋር ከመገናኘታቸዉ በፊት ለዜጎች “ለሉዓላዊነታችን እና ለነፃነታችን ከመቆም” የበለጠ ጠቃሚ ነገር የለም ብለዋል።ትሩዶ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት "ከግርማዊነታቸው ጋር ተቀምጦ ለመወያየት በጉጉት እጠብቃለሁ፣ እንደተለመደው ለካናዳ እና ለካናዳውያን አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ እንወያያለን፣ ለካናዳውያን ለሉዓላዊነታችን እና እንደ ሀገር ለነፃነታችን ከመቆም የበለጠ ጠቃሚ ነገር እንደሌለ እናገራለሁ” ብለዋል።

ተሰናባቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ትሩዶ ባለፈው ወር እንደተናገሩት ትራምፕ ካናዳን ስለመጠቅለል የተናገሩት ንግግር “እውነተኛ ነገር ነው” እናም ከሀገሪቱ የበለፀገ የተፈጥሮ ሀብት ጋር የተያያዘ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።ትራምፕ ካናዳ 51ኛው የአሜሪካ ግዛት ለመሆን ከተስማማች የተሻለች ትሆናለች ሲሉ ደጋግመው ጠቁመዋል።

ትሩዶ ከዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር ትራም ስላደረጉት ውይይት ተጠይቀዉ ከዘለንስኪ ጎን እንደሚቆሙ ተናግረዋል፡፡
https://t.me/Tamrinmedia


የግብፅ ዉጪ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርትራ ይገኛሉ

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትናንት ማምሻውን በግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር በድር አብደላቲ የተመራው የግብፅ ልኡካን ቡድን ተቀብለዉ አነጋግረዋል። 

ሁለቱ ሀገራት ሰፊ ውይይቶችን አድርገዋል ያሉት የኤርትራ የመረጃ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል ሲሆኑ በሁለቱ ሀገራት እንዲሁም በአህጉራዊ - የአፍሪካ ቀንድ እና ቀይ ባህር - የጋራ ጠቀሜታ ባላቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ምክክር አድርገዋል ብለዋል።

ጥልቀት ከተሰጣቸዉ ጉዳዮች ዉስጥም በሶማሊያ የሀገር ግንባታ ላይ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባህር አካባቢዎች የሰላም እና የደህንነት ፈተናዎች በኤርትራ እና ግብፅ ባለስልጣናት ሰፊ ዉይይት መደረጉን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል።

የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር በድር አብደላቲ ለኤርትራ ዜና አገልግሎት በሰጡት አጭር መግለጫ እንደገለፁት በየወቅቱ የሚደረጉ ምክክሮች በቀጠናዊ ጸጥታና መረጋጋት ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋሞችን ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኤርትራ እና ግብፅ መሪዎች መካከል ከአስመራ ካይሮ የሚደረጉ ጉብኝቶች በርከት ብለዋል። የግብፅ ፕሬዚዳንት አብደልፋታህ አልሲሲን ጨምሮ በርካታ የግብፅ ባለስልጣናት ወደ ኤርትራ ጉብኝት ሲያደርጉም ተስተዉሏል።

ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር በባህር በር ስምምነት ጉዳይ ዉዝግብ ዉስጥ ከገባችበት ጊዜ አንስቶ የግብፅ የምስራቅ አፍሪካ እንቅስቃሴ እየተስተዋለ መጥቷል።
https://t.me/Tamrinmedia




ማስጠንቀቂያ :- 1ሚሊየን ብር ሊቀጡ ይችላሉ

አለማወቅ ከቅጣት አያድንም

👉 በባህሪው አደገኛ የሆነ ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ በወንዝ ዳርቻ ያሰወገደ ድርጅት አንድ ሚሊዮን ብር ይቀጣል፣

👉 ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ ወንዝ ላይ የጣለ ግለሰብ 500 ሺህ ብር ይቀጣል

👉 ፍቃድ የወሰዱም ሆነ ሳይወስዱ ፍሳሽን ቀጥታ በወንዞች ዳርቻ ሲያስወግዱ ቢገኙ 100 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

👉 በወንዝ ዳርቻና አካባቢ መጸዳዳት ሁለት ሺህ፤

👉 የፈሳሽ ማጣሪያ ሳይኖር በወንዝ ዳርቻና አካባቢ ተሽከርካሪ ማጠብ 400ሺህ ብር፤

👉 እንስሳትን ማሰማራት፣ ማስገባት ከተፈቀደው ውጪ ተሽከርካሪ ማሽከርከር 30 ሺህ ብር

👉 ለመዝናኛ፣ ለመናፈሻና ለፖርክ ከተፈቀደ ውጪ ግንባታ መገንባት 200 ሺህ ብር፤

👉 ከአምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ማንኛውም ያልታከመ ቆሻሻ መልቀቅ 300 ሺህ ብር ያስቀጣል፣

👉 ኬሚካል ነክ ቆሻሻዎችን የማከሚያ ዘዴ ሳይጠቀም የለቀቀ ግለሰብ 50 ሺህ፤ ድርጅት 300 ሺህ ብር ይቀጣሉ፣

👉 ማንኛውም በካይ ቆሻሻ ከተፈቀደ የፈሳሽ ማጠራቀሚያ ውጪ ያፈሰስ ግለስብ 50 ሺህ ድረጅት 400 ሺህ ብር፤

👉 የአትክልትና ፍራፍሬ ተረፈ ምርቶችን በወንዝ ዳርቻ ማስወገድ ግለሰብ 20 ሺህ፣ ድርጅት 100 ሺህ፤

👉 ዘይት፣ ጨዋማ ፈሳሽ፣የሞተር ዘይት፣ ነዳጅ ሳሙና ነክ ነገሮችን በወንዝ ዳርቻ ያስወገደ 400 ሺህ ብር ይቀጣል፣

👉 ማንኛውም ያልተጣራ ቆሻሻ ወደ ወንዝ መልቀቅ ግለሰብ 150 ሺህ ድርጀት 300 ሺህ ይቀጣል፣

👉 ፍቃድ ሳይሰጠው ያልታከመ ቆሻሻን ወደ ወንዝ ያስወገደ ግለሰብ 15 ሺህ ብር ድርጅት 40 ሺህ ብር ይቀጣል፣

የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን
https://t.me/Tamrinmedia


መረጃ :-

በሳውዲ ዛሬ ጨረቃ ሰለታየች የመጀመሪያ
ረመዳን ቀን ነገ ቅዳሜ ይጀምራል ተብሏል::
https://t.me/Tamrinmedia


እነ ዮሃንስ ዳንኤል ( ጆን ዳንኤል) የፍር ቤት ውሎ

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ በወንጀል የተከሰሱት እነ ዮሃንስ ዳንኤል ( ጆን ዳንኤል) እንዲከላከሉ ብይን ተሰጠ

) የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ልዩ ልዩ ከባድ ወንጀል ችሎት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ በወንጀል የተከሰሱት እነ ዮሃንስ ዳንኤል እንዲከላከሉ ብይን ሰጠ።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል)፣ አማኑኤል መውጫ፣ ናትናኤል ወንድወሰን፣ ኤልያስ ድሪባ፣ ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ላይ በነሐሴ 16 ቀኔ 2016 ዓ.ም ከምሽቱ በግምት 3፡30 ሰዓት ላይ ከአበባ ከተማ ወደ መቐለ ከተማ ለመጓዝ አውሮፕላኑ ለበረራ ዝግጁ ቢሆንም የአየር ሁኔታ ለበረራ አዳጋች በመሆኑ በረራው ቢደረግ በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ የሚያደርሰውን ከባድ አደጋ ለመከላከል ጉዞው ተሰርዞ መንገደኞች ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ ሲነገራቸው በረራው በግድ መደረግ አለበት፤ አውሮፕላኑ ይከስከስ፤ አንወርድም በማለት ቀሪ ተሳፋሪዎችም እንዳይወርዱ በመክልከል አሳድመዋል በሚል በዝርዝር ጠቅሶ ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በተጨማሪም ዐቃቤ ሕግ 1ኛ ተከሳሽን ጆን ዳንኤል በተባለ ተከሳሽ ላይ በ3ኛ ክስ የኮምፒዩተር ወንጀል ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 958/2008 አንቀጽ 13 ንዑስ ቁጥር 3 ሥር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፍ ቲክቶክ በተባለ ማሀበራዊ ሚዲያ በተንቀሳቃሽ ምስል ቀርጾ በቀጥታ ስርጭት ማስተላለፍ የሚል ክስ አቅርቦበት ነበር።

በዚህ መልኩ ተከሳሾቹ የክስ ዝርዝሩ ከደረሳቸው በኋላ ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ በተሰጠ ትዕዛዝ መሰረት ከማረሚያ ቤት ቀርበው ጉዳያቸውን ተከታትለዋል።

ተከሳሾቹ "የወንጀል ድርጊቱን አልፈጸምንም" በማለት የዕምነት ክህደት ቃላቸውን በመስጠታቸው ዐቃቤ ሕግ ለወንጀሉ መፈጸም ያስረዱልኛል ያላቸውን ምስክሮች ቃል አሰምቷል።

ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ዛሬ በዋለው የችሎት ቀጠሮ ሁሉም ተከሳሾች በ1ኛ ክስ ማለትም በወንጀል ህግ አንቀጽ 504 መሰረት እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ሁለተኛውን ክስ በሚመለከት ፍሬ ነገሩ በአንደኛ ክስ ተጠቃሎ የተገለጸ በመሆኑ ተከሳሾቹን በሁለተኛ ክስ ነጻ በማለት በአንደኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል።

በተጨማሪም ፍርድ ቤቱ ጆን ዳንኤል የተባለው 1ኛ ተከሳሽን በተደራቢነት በቀረበበት በ3ኛ ክስ የኮምፒዩተር ወንጀል ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 958/2008 አንቀጽ 13 ንዑስ ቁጥር 3 ሥር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፍ በሚለው ክስ እንዲከላከል ብይን ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን የመከላከያ ማስረጃ ለመጠባበቅ ለመጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጥሯል።
https://t.me/Tamrinmedia


መንታ ልጆች አረገዘች ፣

ግራድ ፒ አዲሷ ሚስቱ መንታ እንዳረገዘችለት ይፋ አደረገ!
https://t.me/Tamrinmedia


ካሪም ቤንዜማ ለመቄዶኒያ ድጋፍን ሊያደርግ ነው !
📌 የቤንዜማ የግል አውሮፕላን ረዳት አብራሪው 5ሺህ ዶላር ለግሷል።

በስፔን ላሊጋ የነገሰው እና በሪያል ማድሪድ መለያ የደመቀው በዋንጫ ያቆጠቆጠ ታሪክን ያፃፈው በአሁኑ ሰአትም ለሳውዲው ክለብ አሊትሀድ እየተጫወተ የሚገኘው ፈረንሳዊው አጥቂ ካሪም ቤንዜማ ለመቄዶንያ የአረጋውያን እና አዕምሮ ህሙማን ማዕከል ልገሳን ሊያደርግ ነው።

የተጫዋቹ የግል አውሮፕላን ረዳት አብራሪ የሆነው ኢትዮጵያዊው አቤል ወይም ጆንሰን ግን በግሉ ለመቄዶንያ የ5 ሺህ ዶላር ድጋፍን ዛሬ አድርጓል።
https://t.me/Tamrinmedia


የመሬት መንቀጥቀጥ‼️
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 5:29 በአዲስ አበባና በሌሎች የተለያዩ አከባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።
የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 4.75 መመዝገቡን ዘገባዎች ያመላክታሉ።
https://t.me/Tamrinmedia


የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ ለመኖር የሚያስችል ፈቃድ በ5 ሚሊየን ዶላር ለሽያጭ አቀረቡ።

ከዚህ ቀደም ከሚታወቀው አረንጓዴ ካርድ (የመኖሪያ ፈቃድ) ጋር የሚስተካከለውና 5 ሚሊየን ዶላር የመክፈል አቅም ላላቸው የሚቀርበው ወርቃማው ካርድ በቀጣዮቹ ቀናት ለገዥዎች ክፍት ይሆናል።
ወርቃማው ካርድ በሂደት የአሜሪካ ዜግነትንም ያስገኛል ተብሏል።
የአረንጓዴ ካርድ ዕጣ ፈንታን በተመለከተ ፕሬዝዳንቱ አስተያየት አልሰጡም። ስለጉዳዩ የሚያውቁ ግን ፕሬዝዳንቱ አረንጓዴ ካርድን የመገደብ ፍላጎት አላቸው። አዲሱ ወርቃማ ካርድ ተሽጦ የሚገኘው ገንዘብ የአሜሪካን የበጀት ጉድለት ለሟሟላት ይውላል።
https://t.me/Tamrinmedia


የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች ከነገ ጀምሮ የብልፅግና ፓርቲ ማስታወቂያን በግዴታ እንዲያሳዩ ሊደረጉ መሆኑ ታወቀ

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የዲጂታል ስክሪን ማስታወቂያ ባለቤቶች እና ህንፃዎቻቸው ላይ የማስታወቂያ ስክሪን የገጠሙ ባለሀብቶች ከነገ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ መልእክት የሆኑ ምስሎችን እና ጽሁፎችን በአስገዳጅነት እንዲያሰራጩ ጥብቅ ትዕዛዝ እንደተላለፈላቸው ታውቋል።

በራሳቸው ወጪ አውጥተው የሰሩትን የዲጂታል ስክሪን ለፖለቲካ ፓርቲ መልዕክት ማስተላለፊያ መደረጉ በህዝብ ዘንድ ለአንድ ወገን ያደሉ ወይም የፓርቲ አባል እንደሆኑ እንዳይወሰድባቸው የሰጉት ግለሰቦቹ አማራጭ እንዳጡ እና አጣብቂኝ ውስጥ እንደገቡ ተናግረዋል።

የብልጽግና ሹሞች ቁጣ በተቀላቀለበት መልዕክት በአስገዳጅነት ማስታወቂያውን ከነገ ጀምሮ ለማሰራጨት እንዳስገደዷቸው ጨምረው ተናግረዋል።

"ከሳምንት በፊት ለአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መሪዎች ሲመጡ 'እንኳን ደህና መጣችሁ' የሚልና ስለ አፍሪካ ህብረት ስብሰባ ተመሳሳይ ትዕዛዝ ተላልፎ  ያስተላለፍነው የፖለቲካ ይዘት የሌለው በመሆኑ ነበር" የሚሉት የማስታወቂያ ድርጅቶቹ "አሁን የታዘዝነው የፖለቲካ ፓርቲ  መልእክት ገበያው በተዳከመበት መሀል ከህዝቡ ጋር እንዳያቃቅረን ስጋት አለን" ብለዋል።

በሌላ በኩል በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብሰባ ወቅት በርካታ የመኪና ኪራይ ስራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች ተሽከርካሪዎቻቸውን በነፃ ለስብሰባው አገልግሎት እንዲሰጡ ተገደው እንደነበር ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።

"ቢዝነስ በተዳከመበት በዚህ ወቅትም ይሁን ድሮ በአመት አንዴ ጥሩ ስራ የምንሰራው እንደ አፍሪካ ህብረት ያሉ ስብሰባዎች ሲመጡ ነበር" የሚሉት የመኪና አከራዮቹ አሁን ግን እሱንም በግዴታ እንደተነጠቁ እና መኪናዎቻቸው የተመለሱላቸው ስብሰባው ካለቀ በኋላ መሆኑን አስረድተዋል።

via# መሠረትሚዲያ !
https://t.me/Tamrinmedia


ሶማሊላንድ‼️
ከሳምንት በፊት የሶማሊያ ራስ ገዝ የሆነችዉ ፑንትላንድ በርካታ ኢትዮጵያዊያንን በቁጥጥር ስር አውላ ወደ ሀገራቸው መላኳን ማስታወቋ ይታወሳል‼️
ዛሬ እየወጡ ያሉ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት ደግሞ የሶማሊላንድ መንግሥት ፖሊስ በሃገሪቱ በተለይም በዋና ከተማዋ ሀርጌሳ የሚኖሩ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውን ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የገበያ ማዕከላትን ጨምሮ ከተለያዩ ሥፍራዎች በቂጥጥር ስር በማዋል ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ መጠነሰፊ ዘመቻ መክፈቱ ታውቋል።
https://t.me/Tamrinmedia


«ፈተናው እየበዛብኝ ነው። ሁላችሁም በፆማችሁ እና በፀሎታችሁ አስታውሱኝ» አብዱ ኪያር

“እማዬ አላህ ነፍስሽን በጀነት ያኑራት። አሁንም አልሓምዱሊላህ።” ይህን ያለው ድምጻዊ አብዱ ኪያር ነው

«በቀደም ሊፍት ወድቆብን ከከባድ አደጋ ተረፍኩ። ዛሬ ደግሞ የናቴን ሞት ተረዳሁ። ፈተናው እየበዛብኝ ነው። ሁላችሁም በፆማችሁ እና በፀሎታችሁ አስታውሱኝ።» ብሏል
https://t.me/Tamrinmedia



15 last posts shown.