ወሎ የመቻቻል ወይስ የግፍ ምድር?
~
"ወሎ ሌት እስላም፣ ቀን ክርስቲያን" ሲባል ሰምተሀል ወንድሜ? ዛሬ ሰው እየሳቀ ያወራዋል። በውስጡ ያዘለው መልእክት ግን የሚያስለቅስ እንጂ የሚያስቅ አይደለም። በተከፈተበት አስገድዶ የማጥመቅ ዘመቻ ሳቢያ ሞት የተጋረጠበት ህይወቱን ለማትረፍ ሲል ቀን ላይ "ክርስቲያን ነኝ" የሚልበትን፤ ሌት ላይ አራ -ጆቹ ከፊቱ ዞር ሲሉለት እለታዊ የእምነቱን ሕግጋት ሲፈፅም የነበረበትን ዘመን ነው የሚያስታውሰው። በዚህ ሳቢያ ነበር "ወሎ ሌት እስላም፣ ቀን ክርስቲያን" የተባለው።
ሌት ላይ በድብቅ ፆም ለመያዝ እሳት ሲያቀጣጥል ታይቶ የተንገላታው ስንቱ ነው?! ትላንት በዚህ አይነት ትንቅንቅ ነበር እምነቱን ያቆየው።
·
የትላንቷ ሙስሊማ ሃይማኖቷን መቀየሯን ያላመኑ ጉልበተኛ አጥማቂዎች ሲያስጨንቋት "ወላሂ ክርስቲያን ነኝ" ስትል ነበር። ሕይወቷን ለማትረፍ "ክርስቲያን ነኝ" ትላለች። ከስጋዋ ጋር የተዋሀደው ኢስላሟ ግን በጎን ሾልኮ እየወጣ ሂወቷን ስጋት ላይ ይጥልባታል። "ወላሂ" ትላለች። አነጋገሯ አስቆህ ከሆነ ሞኝ ነህ። ይሄ የሚያስለቅስ እንጂ የሚያስቅ አይደለም።
·
ይህ ሁሉ ከመፈፀሙ ጋር "ወሎ የመቻቻል ተምሳሌት" እያለ የሚወሸክት አለ። ወሎ የመቻቻል ሃገር ሳይሆን በአንድ ህዝብ ላይ የተፈፀመ መጠነ ሰፊ ሃይማኖት ተኮር ግፍ በገሃድ የሚታይበት ምድር ነው። በዮሀንስ፣ በምንሊክና በራስ ሚካኤል የተባበረ ክንድ እልፍ አእላፍ ሙስሊም በግፍ ተጨፍ ~ `ጭፏል። ከርስቱ ከመሬቱ ብቻም ሳይሆን እትብቱ ከተቀበረበት ሃገር ተፈናቅሎ በየጥሻው ቀርቷል። የአሞራና የጅብ ቀለብ ሆኗል። በረሃብ በቸነፈር እንደ ቅጠል ረግፏል። ጠኔ ባደከማቸው ከሲታ እግሮቹ የወራት መንገዶችን አቆራርጦ ወደማያውቀው ምድር ተሰዷል። እጅግ ብዙው ካለመበትም ሳይደርስ አንድም በሚያሳድደው ጥጋበኛ የኩ ^ f ር ሰራዊት፣ አለያም በረሃብና በወረርሽኝ መንገድ ላይ ቀርቷል።
የተረፈው አይናቸውን በጨው አጥበው "ኢስላም በሰይፍ ነው የተስፋፋው" እያሉ በሚከሱ ሃፍረተ ቢሶች ያለ ምርጫው በሃይል ተጠምቋል። በገዛ እጁ መስጂዱን እያፈረሰ ቤተ ክርስቲያን እንዲገነባ ተደርጓል። የማወራው እዚችው የግፍ ምድር ላይ ስለተፈፀመ ግፍ ነው። ስለ መቻቻል ሰርክ የሚዜምላት ኢትዮጵያ!
·
አስገድዶ የማጥመቅ ዘመቻው ካለፈ በኋላም በሙስሊሙ ላይ የሚፈፀመው ግፍ መልኩን ቀይሮ እንደቀጠለ ነበር። ህዝበ ሙስሊሙ ለገዛ እምነቱ ባይተዋር እንዲሆን፣ የነሱ ባእላት አድማቂ እንዲሆን ተደርጓል። በተፈፀመበት የረጅም ጊዜ ሴራ የተነሳ ጥምቀት እና ገና የሚያከብር፣ ደመራ የሚያቃጥል፣ "አልሐምዱ ሊላሂ ታቦታችን ገባ" እያለ ታቦት የሚሸኝ፣ ፀበል የሚመላለስ፣ ማንነቱ የተደባለቀበት ትውልድ ተፈጥሯል። ይሄ ግን አንዳንድ ቅቤ አንጓቾች እንደሚያስተጋቡት የመቻቻል ውጤት አይደለም። ይልቁንም አስገድዶ ከማጥመቅ የቀጠለው ማንነትን የማደባለቅ ዘመቻ ውጤት ነው።
ይህን ያዩ ሸይኽ ነበሩ እንዲህ ሲሉ የገጠሙት:–
·
"እራሴን ወገቤን ብሎ ሳይናገር
እንዲህ ሆኖ ቀረ የወሎማ ነገር!"
·
ዛሬ "በብሄሬ ሰበብ ተገፋሁ" ብሎ የብሶት ፖለቲካ የሚያራምደው ስንቱ ነው? ዛሬ "በማንነቴ ተበድያለሁ" ብሎ የቂም ታሪክ የሚያስተጋባው ስንት ነው? ግን በዚች የግፍ ምድር ላይ እንደ ሙስሊሙ የተገፋ አለ ወይ? እንደ ሙስሊሙ በጅምላ የታ -ረደ አለ? እንደ ሙስሊሙ በግፍ የተፈናቀለ አለ? እንደ ሙስሊሙ የታሪክ ደባ የተፈፀመበት አለ?! በፍፁም!
"ኢትዮጵያ የመቻቻል ሃገር ናት" የሚለው አባባል በሃገሪቱ በፖለቲከኞችና በጋዜጠኞች ከመደጋገሙ የተነሳ እውነት የመሰለ ትልቅ ውሸት ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ መቻቻል እንዳልነበረ አንድ ሺ አንድ ማስረጃዎችን መደርደር ይቻላል። ትላንት ቀርቶ ዛሬም መቻቻል የለም። ነገር ግን መብቱን የሚጠይቀውን ሁሉ "ፀረ መቻቻል" አድርጎ በመሳል ነባሩን አግላይ አካሄድ ቀባብተው ማስቀጠል ነው ህልማቸው። ትላንት ያልነበረውን፣ ዛሬም የሌለውን መቻቻል እያዜሙ!
·
መስጂዶች ሲፈርሱና ሲቃጠሉ፣ ለመስገጃ ኩርባን መሬት ሲከለከል፣ ሙስሊም ተማሪዎች በሃይማኖታቸው ሳቢያ ከትምህርት ገበታ ሲባረሩ ከግል እስከ መንግስት ሚዲያዎች እና ጋዜጠኞች፣ እስከ አክቲቪስቶች ድረስ ኮሽታ አያሰሙም። ይልቁንም አንተ ቤተ ክርስቲያን ስታፀዳ፣ የኩ ^ፍ -ር በአል ስታደምቅ፣ ለቤተ ክርስቲያን መገንቢያ ገንዘብ ስታስገባ በመቻቻል ስብከት ያደነዝዙሀል። "ጥምቀት የክርስቲያን ብቻ ሳይሆን የሙስሊሙም ነው፣ የሁሉም ነው" እያሉ ከጋዜጠኝነት ባሻገር ሰባኪ ሰባኪ ይጫወቱልሀል። እነሱ ስራቸውን እየሰሩ ነው። ሃይለ ሥላሴ በሙስሊሙ ላይ ስውር ደባ ሲፈፅምም "ሃገር የጋራ፣ ሃይማኖት የግል ነው" የሚል መሸንገያ ነበረው። ዛሬም እንዲሁ እየተፈፀመ ነው። በምላስ እየሸነገሉ በተግባር መውጋት! "አዋህም ከም ዴ ሲል የሞዴ" አለ አርጎባ። "አባትህም እንዲህ ሲል ነው የሞተው!"
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 27/2011)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor