Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ለባለሃብቱ!
~
ለገቢዎች ባለስልጣን መስሪያ ቤት የምትከፍለውን ግብር እያሰብክ ከዘካ እንዳትዘናጋ። ዘካ ለደካሞች የሚሰጥ ሐቅ እንጂ ለሹማምንት የሚሰጥ ግብር ወይም ጉቦ አይደለም። አኺል ከሪም! ገንዘቡን የሰጠህ አላህ ነው። እንጂ ካንተ የበለጠ የሚለፉ ድሃዎች በዙሪያህ አሉኮ። በእውቀቴ አገኘሁት እንዳትል ካንተ የበለጠ የተማሩ ድሃዎች ሞልተዋልኮ። ጥለኸው ለምትሄደው ገንዘብ ብለህ በራስህ ላይ አትሳሳ። እውነተኛው ያንተ ገንዘብ ማለት ለአኺራህ ያሻገርከው ነው። ዐብዱላህ ብኑ ሺኺር - ረዲየሏሁ ዐንሁ - እንዲህ ይላሉ፦
أتَيْتُ النَّبيَّ صلى الله عليه وسلم، وَهُوَ يَقْرَأُ: {أَلْهَاكُمُ التَّكَاثُرُ} قَالَ: ((يَقُولُ ابْنُ آدَمَ: مَالِي، مالي، وَهَلْ لَكَ يَا ابْنَ آدَمَ مِنْ مَالِكَ إلا مَا أكَلْتَ فَأفْنَيْتَ، أَو لَبِسْتَ فَأَبْلَيْتَ، أَوْ تَصَدَّقْتَ فَأَمْضَيْتَ؟)
"ነብያችን ﷺ ዘንድ መጣሁኝ። {በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ} የሚለውን እየቀሩ ነው። ቀጥለው እንዲህ አሉ፦
'የአደም ልጅ 'ገንዘቤ ገንዘቤ!' ይላል። የአደም ልጅ ሆይ! በልተህ ከጨረስከው፣ ለብሰህ ካሳለቅከው፣ ሶደቃ ሰጥተህ አጅሩን ካሻገርከው ውጭ ገንዘብ አለህ'ንዴ?' " [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2958]
እወቅ! የምታወጣው ካጠቃላይ ገንዘብህ 2.5 ከመቶ ብቻ ነው። መቶ ብር ያለው ሰው ሁለት ብር ከሃምሳ ሳንቲም ቢያወጣ ብዙ ነው ወይ? ምስሉ ላይ በጣት የተጠቆመችዋን ተመልከት። ካጠቃላይ ሃብትህ ይቺን ታክል ለዘመዶችህ፣ ለጎረቤቶችህ፣ ለምታውቃቸው ምስኪኖች ብታወጣ ብዙ ነውን? በአኺራ እጥፍ ድርብ ምንዳ እንደሚጠብቅህ የቂን የለህም ወይ?
ደግሞም እወቅ! ወላሂ ሶደቃ ሃብትን አይቀንስም። ይልቁንም ይበልጥ በረካ እንዲኖረው ነው የሚያደርግልህ። አላህ ትእዛዙን ለመፈፀም ያግራልህ።
=
ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
~
ለገቢዎች ባለስልጣን መስሪያ ቤት የምትከፍለውን ግብር እያሰብክ ከዘካ እንዳትዘናጋ። ዘካ ለደካሞች የሚሰጥ ሐቅ እንጂ ለሹማምንት የሚሰጥ ግብር ወይም ጉቦ አይደለም። አኺል ከሪም! ገንዘቡን የሰጠህ አላህ ነው። እንጂ ካንተ የበለጠ የሚለፉ ድሃዎች በዙሪያህ አሉኮ። በእውቀቴ አገኘሁት እንዳትል ካንተ የበለጠ የተማሩ ድሃዎች ሞልተዋልኮ። ጥለኸው ለምትሄደው ገንዘብ ብለህ በራስህ ላይ አትሳሳ። እውነተኛው ያንተ ገንዘብ ማለት ለአኺራህ ያሻገርከው ነው። ዐብዱላህ ብኑ ሺኺር - ረዲየሏሁ ዐንሁ - እንዲህ ይላሉ፦
أتَيْتُ النَّبيَّ صلى الله عليه وسلم، وَهُوَ يَقْرَأُ: {أَلْهَاكُمُ التَّكَاثُرُ} قَالَ: ((يَقُولُ ابْنُ آدَمَ: مَالِي، مالي، وَهَلْ لَكَ يَا ابْنَ آدَمَ مِنْ مَالِكَ إلا مَا أكَلْتَ فَأفْنَيْتَ، أَو لَبِسْتَ فَأَبْلَيْتَ، أَوْ تَصَدَّقْتَ فَأَمْضَيْتَ؟)
"ነብያችን ﷺ ዘንድ መጣሁኝ። {በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ} የሚለውን እየቀሩ ነው። ቀጥለው እንዲህ አሉ፦
'የአደም ልጅ 'ገንዘቤ ገንዘቤ!' ይላል። የአደም ልጅ ሆይ! በልተህ ከጨረስከው፣ ለብሰህ ካሳለቅከው፣ ሶደቃ ሰጥተህ አጅሩን ካሻገርከው ውጭ ገንዘብ አለህ'ንዴ?' " [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2958]
እወቅ! የምታወጣው ካጠቃላይ ገንዘብህ 2.5 ከመቶ ብቻ ነው። መቶ ብር ያለው ሰው ሁለት ብር ከሃምሳ ሳንቲም ቢያወጣ ብዙ ነው ወይ? ምስሉ ላይ በጣት የተጠቆመችዋን ተመልከት። ካጠቃላይ ሃብትህ ይቺን ታክል ለዘመዶችህ፣ ለጎረቤቶችህ፣ ለምታውቃቸው ምስኪኖች ብታወጣ ብዙ ነውን? በአኺራ እጥፍ ድርብ ምንዳ እንደሚጠብቅህ የቂን የለህም ወይ?
ደግሞም እወቅ! ወላሂ ሶደቃ ሃብትን አይቀንስም። ይልቁንም ይበልጥ በረካ እንዲኖረው ነው የሚያደርግልህ። አላህ ትእዛዙን ለመፈፀም ያግራልህ።
=
ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor