Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


كناشة ابن منور

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 1️⃣8️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 92፣ ሐዲሥ ቁ. 151


የዑምደቱል አሕካም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
~
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 92፣ ሐዲሥ ቁ. 151


ሲጋራ
~
ሲጋራ ጎጂ የሆነ ሱስ ነው። ጎጂ ነገር በኢስላም ሐራም ነው። ስለሆነም ጎጂ ነገርን መጠቀምም በጎጂ ነገር መነገድም ሐራም ነው። ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
"ለማንም ሰው ሲጋራ ሊሸጥ አይፈቀድለትም። ምክንያቱም ሲጋራ የተከለከለ ነውና። አላህ አንድን ነገር ከከለከለ የሽያጭ ዋጋውንም ነው የሚከለክለው። እንዲሁም ሲጋራን መሸጥ በወንጀልና ወሰን በመተላለፍ ላይ መተባበር ነው።" [አሊቃኡ ሸህሪይ፡ 22/57]

ኢብኑ ባዝ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ብለዋል፦
"ሲጋራ ማጨሱም፣ መሸጡም፣ በሱ መነገዱም አይፈቀድም። በዚህ ላይ ከባድ ጉዳትና መጥፎ ፍፃሜ አለበትና።" [አልፈታዋ፡ 6/456]
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor

* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M

* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL


ለወገን ተቆርቋሪ የሆኑ ደዕዋ ላይ የተሰማሩ አካላት እነዚህ አራት ርእሶች ላይ አጥብቀው ሊሰሩ ይገባል።
1- ሺርክ፣
2- ቢድዐ፣
3- ዘረኝነት እና
4- ጎጂ ሱሶች (ጫት፣ ሲጋራ፣ አስካሪ መጠጥ፣ አደንዛዥ እፆች)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


ይሄ የሚታየው የመን ሃገር ሐጁር ግዛት ውስጥ የሚገኝ የጫት እርሻ ነው። አካባቢው ቀድሞ የተለያዩ የሰብል አይነቶች የሚመረቱበት ነበር። መሬቱ በእህል ፈንታ በጫት ሲተካ የሚሆነው ግልፅ ነው። ጫት ምሳና እራት አይሆንም። ጫት የህፃናት አልሚ ምግብ አይሆንም። በዚህ መርዝ ቅጠል ሰበብ የእህል ምርት ቀንሷል። ለስንት ልማት መዋል የሚችል ገንዘብ ጤናን ከማቃወስ በቀር አንዳች ፋይዳ በሌለው ቅጠል ላይ ይወጣል። ከዚያ ህዝቡ ኑሮውን በእርዳታ ላይ ጥገኛ ያደርጋል። በሃገራችንም በብዙ አካባቢዎች ያለው ተጨባጭ ይሄው ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


"ካ'ነጋገርም ድግምት አለ"
~
ሐቅ ወይም እውነት ለመረዳት ቀላል፣ ለልቦና ጣፋጭ ነው። ነገር ግን ሐቅ ከኖሩበት ልማድ፣ ከግለሰባዊ ዝንባሌ እና ከማህበረሰብ ወግ ተቃርኖ ሲመጣ ለመቀበል ይከብዳል፤ ይመርራልም። ክብደቱንና ምሬቱን ለማስወገድ ወይም ለመቀነስ የአያያዝ ጥበብ እና የአነጋገር ክህሎት ትልቅ ድርሻ አላቸው። የሻከረ አያያዝና እና የቆረፈደ አቀራረብ ጣፋጩን እውነት እጅ እጅ እንዲል ያደርጉታል።

ከዚህ ተቃራኒ የሆነ ተጨባጭም በተግባር አለ። ስንትና ስንት ባጢል ባሸበረቁ ቃላት ተከሽኖ እልፎችን አሳስቷል?!

የንግግር ክህሎት ትልቅ ኃይል አለው። በትክክል አውቀነው ሳይሆን በተጋነነ ቡድናዊ ስብከት ያለ ደረጃው የሰቀልነው እዚህ ግባ የማይባል ስንት ሰው አለ?! የሌሎችን የቂምና ጥላቻ ዘመቻ ተከትለን መልካም ስብእናውን ያቆሸሽነው፣ ውለታውን በዜሮ ያባዛነው ስንት ሰው አለ?! እና የሌሎች አገላለፅ እይታችንን ሊያዛንፈው እንደሚችል በማሰብ ጥንቃቄ ማድረግ ጥሩ ነው። አንዳንዴ ሰውየው አቋሙ ቀጥ ያለ ሆኖ ሳለ ሌሎች ግን አጥጣመው ሊገልፁት ይችላሉ። እና የሰማሀውን ሁሉ አትመን ለማለት ነው። በግልባጩም እንዲሁ።

قال ابن الرومي :

في زخرفِ القول ترجيحٌ لقائلهِ - والحقُّ قد يعتريه بعضُ تغييرِ
تقول هذا مُجاجُ النحلِ تمدحُهُ - وإن تعِبْ قلت ذا قَيْء الزنابير
مدحاً وذماً وما جاوزت وصفهما - سحر البيان يُري الظلماء كالنور
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ ስለ ሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲልወሃብ ረሒመሁላህ ከተናገሩት
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 1️⃣5️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 86፣ ሐዲሥ ቁ. 143


መመለስ በሚቻልበት ፍቺ (የመጀመሪያ ወይም የሁለተኛ ፍቺ) ተፈታ ዒዳዋን ገና ያላጠናቀቀች ሴት ባሏ ቢሞት ትወርሳለች። አስከሬኑንም ማጠብ ትችላለች። ምክንያቱም ዒዳው እስከሚጠናቀቅ ድረስ ገና ፍቺው አልተጠናቀቀምና። ያለ ወሊይ እና ያለ ምስክር መመለስ የሚቻልበትም ሁኔታ ለዚህ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


የዑምደቱል አሕካም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
~
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 86፣ ሐዲሥ ቁ. 143


ትምህርት ሚኒስቴር መርዘኛ ኢስላም ጠሎች የተሰባሰቡበት ኋላ ቀር ተቋም ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ኪታብ ስንማር የሚገጥመን سدر የቁርቁራ ዛፍ ይሄ ነው። ቁርቁራ በሃገራችን ቆላማ አካባቢዎች በሰፊው የሚገኝ ሲሆን በተለይም በወንዝ ዳርቻዎች ላይ ይበዛል። መጠኑ ከመካከለኛ ቁጥቋጦ እስከ ትልልቅ ዛፍ ይደርሳል። ቁርቁራ የሚበላ ፍሬ ያለው እሾሃማ ዛፍ ነው። ገበሬዎች እርሻቸውንና ጓሯቸውን ለማጠር ይጠቀሙበታል።
የቁርቁራ ቅጠል ለፍየሎች እና ግመሎች ምግብ ከመዋሉ ውጭ በሃገራችን የረባ አገልግሎት የለውም። በውጭ ግን ካልተሳሳትኩ "ቀሲል" እያሉ ለፀጉርና ለቆዳ ውበት ይጠቀሙታል።
በቅርቡ የዑምደቱል አሕካም ደርስ ላይ ስለሚነሳ ነው ማስታወስ የፈለግኩት።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 1️⃣6️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single


ከመግሪብ በኋላ ዑምደቱል አሕካም ደርስ አለ። ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል ኢንሻአላህ፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ወሎ የመቻቻል ወይስ የግፍ ምድር?
~
"ወሎ ሌት እስላም፣ ቀን ክርስቲያን" ሲባል ሰምተሀል ወንድሜ? ዛሬ ሰው እየሳቀ ያወራዋል። በውስጡ ያዘለው መልእክት ግን የሚያስለቅስ እንጂ የሚያስቅ አይደለም። በተከፈተበት አስገድዶ የማጥመቅ ዘመቻ ሳቢያ ሞት የተጋረጠበት ህይወቱን ለማትረፍ ሲል ቀን ላይ "ክርስቲያን ነኝ" የሚልበትን፤ ሌት ላይ አራ -ጆቹ ከፊቱ ዞር ሲሉለት እለታዊ የእምነቱን ሕግጋት ሲፈፅም የነበረበትን ዘመን ነው የሚያስታውሰው። በዚህ ሳቢያ ነበር "ወሎ ሌት እስላም፣ ቀን ክርስቲያን" የተባለው።
ሌት ላይ በድብቅ ፆም ለመያዝ እሳት ሲያቀጣጥል ታይቶ የተንገላታው ስንቱ ነው?! ትላንት በዚህ አይነት ትንቅንቅ ነበር እምነቱን ያቆየው።
·
የትላንቷ ሙስሊማ ሃይማኖቷን መቀየሯን ያላመኑ ጉልበተኛ አጥማቂዎች ሲያስጨንቋት "ወላሂ ክርስቲያን ነኝ" ስትል ነበር። ሕይወቷን ለማትረፍ "ክርስቲያን ነኝ" ትላለች። ከስጋዋ ጋር የተዋሀደው ኢስላሟ ግን በጎን ሾልኮ እየወጣ ሂወቷን ስጋት ላይ ይጥልባታል። "ወላሂ" ትላለች። አነጋገሯ አስቆህ ከሆነ ሞኝ ነህ። ይሄ የሚያስለቅስ እንጂ የሚያስቅ አይደለም።
·
ይህ ሁሉ ከመፈፀሙ ጋር "ወሎ የመቻቻል ተምሳሌት" እያለ የሚወሸክት አለ። ወሎ የመቻቻል ሃገር ሳይሆን በአንድ ህዝብ ላይ የተፈፀመ መጠነ ሰፊ ሃይማኖት ተኮር ግፍ በገሃድ የሚታይበት ምድር ነው። በዮሀንስ፣ በምንሊክና በራስ ሚካኤል የተባበረ ክንድ እልፍ አእላፍ ሙስሊም በግፍ ተጨፍ ~ `ጭፏል። ከርስቱ ከመሬቱ ብቻም ሳይሆን እትብቱ ከተቀበረበት ሃገር ተፈናቅሎ በየጥሻው ቀርቷል። የአሞራና የጅብ ቀለብ ሆኗል። በረሃብ በቸነፈር እንደ ቅጠል ረግፏል። ጠኔ ባደከማቸው ከሲታ እግሮቹ የወራት መንገዶችን አቆራርጦ ወደማያውቀው ምድር ተሰዷል። እጅግ ብዙው ካለመበትም ሳይደርስ አንድም በሚያሳድደው ጥጋበኛ የኩ ^ f ር ሰራዊት፣ አለያም በረሃብና በወረርሽኝ መንገድ ላይ ቀርቷል።
የተረፈው አይናቸውን በጨው አጥበው "ኢስላም በሰይፍ ነው የተስፋፋው" እያሉ በሚከሱ ሃፍረተ ቢሶች ያለ ምርጫው በሃይል ተጠምቋል። በገዛ እጁ መስጂዱን እያፈረሰ ቤተ ክርስቲያን እንዲገነባ ተደርጓል። የማወራው እዚችው የግፍ ምድር ላይ ስለተፈፀመ ግፍ ነው። ስለ መቻቻል ሰርክ የሚዜምላት ኢትዮጵያ!
·
አስገድዶ የማጥመቅ ዘመቻው ካለፈ በኋላም በሙስሊሙ ላይ የሚፈፀመው ግፍ መልኩን ቀይሮ እንደቀጠለ ነበር። ህዝበ ሙስሊሙ ለገዛ እምነቱ ባይተዋር እንዲሆን፣ የነሱ ባእላት አድማቂ እንዲሆን ተደርጓል። በተፈፀመበት የረጅም ጊዜ ሴራ የተነሳ ጥምቀት እና ገና የሚያከብር፣ ደመራ የሚያቃጥል፣ "አልሐምዱ ሊላሂ ታቦታችን ገባ" እያለ ታቦት የሚሸኝ፣ ፀበል የሚመላለስ፣ ማንነቱ የተደባለቀበት ትውልድ ተፈጥሯል። ይሄ ግን አንዳንድ ቅቤ አንጓቾች እንደሚያስተጋቡት የመቻቻል ውጤት አይደለም። ይልቁንም አስገድዶ ከማጥመቅ የቀጠለው ማንነትን የማደባለቅ ዘመቻ ውጤት ነው።
ይህን ያዩ ሸይኽ ነበሩ እንዲህ ሲሉ የገጠሙት:–
·
"እራሴን ወገቤን ብሎ ሳይናገር
እንዲህ ሆኖ ቀረ የወሎማ ነገር!"
·
ዛሬ "በብሄሬ ሰበብ ተገፋሁ" ብሎ የብሶት ፖለቲካ የሚያራምደው ስንቱ ነው? ዛሬ "በማንነቴ ተበድያለሁ" ብሎ የቂም ታሪክ የሚያስተጋባው ስንት ነው? ግን በዚች የግፍ ምድር ላይ እንደ ሙስሊሙ የተገፋ አለ ወይ? እንደ ሙስሊሙ በጅምላ የታ -ረደ አለ? እንደ ሙስሊሙ በግፍ የተፈናቀለ አለ? እንደ ሙስሊሙ የታሪክ ደባ የተፈፀመበት አለ?! በፍፁም!
"ኢትዮጵያ የመቻቻል ሃገር ናት" የሚለው አባባል በሃገሪቱ በፖለቲከኞችና በጋዜጠኞች ከመደጋገሙ የተነሳ እውነት የመሰለ ትልቅ ውሸት ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ መቻቻል እንዳልነበረ አንድ ሺ አንድ ማስረጃዎችን መደርደር ይቻላል። ትላንት ቀርቶ ዛሬም መቻቻል የለም። ነገር ግን መብቱን የሚጠይቀውን ሁሉ "ፀረ መቻቻል" አድርጎ በመሳል ነባሩን አግላይ አካሄድ ቀባብተው ማስቀጠል ነው ህልማቸው። ትላንት ያልነበረውን፣ ዛሬም የሌለውን መቻቻል እያዜሙ!
·
መስጂዶች ሲፈርሱና ሲቃጠሉ፣ ለመስገጃ ኩርባን መሬት ሲከለከል፣ ሙስሊም ተማሪዎች በሃይማኖታቸው ሳቢያ ከትምህርት ገበታ ሲባረሩ ከግል እስከ መንግስት ሚዲያዎች እና ጋዜጠኞች፣ እስከ አክቲቪስቶች ድረስ ኮሽታ አያሰሙም። ይልቁንም አንተ ቤተ ክርስቲያን ስታፀዳ፣ የኩ ^ፍ -ር በአል ስታደምቅ፣ ለቤተ ክርስቲያን መገንቢያ ገንዘብ ስታስገባ በመቻቻል ስብከት ያደነዝዙሀል። "ጥምቀት የክርስቲያን ብቻ ሳይሆን የሙስሊሙም ነው፣ የሁሉም ነው" እያሉ ከጋዜጠኝነት ባሻገር ሰባኪ ሰባኪ ይጫወቱልሀል። እነሱ ስራቸውን እየሰሩ ነው። ሃይለ ሥላሴ በሙስሊሙ ላይ ስውር ደባ ሲፈፅምም "ሃገር የጋራ፣ ሃይማኖት የግል ነው" የሚል መሸንገያ ነበረው። ዛሬም እንዲሁ እየተፈፀመ ነው። በምላስ እየሸነገሉ በተግባር መውጋት! "አዋህም ከም ዴ ሲል የሞዴ" አለ አርጎባ። "አባትህም እንዲህ ሲል ነው የሞተው!"

(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 27/2011)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ኃላፊነት እዳ ነው
~
ከሚገርሙ ነገሮች ውስጥ አንዱ በህዝባዊ አገልግሎት ላይ የተመደበ ሰራተኛ ተገልጋይን ሲያንገላታ ማየት ነው። ኑሮውን የመሰረተበት ወር ጠብቆ የሚወስደው ደመወዝኮ ከህዝብ የተሰበሰብ ገንዘብ ነው። ሐቀኛ ሰራተኛ ሁሌም አንድ ነገር መያዝ አለበት። የሚሰጠው አገልግሎት የዜጎች መብት እንጂ የሱ እርጥባን እንዳልሆነ። ዜጎች አገልግሎት ማግኘት ሐቃቸው ነው። ህዝብ ማገልገያ ወንበር ላይ ተቀምጦ፣ በህዝብ ገንዘብ እየኖረ ከዚያ ሰዎችን ሐቃቸውን መንፈግ ስልጣኔ ሳይሆን ኋላ ቀርነት ነው። እንዲህ ለመሆን ችሎታ ሳይሆን ህሊና ቢስ መሆን ነው የሚፈልገው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


‏إذًا، إذن : كلتاهما صواب
لك أن تكتب بما شئت، والشائع في الكتابة (إذًا)
لكن (إذًا) تكتب بالتنوين لتوكيد الخطاب {إنا إذًا لخاسرون}{قال نعم وإنكم إذًا لمن المقربين}
(إذن) مختصة بالدخول على الفعل المضارع وناصبة له
إذن أكرمك جواب لمن قال :سأزورك
وللعلم (إذن) لم ترد في القرآن الكريم

المرصد اللغوي


‏قد تشترك كلمات في ‎#العربية في الصوت وتختلف في صورة الكتابة ونوعها منها :
يحيى: اسم، يحيا: فعل
عصا : اسم، عصى: فعل
أبا : اسم ، أبى : فعل
على : حرف ، علا : فعل
نما : فعل ، نمى : فعل
لمى : اسم ، لَمَا : حرف
غلا : اسم ، غلى : فعل

‎المرصد اللغوي


ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 1️⃣5️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 75፣ ሐዲሥ ቁ. 126


ዑምደቱል አሕካም ደርስ
~
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 75፣ ሐዲሥ ቁ. 126

20 last posts shown.