ትዳር በኢስላም🌺


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


☞አላማችን ከዝሙት የፀዳን ማህበረሰብ መፍጠር ነዉ።
☞❥የትዳርን ችግር ለመቅረፍ✓
☞ዝሙትን ለማጥፍት✖
☞ወጣቱን ወደ ትዳር እንድገባ ለማድርግ❥
የተለየዩ አስተማሪ ታሪኮች ፣ የስኬታማ ትዳሮች ልምድ፣
የተለያዩ መጣጥፎች የሚቀርቡበት ቻናል ነው ‼️
https://t.me/eross_eross
▮Share and Join

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ረመዳን-4🌙

ጁዝእ-4

ቃሪእ:- አቡ በክር አሽ-ሻጢሪይ
القارئ= ابو بكر الشاطري
👇👇👇👇
@eross_eross


ረመዳን-3🌙

ጁዝእ-3

ቃሪእ:- ያሢር አደውሠሪ
القارئ= ياسر الدوسري
👇👇👇
@eross_eross


ረመዳን-2🌙

ጁዝእ-2

ቃሪእ:- ተውፊቅ አስ-ሷኢግ
القارئ= توفيق الصائغ

ቻናል:- 🌙 «አስ_ሱናህ
↓ ↓ ↓
@eross_eross


⭕ #የረመዷን_ትሩፋቶች

ጾም ከኢስላም ማዕዘናቶች መካከል አንዱ ሲሆን የሚያስገኛቸው ፋይዳዎችና በረከቶች በርካታ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ፋይዳዎች መካከል የአላህ መልክተኛ ﷺ በሐዲሳቸው የተናገሩት አንዱ ነው፡፡

"من صام رمضان إيمانا واحتسابا غفر له ما تقدم من ذنبه" البخاري: ٣٨، مسلم: ٧٥٩

“ከአላህ ዘንድ የሚገኘውን አጅር ታሳቢ አድርጎ እና አምኖ የረመዷንን ጾም የጾመ ከዚህ በፊት ያለፈው ወንጀሉ ይሰረዝለታል፡፡” (ቡኻሪ: 38, ሙስሊም: 759)

ጾም በመጾም የሚገኘው ምንዳ ወይም አጅር እንደ ሰዎች ኒያ ወይም ኢኽላስ ሊለያይ ይችላል፡፡ በጾሙ መካከል ተፈጻሚ የሚሆኑ መልካም ተግባራቶች አንዱን ከፍ አንዱን ዝቅ ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የጾምን አዳብና ስርዓት የሚጠብቅ እና የማይጠብቅ ከአላህ ዘንድ እኩል ደረጃ አይኖረውም፡፡

የረመዷንን ወር ከሌሎች ወሮች ለየት የሚያደርገው የሚሰሩ መልካም ተግባራት ሁሉ ምንዳቸው እጥፍ ድርብ መሆኑ ነው፡፡ በዚህም 。。。


🔶 በረመዷን ወር ሙስሊሙ ሊሰራቸው የሚገቡ መልካም #ተግባራት
.
.
👇👇👇👇👇👇👇
http://telegram.me/tewihd


ረመዷን _1
  🔃ቁርአን ጁዝእ ➊

ቃሪእ:- አቡ በክር አሽ-ሻጢሪይ
القارئ= ابو بكر الشاطري

ቻናል
👉🏿@tewihd


በድጋሚ ረመዷን ሙባረክ🌙


✴️🌙 ሰበር ዜና ... ሰበር ዜና ⤵️

✴️ 🌙 ...*عاجل ... عاجل*...

*تم رصد هلال رمضان في تمير*

*غداً السبت أول أيام شهر رمضان المبارك*

*{تقبل الله منا ومنكم صالح الاعمال}*

*✍ "الراصد نيوز"

📮 ሱዑዲ ላይ ጨረቃ ስለታየች አላህ
ካለ ነገ ቅዳሜ የረመዷን ፆም ጅማሬ  ይሆናል።


@tewihd👉@eross_eross


«ውዷ―እህቴ»

ትዕግስትን( ሶብርን) ስንቅሽ!
የአላህን ቃል ቁርዓንን ጓደኛሽ!
ተወኩልን ተስፋሽ አድርገሽ ይዘሽ!
"ዒልምን ከመፈለግ አትሰልች ።
┊❄┊❄┊❄┊🌹🍃ـ
┊❄┊❄┊🌹🍃ـ
┊❄┊🌹🍃ـ
@eross_eross


🚨 አምስቱ የጂብሪል መልዕክቶች

➥ የፈለከውን ያክል ኑር ሟች ነህ።
➥ የፈለከውን ውደድ ትለየዋለህ።
➥ የፈለከውን ስራ ትመነዳበታለህ።
➥ ሌሊትን መቆም የአማኝ ክብር ነው።
➥ ከሰዎችም መብቃቃቱ ክብር ነው።

🎤 በኡስታዝ አቡ ዐማር ዐብድልዐዚዝ ፈረጅ አላህ ይጠብቀው።
👉🏻https://t.me/tewihd


የኛስ አሻራ የታለ!?

ሁድሁድ - በባዕድ አምልኮ ተሰማርተው ለነበሩ የሰበእ ህዝቦች መስለም ምክኒያት ሆኗል፡፡

ጉንዳን - የነቢዩ ሱለይማን ግዙፍ ሰራዊት ትናንሽ ፍጥረታት ላይ አደጋ እንዳያደርስ አቅጣጫ አስቀይሯል፡፡

ቁራ - ንፁህ ነፍስ አጥፍቶ መላ ጠፍቶት ሲዋትት የነበረውን የሰው ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የአቀባበር ሥርኣትን አስተምሯል፡፡

ዝሆን - የአላህን ቤት ከዕባን ለማፍረስ በተንቀሳቀሰው ጦር ላይ በማመጽ ከአምባገነኖች ጋር ለመተባበር አሻፈረኝ ብሏል፡፡

ዓሳ ነባሪ - በህዝባቸው ተበሳጭተው ከጨለማው ባህር ዉስጥ ለተጣሉት ለአላህ ነቢይ ዩኑስ (ዐ.ሰ.) መጠለያ ሆኖ አገልግሏል፡፡

ሸረሪት - ድሯን በመተብተብ ታላቁን ነቢይ ሰለላሁ.ዐለይሂ.ወሰለም ከጠላት ዐይን ጠብቃለች፡፡

እኮ የኔና ያንተ አሻራ የታለ…
‹በላጩ ሰው ለሰው ጠቃሚ የሆነው ሰው ነው፡፡› ይላሉ የአላህ ነቢይ ሶለላሁ.ዐለይሂ.ወሰላም

👉🏻@tewihd


ኢስላማዊ የወር አቆጣጠር ቅደም ተከተል፡-
1ኛ ወር- ሙሐረም
2ኛ ወር- ሰፈር
3ኛ ወር- ረቢዑል-አወል
4ኛ ወር- ረቢዑ-ሣኒ
5ኛ ወር- ጀማዱል-አወል
6ኛ ወር- ጀማዱ-ሣኒ
7ኛ ወር- ረጀብ
8ኛ ወር- ሻዕባን
9ኛ ወር- ረመዷን
10ኛ ወር- ሸዋል
11ኛ ወር- ዙል-ቀዒዳህ
12ኛ ወር- ዙል-ሒጃህ
@Tewihd @Tewihd


በትክክለኛ መንገድ ላይ ሁን
በድጋሚ
Mubark Ahmed
👇👇👇
@eross_eross




✍የሰብር አንቀፆች ምንኛ ያምራሉ...

‌﴿ وَبَشِّرِ الصَّابِرِينَ﴾
ታጋሾችን(ሰብረኞችን) አበስራቸው።

﴿وَاللَّهُ يُحِبُّ الصَّابِرِينَ﴾
አለህ ታጋሾችን ይወዳቸዋል

‌﴿وَاصْبِرْ وَمَا صَبْرُكَ إِلَّا بِاللَّهِ ۚ﴾
ታገስ የመታገስህ ምንዳ ከአለህ እንጂ ከሌላ አይደለም

﴿ وَجَزَاهُمْ بِمَا صَبَرُوا جَنَّةً وَحَرِيرًا﴾
በመታገሳቸው ጀነትንና የሃር ልብስ መነዳቸው

‌﴿إِنَّمَا يُوَفَّى الصَّابِرُونَ أَجْرَهُمْ بِغَيْرِ حِسَابٍ﴾
ታጋሾች ምንዳቸውን ያለ ልኬት ነው የሚያገኙት።
"አለህ የማይፈትነኝ ሳይወደኝ ቀርቶ የታጋሾችን ምንዳ ልያሳጣኝ ፈልጎ ይሆን?"(ከአባቶቻችን ንግግር)
-------------
ከሰብር ውጪ ይህ ሁሉ ምንዳ የሚገኝበት ምን አለ?
👇👇👇👇
https://telegram.me/tewihd


መወጠራችን አያስከፋን

ህይወት በብዙ ስንክሳሮች የተሞላች ስለመሆኗ ሁላችንም ጋር ያለ እውነታ ነው።ስለ አንዱ ቀዳዳ መደፈን ስናስብ ሌላ መከፈቱም የዚሁ አካል መሆኑ ሳለ የውጣውረዶቹ መብዛት በራሱ የሚፈጥረው ራሱን የቻለ ውጥረት አለ።ታድያ ይህን ውጥረት ምን አይነት ምላሽ እንስጠው?በመከፋት ለምን ተወጠርኩ በሚል እሳቤ ወይንስ ያሉትን ጥሩ ጎኖች አጉልቶ በማየት.....ለመልሱ ሚሆን ምሳሌ እነሆ. . . የብር ላስቲክ በዕለት ተዕለት የህይወት አጋጣሚዎቻችን ሚገጥመን ነገር ነው።ይህ ላስቲክ እየተለጠጠ በሄደ ቁጥር የረጅም ርቀት ኢላማውን መምታት ይችላል. . .ምናሳርፍበት ውጥረት በቀነሰ ቁጥር ግን አጭር ርቀት ብቻ መጓዝ መቻሉ እሙን ነው ታድያ የእኛ ውጥረቶችስ የት
ኛውን አላማ ለማሳካት ይረዱን ይሆን???
እናስተውል: ለውጥረት የሚሆን ምላሽ መስጠት ካልጀመርን ውጥረቱ ሲበዛ ላስቲኩ እንደሚበጠሰው እኛም ተሰብረን ዳግም ላንቃና እንችላለንና እናስብበት. . .

𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 𝐒𝐇𝐀𝐑𝐄👇
👉@eross_eross


➧ለምን አታገባም?

→በዚህ ዘመን ያላገባ በሸይጣን መረብ ውስጥ መከራን ይጋታል!

☞ ሸይኽ ሳሊህ አል' ፈውዛን፦

"ሴት ያለ ወንድ በመከራ ላይ ነች። ወንድም ያለ ሴት መከራ ውስጥ ነው። ተመጣጣኝ ጥንዶች በትዳር ከተቆራኙ የተሟላ ፀጋ ውስጥ ናቸው።"

[اعانة المستفد (2/220)]

☞አል' ኢማም አል' ጁወይኒይ አሽ ሻፊዒይ፦

"ላጤነት የእብደት ሰበብ እንደሆነ ሁሉ ኒካሕ እብደትን ከሚያስወግዱ ነገሮች አንዱ ነው።"
[نهاية المطلب (12/43)]

☞ኢብኑ ዓባስ፦

"አላህ ልጅ የሰጠው ሰው መልካም ስም ያውጣለት፤ በስነ ስርኣትም ኮትኩቶ ያሳድገው፤ ለአቅመ አዳም የደረሰ ግዜ ይዳረው!"

[رواه ابن ابي الدنيا في العيال (443/1)]

☞ሱለይማን አር' ሩሐይሊይ፦

"ያለ ምንም ምክንያት ከማግባት የሚያፈገፍግ ሰው ወደ ሐኪም ጎራ እንዲል እንመክረዋለን"

(منقول من محاضرة)

☞ሸይኽ ሙቅቢል አል 'ዋዲዒይ፦

"እህትህን ወይም ሴት ልጅህን (ለጣሊበል ዒልም) የሸሪዓ እውቀት ተማሪ ለሆነ ወንድ መዳር ለአንተ ከዱንያና በውስጧ ካሉ ነገሮች ሁሉ በላጭ ነው!"

[البشائر في السماع المباشر ص 13 ]

☞ሸይኽ አሕመድ አን' ነጅሚይ፦

"ወንድ ልጅ መልካም ሴት ጋር ትዳር እስኪመሰርት ህይወቱ የተሟላና ደስተኛ አይሆንም። ሴትም እንደዛው።"

[تأسيس الاحكام (4/172) ]

☞ታላቁ ታቢዒይ ጣውስ ፦

"እስኪያገባ ድረስ የአንድ ወጣት ዒባዳ አይሟላም"
[السير (570/1)]

☞ታላቁ ታቢዒይ ኢብራሂም አን ነኸዒይ፦

"አግባ! ቤቷ ሆና የሚመግባት ጌታ በአንተም ቤት አንተንም እሷንም ይመግባቿል!"

[تاريخ ابن محرز (150)]

👉@eross_eross


ረመዳንም እየደረሰ ስለሆነ ቀዷ ያለባቹህ ከወዲሁ ጨርሱ ::

ረመዳን 14 ቀናት ይቀሩታል
መልካም ለይል 🥀


ረመዳን የምንቀበለው

በቁርኣን ወይስ በመንዙማ?

ነብያዊ አስተምህሮቱ ይህ ነበር፦

አቢ ኡማማህ (ረድየላሁ ዐንሁ) የአላህ መልዕክተኛ (ሠለላሁ ዓለይሒ ወሠለም) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፦

«ቁርንን አንብቡ እሱ (ቁርአን) የትንሣኤ እለት ለአንባቢው አማላጅ ሆኖ ይመጣልና:: »

(ሙስሊም ዘግበውታል።)

መጠሪያችን "የቁርኣን ህዝቦች" ነበር ዛሬ ላይ ያለው ተጨባጭ ግን ሌላ ነው

«ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ» ይሉ ዘንዳ ሰዎች በምላሳቸው ባይናገሩትም ተግባራዊ ንግግራቸው ግን ያ ዑመተል ቁርአን !!! ስትል አቦ ፋራ አትሁን "ያ ዑመተ ነሺዳ" "ያ ዑመተ መንዙማ" ነው የሚባለው የሚል ድባብ አለው::

ስንቶቻችችን ለማስተዋል ሞክረን ይሆን!???

እስኪ ታዘቡ ነገር ዓለሙ እኮ መላ ቅጡ ጠፍቷል ! ...

ስልኮች፣ ኮምፒዩተሮች ብቻ ምን አለፋችሁ ዘመናዊ የመጠቃቀሚያ ንብረቶቻችን ቁርአንን Unsuported file format ያሉት ይመስል የቁርአን ድርቅ መቷቸዋል :: እንደው ነፍሱን ተጭኖ "ለበረካው" ብሎ የጫነባቸውም Folder ሠጥቷቸው memory space ከመያዝ ውጪ አድማጭ አጥተዋል ::

ምክንያቱ ወዲህ ነው፦

"ኢስላማዊ አዋርድ" ላይ ተሸላሚና ተፎካካሪ "ነጠላና ጋቢ" የሆኑ "አስለቃሽ" "መሳጭ" እየተባሉ የሚለቀቁ ከሀያሉ ጌታ ቃል በላይ ቅድሚያ የተሰጣቸው የሠዎች ግጥምና ዜማ ተደመጠውና ተሐፍዘው (ተሸመድደው) ስላላቁ ነው ::

ምን ይደረግ ብለህ ነው! ወዲህ ወደ ቁርኣን ተጣሪው ሲሸማቀቅ ፣ ሲሽመደመድና ሲልፈሰፈስ ፤ ወዲያ ሙነሺዱ ጥርስን አብቅሎ፣ ዳዴውን ጨርሶ ፈረጠመ።

ሱናው ጭሰኛ ቢድዓው ባላባት ሆነ! ነሺዳውን ትተህ ቁርኣኑን አዳምጥ ስትለው "ደግሞ ጀመረው" ይልና እዚህ የማልጠቅሰው ውርጅብኝ ያወርድብሃል!

አንተ ስድቡን አጣጥም እኔ ፅሁፌን ቀጠልኩ …

እና እላችኃለሁ ወዳጆቼ!

ታላቁን እንግዳችንን የቁርኣን ወር ረመዷን ለመቀብል በጉጉት ስንጠብቅ ፣ ለ11 ወራት አብዛኞቻችን አኩርፈነው የነበረውን ቁርኣን የሚነበብበት ጊዜ መጣ ብለን ስንፈነድቅ።

ለካ እዚህ ጋር ሌላ ዱብዳ መጥቷል፦

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከቱ የመጡ የነሺዳና የመንዙማ አይነቶች (አዘጋጆቹ አሰቡትም አላሰቡትም) ሙስሊሙን ዑማ ከቁርኣን የሚለያዩ መቀሶች ሆነዋል።

ረመዷን ሲመጣ ሰው የተለያዩ ቃሪኦችን ሲዲ ከመግዛት ይልቅ ፣ ወሩን እግር በእግር ተከታትለው የሚወጡ አዳዲስ የነሺዳና የመንዙማ ሲዲና ካሴቶች ሲሸምት እየታዘብን ነው!

የመሳጂድ በራፎች በአዳዲስ ነሺዳና መንዙማ (መርዙማ) ፖስተርና ድምፆች እየታመሱ ይገኛል።

በጣም እኮ ነው ልብ የሚያደማው!

ሱረቱል ቂያማን በላጥ ላጥ ቀርተን እያለፍን በነሺዳና መንዙማ ተፈኩር እያደረግን እናለቅሳለ....

"ቢያለቅስ" አንተ ምን አገባህ የእንባ ትራፊክ / ባንክ ልትሆን ነው? የሚል አይጠፋም! ልክ ነው "ትራፊክ አልሆንም" ግን…

«إِنَّ فِي ذَلِكَ لَذِكْرَى لِمَن كَانَ لَهُ قَلْبٌ أَوْ أَلْقَى السَّمْعَ وَهُوَ شَهِيدٌ

[سورة ق الآية 37]

«በዚህ ውስጥ ልብ ላለው ወይም እርሱ (በልቡ) የተጣደ ሆኖ (ወደሚነበብለት) ጆሮውን ለጣለ ግሳጼ አለበት» (ቃፍ 37)

እንባው ከተቅዋ የሚመስለን ካለን እንዳንሸወድ ለማለት ያክል ነው...

"ተቅዋ ማለት ዐይንን እያሻሹ ማልቃቀስ ሳይሆን አላህ ዘንድ ያስቀጣኛል ብለን የምናስበውን መጥፎ ስራ ለአላህ ብለን እርግፍ አድርጎ መተው ነው "

ይላሉ ዑለማዎቻችን! ለተቅዋ ከሰጧቸው የተለያዩ ትንታኔ መካከል ነው።

ተቅዋ የሚገኘው በቁርአን ሲያለቅሱ ፣ ሲመከሩ ፣ ሲገሰፁ ከምንም ነገር በላይ ለእርሱ ቅድሚያ ሲሰጡና ሲተገብሩት ነው::

ብዙ ቢያስብልም በዚህ ተብቃቃሁ!

ለዛሬ ራሴን የምገስፅበትን እናንተን የማስታውስበትን ፅሁፍ በዚህ አበቃሁ::

የፅሁፉ አላማ ሌሎችን ማነወር ፈፅሞ አይደለም! በስህተቶች ላይ መተራረም ፣ ሙስሊሞችን ወደ ቁርኣን መጣራት ስህተትንና ስህተተኞችን ማውገዝ ብቻና ብቻ ነው።

የፃፍኩት ያሰብኩትን ነው ፤ ያሰብኩትም የፃፍኩትን ነው!

እንደ ወንጀላችን ሳይሆን እንደራህመቱ የሚያኖረን ጌታ ምስጋና ይገባው::

ያ አላህ! ሙስሊሙን ዑማ ከነሺዳና መንዙማ ፍቅር አላቀህ የቁርኣንን ፍቅር በልባችን አድርግልን! አንተ ሁሉን ቻይ ነህና!

ቁርአንን አንብበው ሰርተውበት የቂያማ እለት ምልጃ ከሚሆንላቸው ያድርገን !!!

አላሁመ አሚን!!!!
👇👇👇👇👇
https://telegram.me/tewihd


ትዳር በኢስላም
የአላህ መልዕክተኛ {ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም} እንዲህ ይላሉ፦
ሴት ልጅ ለአራት ነገራቶች ትታጫለች
★ለመልኳ
★ለገንዘቧ
★ለዘሯና
★ለዲኗ

ዲን ያላትን ያልመረጠ እጁ አመድ ይፈስ ብለዋል።
👉@eross_eross



20 last posts shown.