ከመጽሐፍት መንደር💠


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


አንብብ አዕምሮህ ልክ አንደባህር ይሰፋል። ወንዞችም ለአንተ መገበር ይጀምራሉ። አንተ ወደ ሰዎች ሳይሆን ሰዎችም ወደአንተ ይመጣሉ። ማንብብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!! አንብብ ብታነብ የሚቀርብህ ድንቁርና
🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩
🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨
🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥
ለማንኛውም አስተያየት
@manbabemuluyadergal_bot

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


‹‹አልገባኝም..ይቅርታውስ ለምን ?ምስጋናውስ?፡፡› ‹‹ይቅርታው ገና ስትመጪ ጀምሮ በሙሉ ልቤ ስላልተቀበልኩሽና ለእኔም ሆነ ለቤተሰቦቼ እንደሸክም ስለቆጠርኩሽ…ምስጋናው ዛሬ እናቴንም ሆና መላ ቤተሰብን አንበሽብሸሽ በማስደሰትሽ…..››
‹‹ተው ተው..አሁን ከዚህ ውብ እና አስደሳች ሙዚቃ በኃላ እንዲህ አይነት ንግግር አስፈላጊ ነው…?ይሄውልህ ምን አልባ አንተ ፍቅር በሚፈስበት ቤት ውስጥ በስስት በሚተያዩ ወላጆች እቅፍ ውስጥ ያደክና እስካሁንም እየኖርክ ያለህ ሰው ስለሆንክ ስለመገፋትና ጥላቻ ያለህ እውቀት አናሳ ይመስለኛል….አዎ እንዳልከው ከልብህ በደስታ አልተቀበልከኝም ይሆናል…ግን ደሜን ሲጠርጉ አብረህ ጠርገሀል….በህመም ስጮህ አዝነህ ስትሸማቀቅ ነበር…በእኩለ ለሊት እንደህፃን ተሸክመህ ሀኪም ቤት ወስደሀኛል…. ሽንት ቤትም ስታመላልሰኝ ነበር፡፡ …አእምሮህ የተወሰኑ ክፉ ነገሮችን አሰቦ ቢፈታተንህም ልብህ ግን መልካምና በፍቅር የተሞላ ስለሆነ ድርጊቶች በአጣቃላይ መልካምና ውብ ነበረ….በዚህም ምስጋናዬ ለዘላለም ነው…፡፡ደግሞ አደረግሽ ላልከኝ ..ምንም ያደረኩት ነገር የለም..እኔ እራሴ የምጠቀምበትን ዕቃዎችና የምበላቸውን ምግቦች ነው የተገዛበት፣ይልቅ አንድ ነገር ላስቸግርህ አስቤያለው፡፡››
‹‹ምንድነው..ምችለው ከሆነ ችግር የለውም… ጠይቂኝ››
‹‹በእኔ እና አንተ መካከል በሚስጥር የሚያዝ ነው››
‹‹እኮ ልስማው››
‹‹ትናንት ለሊት የነገርከኝ ትዝ ይልሀል አባትህ ዕቁብ የገባበትን ምክንያት››
‹‹አዎ ትዝ ይለኛል፡፡››
‹‹እንደነገርከኝ ከሆነ ከእዚህ ቤት ቀጥሎ አንድ ሰርቢስ ሊሰራ ነው….››

‹‹አዎ  ይሄ  የተቆለለው  ብሎኬት  ለዛ  የተገዛ  ነው፡፡ነፍሷን  ይማርና  እህቴ  ነበር የገዛችው…ይሄም አሻዋ እንደዛው፡፡››
‹‹ጥሩ ….ስለዚህ ቀሪ የሚያስፈልገው ነገር ምን ምን ይመስልሀል?››
‹‹ያው  ሀያ  ቆርቆሮ  ..ሚስማር  ሲሚንቶ….በራፍ  መስኮት..በዋናነት  እነዚህ  ናቸው የሚያስፈልጉት..ከዛ አባዬ እራሱ ግንበኛም ሀናጢም ስለሆነ የባለሞያ ወጪ የለበትም››
‹‹ስንት ብር የሚፈጅ ይመስልሀል?››
የጥያቄው መአት ውሉ ስላልገባው‹‹ምን አስበሽ ነው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ንገረኝ ስንት ይፈጃል?››
‹‹ለማሰቢያ የሚሆኑትን 5 ደቂቃ ካባከነ በኃላ  ብዙ ነው እስከ50 ሺብር የሚፈጅ ይመስለኛል…››
‹‹ጥሩ አንድ ሀሰብ አለኝ..ሁለት ክፍል ቢሆን ግን ጥሩ ነው››
በጭለማ ውስጥ አፍጥጦ አያት..ይህቺ ልጅ ጭንቅላቷን የተመቻችው ከቆይታ በኃላ ተናግቶ አሁን እያቃዣት ይሆን እንዴ ?››ስል አሰበ፡፡
‹‹አልገባኝም፡፡››
‹‹አንዱ ክፍል የሚቀጥለው እናንተ ጎረምሶቹ እንድታድሩበት አይደል.?››
‹አዎ ትክክል ነሽ…››
አንዱ አነስ ያለ ክፍል ደግሞ እንዲህ ወደ ዋናው መንገድ ጠጋ ብሎ ቢሰራና በውጭ በኩል በራፍ ቢወጣለት ጥሩ አይደል…?››
‹‹ለምኑ ነው ጥሩ የሚሆነው?››
‹‹አንተ ደግሞ አይገባህም እንዴ ?ለለሊሴ ፀጉር ቤት እንድትከፍትበት  ነዋ…ሞያ አላት
….የራሷን አነስተኛ ፀጉር ቤት ብትከፍት እኮ በጣም ድንቅ ነው፡፡››
‹‹በጣም ድንቅ ነው..ግን አንቺ ሰላም ነሽ?››

‹‹አዎ ሰላም ነኝ…..ምነው ጠየቅከኝ?››
‹‹ይሄ ሁሉ የምታወሪው የሟች እህቴ እቅድ ነበር..አሁን አንቺ በማይጨበጥ ሀሳብ እንድቃዥ እያደረግሺኝ ነዋ፡፡››
‹‹አይ እንደዛ አይደለም…ነገ ስራ መቅረት ወይም ማስፈቀድ ትችላለህ? ››
‹‹እችላለው…ግን ለምን?››
‹‹100 ሺ ብር እሰጥሀለው..ያልኩህን ሁለት ክፍል ቤት ለመስራት የሚያስፈልግጉትን እቃዎችን በሙሉ ትገዛና አምጥተህ ግቢውስጥ ትዘረግፈዋለህ…ከዛ ጋሼ ትንሽ ይቆጣል ግን ምንም ማድረግ ስለማይችል ቤቱን ወደመስራት ይገባል፡፡››
‹‹እየቀለድሽ አይደለም አይደል፡?››
‹‹እኔ በቤተሰብ ጉዳይ አልቀልድም?››
‹‹መቶ ሺ ብር ብዙ ነው እኮ..?ከየት ታመጫለሽ..?››
‹‹ከዛ የበለጠ ብር አለኝ…እና ደግሞ ካልበቃም…ጌጣ ገጦቼን ብዙ ብር እንደሚያወጡ የነገርከኝ አንተው ነህ…..ቤቱ እንዳለቀ እሱን እንሸጥና የፀጉር ቤት ዕቃዎችንና ማሽኖችን እንገዛበታለን ለሊሴን ሰርፕራይዝ እናደርጋታለን፡፡በዛውም እግረመንገዳችንን የሞች እህትህን ምኞት እውን እናደርግና ነፍሷ ባለችበት አፀደገነት እንድትደሰት እናደርጋለን….ግን እስከዛው ጉዳዩ በእኔ እና በአንተ መካከል ሚስጥር ነው….በል አሁን እግሬን እየጠዘጠዘኝ ነው ወደውስጥ መልሰኝ፡፡››አለችው፡፡
‹‹እሺ..ግን እወቂ በቁሚ እንድቃዥ እያደረግሺኝ ነው…እህቴ በሬዱ ከሞት ተነስታ እያወራች ያለ እየመሰለኝ ነው፡፡››አለና እንዳመጣት አንከብክቦ አቅፎ ወደውስጥ ይዞት ገባ፡፡እሷም ‹‹አዎ ..አሁን እያወራች ያለች እህትህ ነች ..የእሷ ልብ ባይቀይረኝ እኔ እንዲህ አይነት ለሰው አሳቢና ተጨናቂ ሰው አልነበርኩም››ስትል በውስጦ አብሰለሰለች፡፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራ አንድ

ይህቺን ፀሀፊ ልጅ ወዶታት…እሷ እራሷ የመጀመሪያ ደንበኛው ከመሆኗም በላይ ሌላ ደንበኛ አገኝታለታለች፡፡ስልኩን አወጣና ደወለ……አስቴር ጋር…
‹‹እሺ ወንድሜ ደህና ነህ?››
‹‹አለሁልሽ…የላክሻት ልጅ መታለች ልልሽ ነው፡፡››
‹‹እንዴት ነው …ተስማማችሁ?››
‹‹አዎ ጎበዝ ልጅ ትመስላለች››
‹‹ጎበዝ?››
‹‹አዎ ምነው?››
‹‹አይ በአንድ ቀን እንዴት ጎበዝ መሆኗን አወቅክ ?ብዬ ገርሞኝ ነዋ››
‹‹ማለቴ እንዲሁ  ሳያት ተግባቢና ቀልጣፍ ነገር ነች ልልሽ ነው››
‹‹ወንድሜ ፍቅር እንዳይዝህና እንዳትጎዳብኝ…ልጅቷ ፍቀረኛ አላት››
‹‹አይዞሽ አታስቢ አውቃለው፣በዛ ላይ እኔ ማፈቀሪያ ጭንቅላቴ የተበላሸብኝ ሰው ነኝ….››
‹‹ምኑ ነው ምታውቀው?››
‹‹እንዳላት ነዋ››
‹‹ከምኔው?››
‹‹ውይ ኪያ ደግሞ ….በቃ ቸው ማታ ቤት እንገናኝ››
‹‹እሺ ቸው ወንድሜ››በተንከትካች ሳቅ አጅባ ስልኩን ዘጋችው፡፡


////
ወላጇቾ ብቻ ሳይሆኑ ያደገችበትና የእድሜዋን ግማሽ የኖረችበት እቤቷም ጭምር ናፈቃት‹‹ ቤት ማለት..ግን ምን ማለት ነው?ስትል እራሷን ጠየቀችና መልሱን ከአእምሮዋ ውስጥ በርብራ ለማግኘት አይኖቾን ጨፍና ማሰላሰል ጀመረች
‹‹አዎ እቤት ከድንጋይ ወይም ከእንጨት የሚታነፅ የሰው ልጅ መጠለያ ነው።ያንን ህንፃ ከመጠለያነት ወደ ቤትነት የሚቀይረው ግን የታነፀበት ማቴሪያል ጥራትና ውበት አይደለም...ውስጡ ያሉት  ዘመናዊ የቤት እቃዎች እና ውድነትም አይደለም። ህንፃው ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች እርስ በርስ ያላቸው ግንኙነትና የፍቅር ትስስር መጠን ነው ህንፃውን እቤት የሚያደርገው።ለዚህ ነው ከኖርኩበት የተንጣለለ ቪላ ይልቅ አሁን እየኖርኩበት ያለሁት ባለ ሁለት ክፍል ጎስቋላ ቤት የተሻለ የሞሚሞቀውና የሚደምቀው
››መልሱን ለራሷ ሰጠች፡፡ ቀኑን እንዲሁ በሀሳብና በትካዜ ጊዜውን ብታሳልፍም ሲመሽ ግን ሁሉ ነገር የተለየ ሆነ፡፡
ማታ የቤተሰቡ አባል ጠቅላላ ተሰብስበው በሞቅ ደስታ ከወትሮ በተለየ ድግስ መሰል እራት ቀርቦ በመጎራረስ ከበሉና ቡናም ተጠጥቶ ከተነሳ በኃላ በፀሎት ሽንት ቤት ለመሄድ እንድምትፈልግ ለለሊሴ ነገረቻት…ያሰበችው እሷ ደግፋ እንድትወስዳት ነበር…በተቀራራቢ እድሜ ስለሚገኙ እቤት ውስጥ ካሉ ሰዎች ሁሉ እሷን ማዘዝ ወይም ትብብር መጠየቅ ቀላል ይላታል፡ ….ለሊሴ ግን እንዳሰበችው አላደረገችም….
‹‹ወንድሜ በፀሎትን ሽንት ቤት ትወስዳታላህ?››ብላ ስትጠይቀው ክው ነበር ያለችው….እሱ አንደበት አውጥቶ ፍቃደኝነቱን ሳይናገር በቀጥታ ከተቀመጠበት ተፈናጥሮ ተነሳና ወደእሷ በመሄድ ልክ ትናንት ለሊት እንዳደረገው ከስር ሰቅስቆ ልክ እንደህፃን ልጅ አቀፋት….እንዲህ አይነት ሁኔታ በህይወቷ ገጥሞት ስለማያውቅ መደንገጥ ብቻ ሳይሆን እፍረትም ተሰማት…‹‹.ወላጆቹ እንዲህ ሲያቅፈኝ ምን ይላሉ ?››የሚለው ሀሳብ አእምሮዋ ተሰነቀረና ያንን ለማጣራት እይታዋን በቤቱ ዙሪያ ስትሽከረከር ሁሉም በራሳቸው ጫወታ ተመስጠው እርስ በርስ እያወሩ እየተሳሳቁ ነው……አንከብክቦ እንዳቀፋት ይዟት ወጣ
..ቀጥታ ሽንት ቤት ወሰዳና ወደውስጥ አስገብቶ አቆማት…ልክ እንደሌሊቱ ውሀ በሀይላንድ ከቧንቧው ቀድቶ አመጣላትና የሽንት ቤቱን መጋረጃ ወደታች መልሶ ‹‹ስትጨርሺ ጥሪኝ
››ብሎ ከአካባቢው ዞር አለ፡፡

የሽንት ቤት ጣጣዋን ከጨረሰች በኃላ ቀጥታ ወደቤት አይደለም ይዞት የገባው፡፡ልክ እንደለሊቱ ወንበር አመቻችቶ ስለነበር ተሸክሞ ወስዶ አስቀመጣት….‹‹ቀኑን ሙሉ ተኝተሸ ስለዋልሽ አሁን ትንሽ ንፍስ ይንካሽ››
‹‹አዎ ትክክል ነህ፣በዛ ላይ ጨረቃዋም ናፍቃኝ ነበር፡፡››
እሱም ለራሱ መቀመጫ አምቻችቶ ከፊት ለፊቷ እየተቀመጠ‹‹ከጨራቃዋ ጋር ወዳጅ ናችሁ እንዴ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ ለዛውም የእድሜ ልክ››
‹‹ያን ያህል ብቸኛ ነሽ ማለት ነው?››
‹‹እንዴት ከጨረቃ ጋር ለመወዳጀጀት ብቸኛ መሆን የግድ ነው እንዴ?››
‹‹አይ የግድ ባይሆንም ከልምዴ ስነሳ ብዙውን ጊዜ ከጨረቃዋ ጋር ለረጅም ጊዜ የማውጋት ልምድ ያላችው እንቅልፍ አልባ ብቸኛ ሰዎች ናቸው……በተለይ በፍቅር የተሰበሩ››
‹‹እንዴ በፍቅር የተሰበሩ ነው ያልከው..አይ እንደዛ እንኳን አይደለም…..ባይሆን እንዳልከው ከቤተሰብ ጋር በተያያዘ በሚፈጠር ብቸኝነት ብንለው የተሻለ ነው..የፍቅር ጉዳይማ ቢሆን በምን እድሌ..ፍቅር እኮ በጣም ምርጥ ነገር ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ… ፍቅር በጣም ወሳኝ ስሜት ነው….አንድ ሰው ሩሚን ‹‹ፍቅር ምንድነው?››ብሎ ጠየቀ።ሩሚም ..‹‹ፍቅር ምን እንደሆነ ትክክለኛ ትርጉሙን ልታውቅ የምትችለው ውስጡ መጥፋት ስትችል ነው።›› ብሎ መለሰለት…..፡፡
‹‹አዎ ትክክለኛ አባባል ይመስለኛል….ፍቅር የምትተነትነውና የምታወራው ነገር አይደለም፣ፍቅር ኖረህ የምታጣጥመው የተቀደሰ ስሜት ነው….በፍቅር መጥፋት ጥሩ አባባል ነው››
‹‹አይ ጥሩ…ለማንኛውም ለደቂቃም ቢሆን እስቲ ከጨረቃዋ ጋር ብቻችሁን ልተዋችሁ…. መጣሁ›› ብሎ ተነስቶ ወደቤት ገባ..እሷ አይኖቾን ወደላይ አንጋጠጠች…ሰማዩ ጥርት ብሎ ይታያል ፡፡ጨረቃዋ ሙሉ ክብ ሆና ደፍናለች..ዙሪያዋን የተበተኑና ከዋክብቶች ብልጭ ድርግም እያሉ ይታያሉ…አናትና አባቷ ትዝ አሏት..ይሄኔ የእሷን መጥፋት ምክንያት በማድረግ የመጨረሻውን ጥል እየተጣሉና የመጨረሻ የተባለውን አንጀት በጣሽ ስድብ

እየተደሰዳደብ እንደሆነ በምናቧ አሰበችና ሙሉ ሰውነቷ ሽምቅቅ አለባት..ሰውነቷ ሲሸማቀቅ ደግሞ የእግሯ ሆነ የፊቷ ጥዝጣዜ ህመም ተቀሰቀሰባት….
ድንገት የሰማችው ድምፅ ነው ከሀሳቧ ያባነናት…..ያልገመተችውን ነገር ነው እያየች ያለችው..ፊራኦል ፊት ለፊቷ ቅድም የነበረበት ቦታ ቁጭ ብሎ ክራር እየከረከረ የሙሀመድ አህመድን የትዝታ ሙዚቃ ያንቆረቁራል….ፍዝዝ ብላ በፍፁም ተመስጦ ታዳምጠው ጀመር፡፡
ስንቱን አስታወስኩት…ስንቱን አስብኩት ልቤን በትዝታ ወዲያ እየላኩት
አንዴ በመከራ …አንዴ በደስታዬ ስንቱን ያሳየኛል ..ይሄ ትዝታዬ በድምፁ ድንዝዝ ብላ ጠፋች………… የትናንቱ ፍቅር ….ጣሙ ቁም ነገሩ ምነው ያስተዋሉት ያዩት በነገሩ
ሁሉም እንደገና ኑሮን ቢያሰላስል አይገኝም ጊዜ ያኔን የሚመስል፡፡
ዘፈኑን ሲጨርስ‹‹አንተ..አንድ ሺ አመት በዚህ ምድር ላይ ኖረህ ከዛሬ 500 ዓመት በፊት ያለውን ጊዜ ናፍቀህ የምትተክዝ እድሜ ጠገብ አዛውንት ነው የምትመስለው፡፡››የሚል አስተያየት ሰጠችው፡፡
‹‹ያን ያህል?››
‹‹አዎ …ድምፅህ በጣም ግሩም ነው….ሙዚቃ ትሰራለህ እንዴ?››
‹‹አይ ያን ያህል እንኳን ሰራለሁ ማለት አልችልም …በፊት በፊት ቀበሌ ኪነት ከጓደኞቼ ጋር እሞክር ነበር አሁን ከህይወት ሩጫ ጋር አብሮ እልሄድ አለኝና ተውኩት፣እንዲህ አንደዛሬው ጨረቃዋ ሙሉ ስትሆን እንዲህ እቀመጥና ለእሷ አዜምለታለው፡፡››

‹‹እንዴ..ለእኔ የዘፈንክልኝ መስሎኝ ውስጤ በደስታ ተፍነክንኮ ነበር ..ለካ ለጨረቃዋ የተዘፈነውን ዘፈን ነው ሳይፈቀድልኝ የሰማሁት…..››
‹‹አይ እንደዛ አንኳን ለማለት አልችልም…የዛሬው ዘፈን ቀጥታ ላንቺ ነው..ምስጋናና ይቅርታ ለመጠየቅ፡ ብዬ ነው የዘፈንኩት፡፡››


ሰው በጎደለበት ቦታ ሟሟያ ሳይሆን......ሰው በሚያስፈልግበት ቦታ ተፎካካሪ ሴት ሁኚ❕

🙏

  
Sabawit ✨


ጋዜጠኛ፦ ቀጣይ ህይወትን እንዴት መኖር ትፈልጋለህ?

ቡኮውስኪ፦

“በሚቀጥለው ሕይወቴ ድመት መሆን እፈልጋለሁ። በቀን 24 ሰአታት ለመተኛት እና ያለምንም ስራ ለመመገብ ከዛ ቂጤን እየላስኩ መቀመጥ..”

ጋዜጠኛ፦ ሰዎች በተመሳሳይ ህይወት ድብርት ውስጥ ወድቀዋል። ለዚህ መፍትሔ አለ ብለህ ታስባለህ?

ቡኮውስኪ፦

“ተመሳሳይ ህይወት አሰልቺ ነው። የዕለት ተዕለት ተግባራችሁን ለመቀየር ሞክሩ፤ ለምሳሌ ቲቪ ላይ ተቀምጣችሁ ሶፋውን ተመልከቱት።” 🤗


አለመሳቅ እኮ ይቻላል...
-----------------------


አለመሳቅ እኮ ይቻላል -
አለማልቀስ ነው ጭንቁ፣
የመንፈስን እንጉርጉሮ -
በመንፈስ እምባ ማመቁ፣

ውስጥ ውስጡን እየደሙ -
በቀቢፀ ተስፋ መድቀቁ፣
ለተስለመለመች እውነት -
የደም ደብዳቤ ማርቀቁ፣

በቅሬታ ሰደድ እሳት -
ህዋሳትን መጨፍለቁ፣
አለመሳቅ እኮ ይቻላል -
አለማልቀስ ነው ጭንቁ።

    
- ደበበ ሰይፉ

   


ገባ….፡፡የተዝረከረኩ ነገሮችና የተቀዳደቁ ወረቀቶችን አነሳሳና አስተካከለ…ቢሮው ሁለት ክፍል ሲሆን የመጀመሪያውን የፊት ለፊቱን በመተው ወደ ውስጠኛው አለፈና ወንበሩ ላይ ተመቻችቶ ተቀመጠ፣ሌላ ነገር ለማሰብ ከመጀመሩ በፊት በራፉ ተቆረቆረ…..ድምፀን ከፍ አድርጎ ከመቀመጫው እየተነሳ ወደፊት ለፊቱ በራፍ እየተራመደ ‹‹ይግቡ ››አለ.. በራፉ በስሱ ተከፈተና አንድ አንገተ መቃ ጠይም ወጣት ታየችው….ሙሉ በሙሉ ከፍታ ወደውስጥ ገባች….፡፡ስሯ ደረስና እጁን ለሰላምታ ዘረጋ፡፡
‹‹ሰለሞን ገብረየስ›› እባላሁ፡፡
‹‹ለሊሴ ለሜቻ ›› ስሟን አስተዋወቀችውኝ፡፡
‹‹ግቢ ››አለና ወደ ውስጠተኛው ክፍል እመራ.. ዞሮ ወንበሩ ላይ ተቀመጠና ከፊት ለፊቱ እንድትቀመጠ ጋበዛት..ተቀመጠች፡፡

‹‹እሺ ምን ልታዘዘዝ…?እዚህ ቤት ውስጥ ያለነው እኔና አንቺ ብቻ ነን..እዚህ የምንነጋገርነው ነገር እስከመጨረሻው በእኔና አንቺ መካከል ሚስጥር ሆኖ ተቀብሮ የሚቀር ስለሆነ ሁሉንም ነገር ያለምንም መሳቀቅና ይሉኝታ ንገሪኝ …ከዛ መፍትሄ እንፈልጋለን….››
የልጅቷ አይኖች ፈጠጡ….ግራ በመጋባት ..‹‹‹ይቅርታ….እህትህ ነች የላከችኝ፡፡››አለችው
‹‹እህትህ የእኔ ?ለምን፡፡››ግራ መጋባቱ የእሱ ተራ ሆነ.፡፡
‹‹ፀሀፊ ይፈልጋል ብላኝ ነው››
‹‹ኦ……ገባኝ››የንዴት ሳቅ ሳቀ፡፡
ባልጠበቀችው ሁኔታ ቀጥታ ወደገደለው ገባላት‹‹እሺ እንደዛ ከሆነ ጥሩ፣ስራ መች መጀመር ትችያለሽ?››
‹‹ነገ››
‹‹ጥሩ በቃ››
‹‹በቃ…ማለቴ ሌላ የምትጠይቀኝ ነገር የለም?››
‹‹እኔ እንጃ ምን እጠይቅሻለው…..?አንቺ የምትጠይቂኝ ጥያቄ አለሽ?››
‹‹አዎ… ስንት ትከፍለኛለህ?››
‹‹ስንት እንድከፍልሽ ትፈልጊያለሽ?››
‹‹አራት ወይም አምስት ሺ ብትከፍለኝ ደስ ይለኛል፡፡››
‹‹ለመጀመሪያ የሶስት ወር የሙከራ ጊዜ አራት ሺ ብር ከፍልሻለው…ከዛ በኃላ ደግሞ አብረን እናየለን….ሌላ ይያቄ አለሽ …?››
‹‹የለኝም፡፡››
ኪሱ ገባና ቁልፍ መያዣውን አውጥቶ ከውስጡ የቢሮውን ትርፍ ቁልፍ አወጣ‹‹.ይሄው የቢሮ ቁልፍ..የስራ መግቢያ ሰዓት 2.30 ነው….ነገ ስመጣ ቢሮ ከፍቶ መግት አይጠበቅብኝም ማለት ነው?፡፡››አላት፡፡

‹‹አዎ ትክክል ››አለችና ቁልፉን ይዛ ለመሄድ ተነሳች፡፡
‹‹ይቅርታ ነገ ሰራተኛ ሆኜ ስራ ከመጀመሬ በፊት ዛሬ እንደ ደምበኛ አገልግሎት ማግኘት እችላለሁ…?.››
ጥያቄዎ አስደምሞት በትኩረት አያት፡፡‹‹ቁጭ በይ›› አላት፡፡ተመልሳ ቁጭ አለች፡፡
‹‹እሺ እየሰማሁሽ ነው፡፡››
‹‹የጋብቻ ጉዳይ ሳይሆን የፍቅር ጉዳይ ነበር››
‹‹ገባኝ››
‹‹ሁለት አፈቀርንሽ ብለው እንዳገባቸው እየጨቀጨቁኝ ያሉ ወንዶች አሉ…ከሁለቱም ጋር ከሁለት አመት በላይ እውቂያ አለኝ፡፡አንዱ የተማረ እስማርት የሚባል የመንግስት ሰራተኛ ነው…የመንግስት ሰራተኛ ነው ስልህ ያው ይገባሀል አይደል…ከወር እስከ ወር ያለውን ወጪ ለመሸፈን የሚቸገር አይነት ሰው ነው..ሁለተኛው ነጋዴ ነው…ደህና ድርጅት አለው
….ሁለቱም እንዳገባቸው ጠይቀውኛል ..የትኛውን እሺ ማለት እንዳለብኝ ግራ ተጋብቻለው…..እንዴትና በምን አይነት መስፈርት ነው መምረጥ የምችለው?››
‹‹የትኛውን ይበልጥ የምትወጂው ይመስለኛል…?››
‹‹እኔ እንጃ ከመንግስት ሰራተኛው ገር ስሆን በጣም ዘና እላለሁ..ቀልዶቹ ያስቁኛል
….ነጋዴው ደግሞ የፈለኩት ቦታ ወስዶ ያዝናናኛል..ጥሩ ጥሩ ስጦታ በመስጠት ያስደስተኛል….ግን ንግግሩ ደረቅና የጠነዛ ነገር ነው…ግራ ተጋብቻለው…አንዳንዴ ሁለቱ ተጨፍለቀው አንድ ሰው ቢሆኑና እሺ ብያቸው በተገላገልኩ እላለው፡፡››
ለተወሰነ ደቂቃ አሰበና መናገር ጀመረ‹‹እንግዲህ ይህንን ችግርሽን ለመፍታት ሶስት ወር የተከፋፈለ የቤት ስራ እስጠሸለሁ፡፡
‹‹ሶስት ወር ሙሉ አልበዛም?››
አይ አልበዛም…ለእድሜ ልክሽ አብሮች የሚኖረውን ሰው እኮ ነው የምትመርጪው
….ፍቅረኛ ብቻ ሳይሆን የዕድሜ ልክ ባልሽን ነው የምትመርጪው…   ጓደኞችሽ እና

ወዳጆችሽ ፊት ይዘሽው ምትሄጂውን ሳይሆን ከቤተሰቦችሽ ወስደሽ ምትቀላቀይውን ሰው ነው የምትመርጪው….እና ደግሞ ያንቺን ባል ብቻ ሳይሆን ነገ ለምትወልጃቸው ልጆችም አባት የሚሆነውን ሰው ነው እየመረጥሽ ያለሽው፣እና እዚህ ጉዳይ ላይ ሶስት ወር አይደለም ሶስት አመትም ብታሳልፊ እንደብክነት የሚቆጠር አይደለም…..ግን እንዲህ ስልሽ ይሄን ሁሉ አድርገንም ይንን ሁሉ ጊዜ አባክነንም ፍፅም ትክክለኛውን ሰው መምረጥ እንችላለን ለማለት አይደለም….የፍቅር  ጓደኛ በመምረጥ ሂደት ውሥጥ ፍጽም ትክክል የሚባል ምርጫ የለም…ግን በብዙ መስፈርት ሲለካ የተሻለውን መምረጥ እንችላለን..እና ለዛ ሶስት ወር አይበዛም፡፡
‹‹አሳምነሀኛል…የማደርገውን ንገረኝ፡፡››አለችው፡፡
በመጀመሪያ ወር አንደኛውን ምረጪና ከእሱ ጋር ብቻ ተገናኚ…ሌላውን የሆነ ምክንያት ስጪውና ሙሉ በሙሉ ግንኙነት አቋርጪ…. በስልክም ቢሆን አታግኚው፣ፎቶውንም ቢሆን እንዳትመለከቺ ….ሙሉ ትኩረትሽን አንደኛው ላይ ብቻ አድርጊ….ልክ ወሩ ሲያልቅ ይሄኛውን በተመሳሳይ ከግንኙነት ውጭ አድርጊውና ከሌለኛው ጋር ተገናኚ…በሶስተኛው ወር ደግሞ ሁለቱንም ሳታገኚ ለብቻሽ አሳልፊ፣ስለሁለቱም በጽሞና አስቢ …ከዛ አብረን እናወራበታለን፡፡››
‹‹ጥሩ ይመስላል ..አዎ እንዳልከኝ አደርጋለሁ…..አዎ እንደዛ ባደርግ ጥሩ ይመስለኛል….ግን በጣም የተቸገረች ጓደኛዬ ነበረች..ምን የመሰለ ትዳሯ ሊፈርስባት ነው…እባክህ እርዳት ቆይ እንደውም ልደውልላለት..››አለችን ስልኳን አንስታ እየደወለች መቀመጫዋን ለቃ ወደውጭ ወጣች፡፡
ሰሎሞን‹‹ዋው የመጀመሪያ ኢትዬጵያዊት ደንበኛዬን ኢንፕረስ አደረኳት ማለት ነው…››ሲል አሰበና .ደስ አለው ..፡፡
ስልክን አናግራ ተመልሳ መጣች…‹‹ጓደኛዬ ነገ መምጣት ትችላለች..?እባክ ችግሯ በጣም አጣዳፊ ስለሆነ እንደምንም ጊዜህን አሸጋሽገህ አግኛት፡፡››ተለማመጠችው፡፡
‹‹ነገ ምንም ደንበኛ የለኝም በፈለግሽው ሰዓት ቅጠሪያት››
‹‹አመሰግናለው…አራት ሰዓት ትመጣለች..በቃ ቸው..ጥዋት እንገኛን ››ብላ ለመሄድ መንገድ ከጀመረች በኃላ ወደኃላ ዞራ..‹‹ይቅርታ ክፍያውን ዛሬ ስላላያዝኩ ነው…..ነገ ይዤ መጣለው››
‹‹ችግር የለውም…ሲሳካ ምሳ ትጋብዢኛለሽ ››አላት

‹‹አመሰግናለው››ብላ በደስታ እየሳቀች ወጥታ ሄደች፡፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስር

ሀሳቧን ሳትጨርስ ፊራኦል ከውጭ ስልኩን እየጎረጎረ መጥቶ ፊት ለፊቷ ቁጭ አለ…ለረጅም ደቂቃዎች አላናገራትም …
‹‹ይሄን ያህል ምን ቢመስጥህ ነው?››
‹‹ባክሽ የድሮ መስሪያ ቤቴ..ማለቴ ቆርቆሮ ፋብሪካ ምናምን ብዬ አውርቼሽ ነበር አይደል?››
‹‹እ..ስለምትናፍቅህ ልጅ እያወራኸኝ ነው?››
‹‹አዎ ..ትክክክል?››
‹‹እና እሷ ምን ሆነች?››

‹‹እባክሽ ጠፋች…አንድ ብቸኛ ልጃቸው ጠፋችባቸው…ከዛሬ ነገ አገኛታለሁ ብዬ ስቃትት የእህቴንም ልብ ይዛ ጠፋች››
‹‹ጠፋች ማለት?››
‹‹እኔ እንጃ ..ዛሬ ሶስተኛ ቀኗ ነው…ማህበራዊ ሚዲያው ሁሉ ስለእሷ ነው የሚያወራው››
‹‹ስለጠፋች ብቻ?››
‹‹አዎ አባትዬው ያለችበትን ለጠቆመ 5 ሚሊዬን ብር በሽልማት መልክ እክፍላለሁ ብሎ ስላሳወጀ ምድረ ድርዬ ጠቅላላ መንገድ ላይ ያገኞትን ወጣት ሴት ሁሉ እያስቆሙ ከእሷ ፎቶ ጋር ማስተያያት ጀመረዋል፡፡››
‹‹እየቀለድክ መሆን አለበት?››
‹‹እውነቴን ነው…አታይውም እንዴ..?››ብሎ ስልኩን አቀበላት… ማህበራዊ ሚዲያውን የተቆጣጠረውን ሁለት ሶስት ፎቶዋን አየች…ውስጧን በረዳት…ግማሽ ፊቷ በፋሻ የተሸፈነ ቢሆንም አስተውሎ ያያት ሰው ሊለያት ይችላል…ፊቷ የተቀመጠው ፊራኦል እስከአሁን እንዴት እንዳለያት ተደንቃለች፡፡
ስልኩን መለሰችለት‹‹ምን ሆና ይሆን …..?የሀብታም ልጅ ነገር ይሄኔ ቀብጣ ሊሆን ይችላል?››ስትል አፏ ላይ እንደመጠላት ተናገረች፡፡
‹‹አይ እንደዛ እንኳን ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም…እሷ የሀብታም ልጅ ስለሆነች ነገሩ ጮኸ እንጂ በየቀኑ እኳ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች እዚህም እዛም ከያሉበት ተወስደው የሚጠለፉበት…በሰው ሚሊዬን ብር የሚጠየቅበት ሀገር ነው እኮ ያለነው….ስንቶች የተጠለፈባቸውን ልጃቸውን ወይም ባላቸውን ለማስመለስ ቤታቸውን ሸጠዋል…?ስንቶች የመኪናቸውን ሊቭሬ አስይዘው አራጣ ተበድረዋል….?.ንብረቱን አሟጦ ሸጦ ከከፈለስ በኃላ ስንቱ ሬሳ ተልኮለታለል…….እዚህ አገር በዚህ ጊዜ እየሆኑ ያሉትን ነገሮች እንኳን ለማውራት ለማሰብም ይከብዳ…እና ይህቺ ልጅ ምን እንደገጠማት ማንም የሚያውቅ የለም….፡፡››
‹‹እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን አላውቅም››

‹‹እንዴ!! ሀገር ውስጥ እየኖርሽ አልነበረም እንዴ…..?ክፍለሀገር ያለች የእናቱን ሞት ሰምቶ ሄዶ መቅበር ያልቻለ ስንት አለ….?ዘመድ ከዘመድ ከተቆራረጠ እኮ ቆየ፣ስንቱ የትውልድ አካባቢውን ሄዶ ለማየት ልክ እንደአውሮፓና አሜሪካ እንደመሄድ ከባድና የማይቻል ሆኖበታል…እና የዚህች ልጅ ቤተሰብ ጭንቀታቸውን ተመልከቺ…ስንቱን ያስባሉ… እህቴ ብትሆንስ ብዬ ሳስብ ዝግንን ይለኛል…እንደውም በቀደም የሰማሁትን ታሪክ ላጫውትሽ…››
በጉጉት ትኩረቷን ወደእሱ አቅንታ‹‹እሺ እየሰማሁህ ነው..››አለች ፡፡
ከአስር ወራት በፊት አዳማ አካባቢ ካለ አንድ የጠበል ቦታ ታጣቂዎቹ ድንገት ይመጡና የተወሰኑ ሰዎች አፍነው ይወስዳሉ፡፡ከተወሰዱት ውስጥ አንዱ ከአርሲ አካባቢ ነው የመጣው…የተጠየቀውን ብር ወላጆቹ በቀላሉ ማሟላት አይችሉም ቢሆንም ተለምኖና ከየሰው ተለቃቅሞ ከተጠየቀው ሩቡን ያህል ብር ለታጣቂዎች ይላክና የልጁ መለቀቅ ይጠበቃል..ግን ከዛሬ ነገ ይመጣል ሲባል ወራቶች ያልፋሉ፣..እናት እንቅልፍ ታጣለች…ቀንና ለሊት ማልቀስ ይሆናል ስራዋ…ልጇ ይኑር ይሙት የምትጠይቀው ሰውና የምታጣራበት መንገድ አልነበራትም…በመጨረሻ ሰው መፍትሔ ያለውን ይነግሯታል…የሞተ ሰው ነፍስ ጠርተው የሚያናግሩ ሰዎች ጋር ይዘዋት ይሄዳሉ…እንደተባለውም የልጇ ነፍስ ሲጠራ ይመጣል..‹‹አዎ እማዬ እኔ ልጅሽ ከሞትኩ 6 ወር አልፎኛል….እርምሽን አውጪ ይላታል››እናትም ወደቤቷ ተመልሳ ድንኳን ጥላ የልጇን እርም ታወጣለች…ዘመድ አዝማድ ሁሉ ለቅሶ ደርሶ እርማቸውን ያወጣሉ..በጣም የሚገርመው ምፀት ደግሞ ምን መሰለሽ እሷን ለቅሶ ለመድረስ ከሚመጡት የቅርብ ዘመዶቾ ውስጥ ሶስቱ ዳግመኛ በታጣቂዎች ተጠልፈው አረፉት፡፡››
ንግግሩ ይበልጥ ሆድ እንዲብሳት አደረጋት..እንባዋን ሊዘረገፍ ሲተናነቃት ተሰማት..
እሱ ንግግሩን ቀጠለ…‹‹አባዬ ይሄንን ባይሰማ ደስ ይለኛል…ከሰማ በጣም ነው የሚያዝነው….እሷን ሰፈራቸው ድረስ እየሄደ ከመኪና ስትወርድና ከቤት ስትወጣ እንደሚያያት አውቃለው…ልጄን በውስጧ ይዛለች..እሷን ሳያት ልጄ በከፊልም ቢሆን በህይወት እንዳለች ይሰማኝና እፅናናለው ይላል…ይገርምሻል እኔ እራሱ እንዲዚህ እንዳስብ ተፃዕኖ ያደረገብኝ እሱ ነው››

‹‹ይገርማል ….ግን ጋሼ ምን በሩቅ አሳያቸው ማለቴ እቤት ገብተው ቢያዮት እኮ ሰዎቹ የሚቃወሙ አይመስለኝም፡››
አዎ እንዳልሽው አይቃሙም ይሆናል..ግን አባዬ እኛን ፊት ለፊታቸው ካዩ ይሳቀቃሉ…ልጅቷ ፊት ከቀረብን ማልቀሳችን አይቀርም.. እሷ ፊት ማልቀስ ማለት ደግሞ ልጅቷ ልክ በሌላ ሰው ህይወት እንደምትኖር እንድታስብ ማድረግና ልጅቷን መጉዳት ነው….ሁላችንም ከእሷም ሆነ ከቤተሰቡ በስህተት እንኳን መገናኘት የለብንም ብሎ ቁርጥ ያለ ትዕዛዝ ለሁሉም አስተላልፏል…እኔንም ከዛ ፋብሪካ ስራዬን ጥዬ እንድወጣ ያስገደደኝ በዛ ምክንያት ነው፡፡አሁን አሁን ግን ያንን የእሱን ትዕዛዝ ለመጠበቅ እየተቸገርኩ ባለሁበት ሰዓት ነው…ይሄው አንደምታይው ልጅቷ የጠፋችው…››
‹‹‹በቃ ደከመኝ መሰለኝ ትንሽ ልተኛ ››ብላ አልጋ ልብሱን ወደላይ ሳበችና ሙሉ በሙሉ ተሸፈነችና ..በፀጥታ እንባዋን ዘረገፈች…አባትና እናቷ አሳዘኗት….ቢሆንም ለአመታ ያበሳጮትን ብስጭት ልትረሳላቸው አልቻለችም….በውሳኔዋ ፀንታ እስከመጨረሻው መቆየት እንዳለባት ዳግመኛ ወሰነች፡፡‹‹አዎ አሁን እያዩት ያሉት ስቃይ ይገባቸዋል››በማለት በረጅሙ ተነፈሰች፡፡ ////
ሰለሞን በሶስተኛው ቀን አርፍዶ ሶስት ሰዓት አካባቢ ወደቢሮ እየሄደ ሳለ ስልኩ ጠራ…የማያውቀው አዲስ ቁጥር ነው…አነሳው፡፡
‹‹ኪያ የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ ነው፡፡››ድርጅቱን ኪያ ብሎ የሰየመው አስቴርን ለማስደሰት ስለፈለገ ነበር…አስቴር እናቷ ከመሞታቸው በፊት ‹‹ኪያ ›› እያሉ ነበር የሚጠሯት እሱም አልፎ አልፎ ይሄንን ስም ይጠቀማል…ድርጅት ለመመስረት ሲያስብ ግን ወዲያው በምናብ የመጣለት ስም ይህ ኪያ የሚለው ስም ነው፡፡እንደምንም ብሎ አግብቶ ከእሷ ጋር አንድ ቤት መኖር ሲጀምሩ ደግሞ ሙሉ በሙሉ በወጥነት ኪያ የሚለውን ስም ይጠቃማል..ሚስቱም ሆነ ድርጅቱ በአንድ ስም ይጠራሉ…ይህ ነው እቅዱ፡፡

ሴሎቹ ሁሉ ተነቃቁ…‹‹በስተመጨረሻ ተሳካ…በስተመጨረሻ የመጀመሪያ ደንበኛዬን አገኘሁ….‹‹ሰሎሞን ጀግና ነህ፣›››ብሎ ተደሰተና ድምፁን ጎርነንና ሻከር አድርጎ፡፡‹‹አዎ ትክክል ኖት..ምን ልታዘዝ?፡፡››ሲል መለሰ፡፡
‹‹እባኮት የቢሮዎትን ትክክለኛ አድርሻ ላስቸግሮት…?››
‹‹ሜክሲኮ ኬኬር ህንጻ 3ተኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 102 ፡››
‹‹አመሰግናለው ..ከ15 ደቂቃ በኃላ ደርሳለሁ›› ስልኩ ተዘጋ፡፡
እሱ ደግሞ ቢሮ ለመደርረስ 5 ደቂቃ ብቻ ነው የሚቀረው.. ‹‹ቢያንስ የመዘጋጃ 10 ደቂቃ ይኖረኛል›› ሲል አሰበ…‹‹ ደንበኛዬ መጀመሪያ የምትፈልገውን ምክር ሆነ ማንኛውንም አገልግሎት በነፃ ነው የምሰጣት ..ክፍያ አልቀበልም….››ሲል ወሰነ ፡፡መልሶ ደግሞ ሀሳቡን ቀየረ‹‹አይ እንደዛማ አይሆንም….የእኛ ሰው ላልከፈለበት ነገር የሚሰጠው ዋጋ ትንሽ ነው….ምክሬን ከልቧ ሰምታ ተግባራዊ ለማድረግ የምትሞክረው ገንዘብ ካወጣችበት ብቻ ነው….ስለዚህ ተመጣጣኝ የሆነ ክፍያማ ላስከፍላት የግድ ነው…አዎ የተወሰነ አስከፍላታለው.፡፡››ሲል ውሳኔውን አሻሻለ፡፡.ቢሮው ደረስና ከፍቶ


አንዳንዱ ጋር  ቸኩዬ አንዳንዱ ጋ ፈጥኜ ዋጋ ከፍያለሁ ።
አንዳንዱ ጋር ጥጋቤ አንዳንዱ ጋ ትህትናዬ አስገምቶኛል።
አንዳንዱ ጋር መጠየቄ አንዳንዱ ጋ ዝምታዬ ጥያቄ አስነስቷል። አንዳንዱ ጋር ጥንቃቄ አንዳንዱ ጋ ግዴለሽነቴ አስመርምሮኛል ።
አንዳንዱ  ጋር ጨዋነቴ አንዳንዱ ጋ ብልግናዬ ረብሿል።
አንዳንዱ ጋር አማኝነቴ አንዳንዱ ጋ አህዛብነቴ አጠያይቋል። 
አንዳንዱ ጋር  ቸርነቴ አንዳንዱ ጋ ስስቴ አስገርሟል
!!


ከበአል ድባብ ሁሉ የላቀው - ቅርጫ እና ስርአቱ

👇🏾

እምነት እና ሃቅ - መዳቢው የመደበልህን አምነህ መሄድ
.
ሰው እና ትስስር - ከእገሌ ጋር ቅርጫ አለኝ የማለት ትስስር
.
አብሮ መብላት እና መቋደስ - አብሮ መብላት መጠጣቱ

👇🏾

እንኳን አደረሳችሁ !!!


አባቴ ካጠገቡ የማትጠፋ ራዲዮ ነበረችው። ኹለት ስፒከር አላት ካሴትም ታጫውታለች...

ፀሐይ በራኺን አስሬ ይሰማታል። አክስቴ ትመስለኝ ነበር፤ ድምጿ እኛ ቤት አይጠፋም ስትዘፍን እኩል እላለሁ ከሙዚቃው ጋር...

"መጀመርታ ፍቅሪ
ኣብ መን ተጀመረ
ኣዳምን ሔዋንን
አለም ምስተፈጥረ
ኣነ ከይፈለጥኩ
አብ ልበይ ሐደረ
እንታይ እሞ ክገብር
ዕድለይ ካብ ኮነ አይ..አይይ*

አባቴ ወታደር ነበር። ጠይም ነው መከፋቱ ፊቱ ላይ ብዙ አይታይም፤ ማጣቱ በየምክንያቱ አንደበቱ ላይ አይንፀባረቅም ....ዝምም ይላል

ረጋ ያለ ነው ።

ጥርሱን ሳያሳይ  ነው ደስ ብሎኛል ፈገግታ ፈገግ የሚለው፤ ተገርሜያለሁ ፈገግታ ፈገግ የሚለው ተበድያለሁ ፈገግታ ፈገግ የሚለው   አጠገቤ ሲሆን እረጋጋለሁ።

ሰሞኑን ሰውነቴ እንደከሳ፤ ፊቴ ማዘን እንደታከከው፤ ድብርት ነገር እንዳንጃበበብኝ አወቀ።  አባትም አይደል? ንብረቱም አይደለሁ? ዋጋ ከፍሎብኝም የለ?

ፊቴን አይቶ "ደህና ነህ ህሉፌ ...?" አለኝ።

'እ ...ትንሽ ደከመኝ...
አሻግሬ ማየት እያቃተኝ... ቶሎ ቶሎ እጅ  እየሰጠው ..." አልኩት።

ረጅም ሰዓት ዝም አለ ...

"ታስታውሳለህ በረሃ እያለሁ የምፅፍላችሁ ደብዳቤ፤ በርቱልኝ፥ ምን ጎደላችሁ፥ እወዳችኋላሁ፥ በቅርብ እደውልላችዋለሁ፥ እመጣለሁ፥ ዓይነት ይዘት ያለው ፅሁፍ ?! ።"

"ባሩድ እየሸተተኝ ነበር፥ አብሬው የዋልኩት ጓደኛዬ ሞቶብኝ፥ ፍንጣሪ ጥንት መ'ቶኝ፣ ጠላት ሊፈጀን እያቀደብን፣ ጀኔራላችን ምሽግ ሰብራችሁ ግቡ ሊለን እንደሚችል እያወቅን፥ የተቀበረ ቦንብ ልንረግጥ እንደምችል እያወኩ፥ ከአውሮፕላን የተወረወረ ፈንጅ ሊያወድመን እንሚችል እያወኩ፥ ነበር...አሻግሬ ተስፋ የማየው..."

ፋታ ወስዶ ቀጠለ...

"ልጆቼን እንደማገኛቸው፥ አባት እንደምሆንላቸው፥ ሚስቴን ዳግም እንደማገኛት ፤ቤተክርስትያን እንደምሳለም የፈንጂ  ድምፅ ሳልሰማ እለት እለት የወደቀ ሬሳ ሳልሻገር እንደምኖር ተስፋ አደርግ ነበር ...

ስለመግደል የሚታቀድበት ስፍራ ላለመሞት የሚዘየድበት  ቦታ አንድ ቀን እንደማልኖር አምን ነበር ...!

ተስፋን ሙጥኝ ብዬ ነው ዛሬን ያየሁት ። ያጋጠመኝን መውደቅ እና ሃዘን ህመም ችላ ብዬ ነው ያን በርሀ የተሻገርኩት !!

አጆኻ ዝወደይ ..
ሁሉም ሰው መስቀል አለው ልዩነቱ አይነቱ እና  አሸካከሙ ነው !!"
    


😊😊 🥰ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ  እንኳን ለመድኃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ልደቱ በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ
መልካም በአል ይሁንላችሁ❄️💐🎄💐🎄💐🎄

merry Christmas for your and your beloved family🔔🔔


ከረጅም ግዜ በኃላ ፍሬንዴን አገኘሁት። ፈታ ያለ ነው። ሳቅ ያበዛል ሰላምታ ሲሰጥ እቅፍ አደርጎ ነው።

ያቆላምጣል ...

ሲስቅ አይኑ፥ ጥርሱ፥ ጉንጩ ቅይር ይላል። እሱን ማግኘት Energy ይሰጣል ።

ከዓመት በኋላ ሳገኘው '...ባክህ ፋዘርም ብራዘርም ደየሙብኝ.. በተከታታይ...' አለ።...ትክ ብዬ...በመደናገጥ አየሁት።

'ቤትም ሱቅም ወረስኩ ... በልጅነቴ ኪራይ ሰብሳቢ ሆንኩልህ...' ብሎ ሌላ ሳቅ ለቀቀ።

እንዳንድ ሰው ቀለል የሚያደርገው ነገር አገራረሙ ..

ሌላ ቀን ሌላ ቦታ እየሄድን...

"የሞተ ሰው በአይንህ አይተህ ታውቃለህ?" አልኩት።

'አባቴ ድንገት ታሞ ተሯሩጠን ከወንድሜ ጋ ሆስፒታል ወሰድነው አልቆየም ነርሷ ሞተ አለቺኝ እንዲ አትበይ ተይ ተይ ተይ አልኳት...
ያልነገርኩት ነገር አለ ተይ አልኳት...ተይ ደስ የሚለውን በልደቴ ቀን እነግረዋለሁ ብዬ ያቆየሁት ነገር አለ ተይ ሞተ አትበይ አልኳት...'

ያለቺው ነበር የሆነው።

'እኔና ከወንድሜ ከነርሷ ጋር በጋራ ሆነን ገነዝነው።'

'እምባ እየከለለኝ እጄ አልታዘዝ እያለ እኔ ነኝ ለቀብር ያበጃጀሁት...

ልጨምርልህ...?!

ፈገግታው በእንባ ተቀይሯል፤ ድምፁ ሳግ አለው፤ ዐይኑ እምባ ተሞልቷል...

'አባቴ በሞተ በሰባት ወር ወንድሜ እጄ ላይ ነው የምተው። ወደቀ ተብዬ ስጠራ ስበር ደረስኩ ያኔ ነብሱ አልወጣችም ነበር እንዳቀፍኩት፥ እየጠራሁት፥ አይዞህ እያልኩት፥ ውኃ አምጡ ላፍስስለት እያልኩ እጄ ላይ ሞተ...።'

ከእማማ እልፍኝ ጋ ሆኜ ገነዝኩት...

'ታላቄን የሚቆረቆርልኝን ገነዝኩት። ዐይኑ፥ ገላው፥ በድን ሲሆን አየሁ ...አብሮ አደጌን አንድ ወንድሜን ቀበርኩት...'

'ከዓለም ተኳረፍኩ። ጠዋት ማታ ዊድ ነፋሁ፤ ወንድሜ አግብቼ እኖርበታለሁ ያለው ቤት፤ አባቴ የሚጦርበት ሱቅ የኔ ሆነ። መጠጥ ውስጥ ተደበኩኝ በዊድ ተከለልኩ።

'ስጋችን እንዴት እንዳስጠላኝ፤ ሰውነት እንዴት እንደደበረኝ፤ ነገ እንዴት እንደቀፈፈኝ፤ ዕቅዴን እንዴት እንደናኩት!!'
.
.
ሳቃችን የከለለው ሃዘን ብዛት !!!

©Adhanom Mitiku


‹‹ይሄንን ካሮት፤ ቆስጣ ፤ስጋ ፤መኮሮን ይሄን ሁሉ በእሷብር ነው የጋዛሽው ››
‹‹አዎ አባዬ››
‹‹እንዴት እንዲህ ታደርጊያለሽ ለሊሴ…?ችግር ላይ ካለች ልጅ እንዴት? ››
‹‹ጋሼ እኔ አስገድጄያት ነው…..ያው ለእኔው እኮ ነው… ደህና ደህና ምግብ ካልተመገብኩ ከስብራቴ ቶሎ አልድንም..ውጌሻዋ ያለችውን አልሰማህም፡፡››
‹‹ቢሆንም ..ይሄው እኔ እኮ ለአስቤዛ የሚሆን ብር ይዤ መጥቼለው ››አሉና እጃቸውን በወደኪሳቸው ሰዳው የተወሰኑ ድፍን ብሮችን አውጥተው ዘረጉ
በፀሎት እንባዋ ካለፍቃዶ ዘረገፈች…ይገርማል ወላጆቾ ቤት እያለች ዘወትር የምታለቅሰው በእነሱ ጥል እና ጭቅጭቅ በመበሳጨት ነበር..እዚህ ቤት እግሯ ከረገጠ ጀምሮ ግን እንባዋ የሚረግፈው በመሀከላቸው በምታየው ፍቅርና ለእሷ በሚያደርጉላት እንክብካቤ ስሜቷ እየተነካ ነው…ሰው ለሀዘንም ለደስታም እንዴት ተመሳሳይ ምላሽ ይሰጣል..?‹‹ጋሼ እኔ በጣም ብዙ ብር አለኝ …ችግሬ ብር አይደለም..ከእናንተ የምፈልገው ፍቅር ብቻ ነው……››

‹‹ይሁን እስኪ ..ግን እንዲህ መሆን አልነበረበትም.››.እያሉ ከቆሙበት ተንቀሳቀሱና ወደውስጥ ዘልቀው ፊት ለፊት ያለው ደረቅ ወንበር ላይ ተቀመጡ፡፡ወ.ሮ እልፍነሽና ለሊሴ አስቤዛውን ተጋግዘው ወደ ጓዲያ ወሰዱት፡፡
አቶ ለሜቻ ማውራት ጀመሩ…‹‹ምንም ነገር ከፈለግሽ ለእኔ ለአባትሽ ንገሪኝ..በስልክ እድንጠራልሽ የምትፍጊው ሰው ካለም…..ችግር የለው››
‹‹ጋሼ ሙሉ በሙሉ እስከምድን ድረስ ከማንም ሰው ጋር መገናኘት አልፈልግም..ደግሞ እመነኝ እኔ በመጥፋቴ ማንም የሚያስብ ሆነ የሚጨነቅ ሰው አይኖርም….እንደውም ጠፍታለች ሳይሆን ለሆነ ስራ የሆነ ሀገር እንደሄድኩ ነው የሚያስቡት..ከዚህ በፊትም ሁለት ሶስቴ አድርጌዋለው››
ከመቼ ወዲህ እንዲህ ውሸታም እንደሆነች ለራሷም ግራ ገባት ፡፡አሁን የት ሄደሽ ነበር ቢሏት የት ልትል ነው?፡፡ለመዝናናት ካልሆነ ለመኖር ወይም ለተወሰነ ጊዜ ቆይት ከአዲስአባባ ውጭ እግሯን አንስታ አታውቅም…ስለየትኛውም ሌላ ከተማ የጠለቀ እውቂያ የላትም..ብቻ ከቤሰተቦችሽ ተገናኚ እያሉ እንዳያጨናንቋት ማድረግ ያለባት እንደዚህ እንደሆነ በውስጧ አምናለች፡፡
‹‹ይሁን..እንግዲያው …እኛ አለንልሽ..አይዞሽ…ግን እንዲህ ብርሽን አታባክኚ… ስትድኚ በጣም ያስፈልግሻል ››
‹‹አይ ጋሼ..ስለእኔ አታስብ..እናቴ ብዙ ብር ጥላልኝ ነው የሞተችው…ባንክ በቂ ብር አለኝ፡፡››
‹‹ይሁን ልጄ..ብር ግን አያያዙን ካላወቁበት ስር የለውም..ሲታይ ብዙ የመሰለ ብር ከእጅ በኖ ሲጠፋ ቀናት አይፈጅበትም ››
‹‹ገባኝ….፡፡››
‹‹እሺ በቃ… አሁን አረፍ በይ..ሰፈር አንዲት ለቅሶ አለች… ደረስ ብዬ መጣሁ››
‹‹እሺ ጋሼ››
ወጥተው…ሄዱ…እሷም ወደትካዜዋ ገባች፡፡

ድንገት በቀኝ በኩል ወደአለው ግድግዳ ቀና ብላ አይኗን ስትተክል ግዙፍ ፎቶ ላይ ፈዛ ቀረች…የበሬዱ እንደሆነ እርግጠኛ ነች….
ከንፈሯቾ በፀደይ ወራት ለመበላት እንደደረሰ የጎመራ ብርቱካን ይመስላሉ…ስስ ነው በጣም ስስ..የሚገመጥ ሳይሆን የሚመጠጥ አይነት እና ደግሞ ጠባብ ነው ጠባብ የሚስጥር በር መሳይ  ጠባብ፡፡አይኖቾ ብርሀናቸውን ከከዋከብት የተዋሱት ይመስላል
…አፍንጫዋ ዝንፈት በሌለው የሂሳብ ስሌትና ትንግርት በሚያበስር የስነ.ከዋክብት ትንቢታዊ ጥበብ እንደተሰራ የግብፃችን ፕራሚድ አይነት ነው፡፡ፀጉሯ ምድረ አራዊት ሁሉ ተሰብስበው የሚኖሩበትና አማዞን ደን መሰል ነው፡፡እንዲህ ፎቶዋ ሲታይ ይሄ ቢሰተከካከል ብሎ ምንም እንከን ወይም ጉድለት ሊገኝበት የማይችል አይነት ነው፡፡
‹‹ሞት ግን ምንድነው?›› እራሷን ጠየቀች….ሞት በቀላሉ ጭሩሱኑ ባይኖር ብለን የምናማርረው ነገር አይደለም…ሞት ባይኖር ምድር የበለጠ የምትሰለች አስቸጋሪና አስጨናቂ ስፍራ ትሆን ነበር…ስለዚህ ሞት የህይወትን ያህል እጅግ አስፈላጊ የአምላክ ስጦታ እንደሆነ ታምናለች ይሁን እንጂ ሰው ደግሞ የህይወትን ጫፍ እንኳን ሳያይ እንዲህ በጨቅላ እና በለጋ ህይወቱ ሲቀጠፍ ያሳዝናል..‹‹በተለይ ለወላጆቾ እና ለሚያፈቅሯት ሰዎች ይሄንን እውነት መቀበል በጣም ከባድ ነው፡፡››ስትል አሰበች
‹‹አንቺ ሞተሸ አልሞትሽም ዋናው አንቺነትሽ ለእኔ ህይወት ሰጥቶኛል….የአንቺ ልብ ከእኔ ማንነት ጋር ከተዋሀደ በኃላ ቀይሮኛል፡፡››ስትል በውስጧ አጉረመረመች፡፡ሀሳቧን ሳትጨርስ ፊራኦል ከውጭ ስልኩን እየጎረጎረ መጥቶ ፊት ለፊቷ ቁጭ አለ…ለረጅም ደቂቃዎች አላናገራትም

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ዘጠኝ
አቶ ኃይለ መለኮት እቤታቸው ባለ የገዛ ቢሯቸው ውስጥ ተሸከርካሪ ወንበራቸው ላይ ተቀምጠዋል…በቀኝ እጃቸው የሚያብረቀርቅ ማካሮብ ሽጉጣቸውን ይዘው ፊታለፊታቸው ያሉት ሶስት ግለሰቦች ላይ በየተራ እያነጣጠሩ ምላጩን በስሱ እየዳበሱ ይናገራሉ
‹‹በመጀመሪያ ማንን ልግደል?››
‹‹ጌታዬ ይቅር ይበሉን…አጥፍተናል….››

‹‹አጥፍተናል….ጥፋት እኮ በቀላሉ ሊስተካከል የሚችል ስህተት የሆነ ድርጊት ስታደርግ ነው፡፡ለምሳሌ እዚህ መኖሪያ ቤቴ ላይ ጋዝ አርከፍክፈህ ክብሪት በመለኮስ ግማሹን ህንፃ ብታወድመው ጥፋት አጥፍተሀል ብዬ የጠየቅከውን ይቅርታ ልቀበልህ እችላለው፡፡ ምክንያቱም እቤቱን አሁን ካለበት ይዘት ይበልጥ አስውቤ ከእንደገና ላስገነባው እችላለሁ…ወይም ከፋብሪካዎቼ ትልቁን መርጠህ ሙሉ በሙሉ ብታወድመው እንደጥፋት ቆጥሬ ይቅርታህን ልቀበል እችላለው…ወይንም ሽጉጥህ ባርቆብህ ቀኝ እጄን ብትመታኝና በዛ የተነሳ እጄ ቢቆረጥ አዎ ይቅርታህን ልቀበል እችላለው፡፡ግን አሁን ምንም አላስቀረህልኝም፡፡ልጄ ሁለ ነገሬ ነች…ምንም መተኪያ ምንም ማካካሻ የላትም…ያ ማለት ይቅርታ ላደርግላችሁ ፈፅሞ አልችልም.››
‹‹ጌታዬ ይገባናል፣ አንተ ትክክል ነህ..ግን ቢያንስ በፍለጋው ላይ ጠንክረን እየሰራን ነው….የሆነ ትንሽ ቀን ጨምርልንና አቅማችንን አሟጠን እንፈልጋት… የሆነ ያህል ጊዜ ስጠን… ካልተሳካልን ያሰብከኸውን ታደርጋለህ፡፡››
‹‹አዎ እሱማ አደርጋለው….ዋጋማ ትከፍላላችሁ….አሁን የምናደርገው…..››ንግግራቸውን ሳያጠናቅቁ ስልካቸው ጠራ…የደቀኑትን ሽጉጥ ሳያወርድ ስልኩን አንስተው ማውራት ጀመሩ፡፡
‹‹እሺ…ጥሩ …ሶስቱም ነው እይደል… በጥንቃቄ ጠብቋቸው››
ስልኩን ከዘጉ በኃላ ንግግራቸውን ቀጠሉ‹‹ስልኩ ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ…?የእናንተ የሁለታችሁን አንዳንድ ልጃችሁን ያንተን ደግሞ ምትወዳትን ሚስትህን አሳግቼቸዋለው…ልጄ በሚቀጥሉት ሶስት ቀን ውስጥ ተገኝታ ወደቤቷ ካልተመለሰች ያው የምወዳትን ልጄን ስላሳጣችሁኝ ለዛ ክፍያ የምትወዱትን ሰው ታጣላችሁ ማለት ነው፡፡››ሲል ሰቅጣጭ መርዶ አረዷቸው፡፡
ሶስቱም ሰዎች ላይ የታየው ድንጋጤ ሲኦላዊ ነበር፡፡፡አቶ ኃይለልኡል ሰዎቹን ከቢሮቸው አሰናብተው ሽጉጡን ወደመሳቢያው ውስጥ መልሰው በማስቀመጥ ቆለፉበትና ወጥታው ወደ ባለቤታቸው ወ.ሮ ስንዱ መኝታ ቤት ሄዱ ….ሚስታቸው አልጋው ላይ ተሰትረው ጉልኮስ ክንዳቸው ላይ ተሰክቶ እህህ እያሉ ነው..ለዘመናት ወደዋቸው የማያውቁት ባላቸውን ድምፅ ሲሰሙ የከደኑትን አይን ገለጡ እና በመከራም ቢሆን ከንፈራቸውን አነቃነቀው ማውራት ጀመሩ

‹‹ኃይሌ…ልጃችን አልተገኘችም?››
‹‹አይዞሽ አታስቢ ..ትገኛለች….አንቺ ምንም አትጨነቂ››ሊያፅናኗቸው ሞከሩ፡፡
‹‹እንዴት አልጨነቅ…?በዚህ አለም ላይ ያለቺኝ እሷ ብቻ ነች..በህይወቴ ሙሉ የበደልከኝን በደል እንድረሳልህ…የሰራህብኝን ስራ ይቅር እንድልህ ከፈለክ ልጄን አግኝልኝ….ልጄን ካገኘህልኝ ያልከኸውን ሁሉ አደርግልሀለው….እንደውም ምንም ሀብት ሳልካፈልህ እፈታሀለው…እፈታህና ገዳም እገባለው..አዎ ልጄ ሰላም መሆኗን ካረጋገጥኩ ከህይወትህ ዞር እልልሀለው››
‹‹አረ ተይ …ለእኔም ልጄ እኮ ነች…እሷን ለማግኘትና ወደቤቷ ለመመለስ ከአንቺ ጋር ይሄንን አድርጊልኝ እያልኩ የምደራደር ጭራቅ ነገር እመስልሻለው….?ተይ እንጂ..አሁን ወጣ ብዬ ፖሊሶቹ ምን ላይ እንደደረሱ መጠየቅ አለብኝ..ሀኪሞቹ ሚሉሽን ስሚና ጤናሽን ተነክባከቢ..ልጃችን ስትመጣ እንደዚህ ሆነሽ እንደታገኚሽ አልፈልግም…እናቴ በእኔ ምክንያት ሽባ ሆነች ብለ መፀፀት የለባትም››ብሎ ወጥቶ ሄደ…..
///
በፀሎት ከእንቅልፏ የባነነችው በቤቱ ውስጥ ግርግር እና የብዙ ሰው ድምፅ ስትሰማ ነበር..አይኖቾን ስትገልጥ ግን ያሰበችውን ያህል ብዙ ሰው አልነበረም ነበር…ወ.ሮ እልፌ
፤አቶ ለሜቻና አንድ ሙሉ ሱፍ የለበሰ ጎልማሳ ሰው ነበር በቤቱ ያሉት….ግን ያ ጎልማሳ ሰው ሲያወራ ድምጹ መመጠኛው እንደተበላሸበት ማይክራፎን ከጣሪያ በላይ ይጮኸ ስለነበረ የብዙ ሰው ድምጽ ይመስላል….
አይኗን ስትገልጥ አየና ወደእሷ ተጠጋ.‹‹ልጄ ተነሳሽ..?ጥሩ …ይሄ ዶክተር ታፈሰ ይባላል..የጓደኛዬ ልጅ ነው….አንቺን እንዲያይልኝ አስቸግሬው ነው፡፡›››አቶ ለሜቻ ናቸው ተናጋሪው፡፡
‹‹አባቴ ዝም ብለህ ነው እኮ የተቸገርከው..ደህና ነኝ እኮ››
ከወ.ሮ እልፍነሽ ጋር በተስማማችው መሰረት ቢሻክራትም አንቱታውን በአንተ ቀይራ ማውራት ጀመረች…
‹‹ደህና መሆንሽና አለመሆንሽን እኔ ሀኪሙ አይቼ ብወስን አይሻልም›› ዝም አለችው….
ወደእሷ ተጠጋና  አያት…ግንባሯና ከፊል ፊቷ በስነስርአት መታሸጉን አረጋገጠና  ..አንድ መርፌ በክንዷ ወግቷት መድሀኒት አዘዘላት…
‹‹በቃ ጋሼ..የወንድሞት ልጅ በጥሩ ሁኔታ ላይ ትገኛለች..ቁስሉ ጊዜውን ጠብቆ ፋሻው ተነስቶ በደንብ ፀድቶ ከእንደገና መታሸግ አለበት…›››
‹‹ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም እያልከኝ ነው?››
‹‹አይ የለም ሰላም ትሆናለች..ግን ምን አልባት ፊቷ ላይ ጠባሳ ሊሆንባት ይችላል፡፡››
‹‹ያንን ማስቀረት አይቻልም?››አቶ ለሜቻ ጠየቁ፡፡
‹‹ያው የቆዳ ስፔሻሊስቶች ያስተካከሉታል..በአሁኑ ጊዜ ብር ካለ የማይስተካከል ነገር የለም..ዋናው በህይወት መትረፏና አካለ ጎዶሎ አለመሆኗ ነው…የጠባሳው ነገር የገንዘብ ጉዳይ ነው… ይስተካከላል፡፡››
‹‹ይሁን እንግዲህ…….አንተንም አስቸገርኩህ››
‹‹አረ ጋሼ…ለርሶ ባልታዘዝ አባቴ አያናግረኝም….በማንኛውም ሰዓት ካመማት ደውሉልኝ..አሁን ልሂድ….፡፡እግዜር ይማርሽ እህቴ››
‹‹አመሰግናለው ዶ/ር፡፡››
‹‹ዶ/ር አቶ ለሜቻን አስከትሎ ቤቱን ለቆ ወጣ ..ክፍል ውስጥ ወ.ሮ.እልፍነሽና በፀሎት ብቻ ቀሩ፡፡
‹‹ጋሼ ዝም ብሎ እኮ ነው የሚጨነቀው?››
‹‹እሱ..እንዲሁ ነው….ታያለሽ ነገ ደግሞ ሌላ ዶክተር ለምኖ ይዞ ይመጣል..እስክትድኚ እረፍት አይኖረውም››
አቶ ለሜቻ ተመልሰው ከመምጣታቸው በፊት ለሊሴ ከሄደችበት ተመልሳ መጣች፡፡ ይዛ የመጣችው ዕቃ ግን የሳሎኑን ግማሽ የሸፈነ ነበር….ከአምስት በላይ ፔስታል ከባለታክሲው ጋር እየተጋገዙ ወደውስጥ አስገቡ….ከገዛችው ዕቃዎች ውስጥ ለበፀሎት አዲስ አንሶላዎች
…ምቾት ያለው ብርድልብስ ፣ቢጃማ ..ሸበጥ ጫማ..ቅባት…ፓንቶች..ብቻ ያስፈልጋታል ያለችውን እና በእይታዋ የገባላትን ዕቃ ሁሉ ገዝታ ነበር..ከዛ የቤት አስቤዛ አትክልቱን..ፍራፍሬውን..ፓስታ ..መኮሮኒ..ስጋና የመሳሰሉትን እልክ የታጋባች ይመስል ቤቱን ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በቁሳቁስ ሞላችው…፡፡
አቶ  ለሜቻ  ዶክተሩን  ሸኝተው  ሲመለሱ  ትተው  የሄዱት  ሳሎን  ሌላ  መልክ  ይዞ ሲጠብቃቸው ከመደንገጣችው ብዛት ባሉበት ደርቀው ቆሙ….
‹‹ሊሊሴ ምንድነው ይሄ ሁሉ?››
‹‹አየህ አባዬ አንሶላው አያምርም… ብርድ.ልብሱስ….?.የሄው ቢጃማም ገዛሁላት…››
‹‹ጥሩ አደረግሽ…ብሩን ከየት አመጣሽው?››
‹‹እኔማ ከየት አመጣለው….እራሶ ሰጥታኝ ነው፡››አለች ወደበፀሎት እየጠቆመች፡፡


‹‹አዎ ልጄ… እሱ እንደዛ ነው የሚያደርገው››
‹‹በይ አታስቢ…ብላ ብሩን ቦርሰዋ ውስጥ ከታ እንዳመጣጡ ጓዲያውን ለቃ ወጣችን ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ላይ ያለችውን በፀሎትን እስከአሁ አይታት በማታውቀው መንገድ በስስት አይን እያየቻት እቤቱን ለቃ ወጣች፡፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


‹‹ያው የተገኘውን ነዋ….ከሁለት አመት በፊት ነው ከተግባረእድ በፀጉር ስራ የተመረቀችው…..አፈሩን ገለባ ያድርግላትና ሁለት አመት ከፍላ ያስተማረቻት ሟች እህቷ ነበረች…የሆነ ቤት ተቀጥራ ለአንድ አመት ሰርታ ነበር ፡፡አልተስማማችም መሰለኝ ሰሞኑን ለቀቀች ….አሁን ሌላ ቦታ እየፈለገች ነው፡፡ አንድ ወዳጇ ፀሀፊነት አግኝቼልሻለው ብላት ያንን ለማረጋገጥ ነው የሄደችው፡፡››
የሞቿ ስም ሲጠራ እንደተለመደው የበፀሎት ሰውነት ሽምቅቅ አለ‹‹ግን እቤታችሁ ፊት ለፊት ነው….የሆነች ትንሽ ክፍል ቢኖር እኮ የራሷን ስራ ብትሰራ ጥሩ ነበር››

‹‹እሱማ እንዳልሽው ጥሩ ነበር …ልጄ ግን ቀላል ይመስልሻል…?ለእኛ ያንን ማድረግ ከባድ ነው፡፡እህቷ ልክ አሁን አንቺ እንዳልሺው አይነት እቅድ ነበራት…ተምረሽ ስትጨርሺ ከምሰራበት ባንክ ተበድሬም ቢሆን የራስሽን ፀጉር ቤት ከፍትልሸለሁ ብላ ቃል ገብታላት ነበር…ልጄ ቃሏን የምታጥፍ ሰው አልነበረችም……››እንባቸው በአይናቸው ግጥም ብሎ ረገፈ….አብራ አለቀሰች…እንደምንም ለመረጋጋት እየሞከሩ ንግግራቸውን ካቆሙበት ቀጠሉ‹‹እንዳልሺው…እንደምንም እቤቱን ብንሰራላት እንኳን ማሽኑን ከየት መጥቶ ይገዛል…..እንዳልሽው ግን አንድ ቀን እንደዛ ማድረጋችን አይቀርም…››በትካዜ መለሱላት፡፡
‹‹እማዬ››
‹‹አቤት ልጄ››
‹‹የሆነ ቦርሳ ነበረኝ አይደል..?››
‹‹አዎ አለሽ ..ላምጣልሽ?››
‹‹አዎ ካላስቸገርኮት››
‹‹የምን መቸገር አመጣሽብኝ..አመጣልሻለሁ››አሉና የበላችበትን እቃ ከተቀመጠበት አንስተው ወደውስጥ በመግባት ከደቂቃዎች በኃላ ቦርሳውን አንጠልጥለው አመጡና ስሯ አስጠግተው አስቀመጡላት፡፡
ዚፑን ከፈተችና ከላይ ያሉትን ሁለት ጅንስ ሱሪ…ሁለት ቲሸርቶች አወጣችና አልጋ ላይ አስቀመጠች….ከዛ በኃላ ያለውን እስር እስር ባለሁለት መቶ ኖት ብር ነው…ስንት ብር እንደሆነ አታውቅም …በተለያየ ጊዜ ዝም ብላ ቁም ሳጥኗ ውስጥ እየወረወረች ያጠራቀመችው ገንዘብ ነው..ምን አልባ ሶስት ወይም አራት መቶ ሺ ብር ይሆናል፡፡አንዱን እስር አወጣችና ልብሱን መልሳ ከታ.. ዚ..ፑን ዘጋችና ከራስጌዋ አስቀመጠችው…
‹‹እማዬ..››
አቀርቅረው ሲኒ እያጠቡ ነበረ ..ስትጠራቸው ቀና አሉና‹‹አቤት ልጄ.. ጠራሺኝ?››አሉ
‹‹እንኩ ይሄንን ብር››
ለደቂቃዎች ያህል ክው ብለው አዮት…‹‹ምን እያልሽ ነው ልጄ?››

‹‹ለቤት አንዳንድነገር ይግዙበት….››
‹‹እንዴ ይሄን ሁሉ ብር?››
‹‹ትንሽ እኮ ነው…ሀያ ሺ ብር ነች››
ፈገግ ብለው ‹‹አይ ልጄ… ሀያ ሺ ብር እኮ በአንድ ጊዜ እንዲህ ከነክብሩ እዚህ ቤት ገብቶ አያውቅም..በይ መልሺው…..ከህመምሽ ስታገግሚ ያስፈልግሻል፡፡››
‹‹አይ አያስፈልገኝም…››
‹‹አይ ልቀበልሽ አልችልም….ለሜቻስ ዝም ሚለኝ ይመስለሻል?››
ከጎኗ ያስቀመጠችውን ሻንጣ መልሳ ሳበችና ዚፕን እስከመጨረሻው በመክፈት.. ከነልብሱ ዘቅዛቃ ፍራሹ ላይ ዘረገፈችው….
ወ.ሮ እልፍነሽ በህልማቸው እንኳን አይተው የማያውቁት አይነት የብር ቁልል እየተመከቱ ነው..ያለፍቃዳቸው የተከፈተውን አፋቸውን መልሰው መክደን አቃታቸው፡፡
‹‹አዩ አይደለ….ይሄ ሁሉ ብር አለኝ….ደግሞ አዩት ይሄንን ሀብልና የጆሮ ጌጥ ብዙ መቶ ሺ ብር የሚያወጣ ነው..ከቸገረኝ እሸጠዋለው….እና ይሄንን ብር ይቀበሉኝና እቤት ውስጥ የጎደለውን ነገር ያሟሉበት….ደግሞ እናንተ ማለት እግዚያብሄር ለእኔ የሰጣችሁ ስጦታዎቼ ናችሁ …እንኳን ብሬን ህይወቴን እሰጣችኃላው፡፡የተገለበጥኩት መንገድ ላይ ወይም ሌላ ሰው ጊቢ ቢሆን አኮ…እንኳን ብሬን ህይወቴን እንኳን ማትረፍ አልችልም ነበር…እዛው ሳጣጥር ገድለው ቀብረውኝ ..ገንዘቡን በሙሉ ይወስዱት ነበር፡፡››
‹‹በስመአብ በይ ልጄ ….ተይ ተይ…››
‹‹እውነቴን ነው….እናንተ ሻንጣውን እንኳን ምን እንዳለበት ከፍታችሁ አላያችሁትም››
‹‹የሰው ዕቃ ያለፍቃድ እንዴት ይታያል …?.ነውር አይደለ እንዴ?››
‹‹እኮ እኔም ለማለት የፈለኩት ያንን ነው..በዚህ ዘመን ነውር የሚባል ነገር ጠፍቷል…ሰው ቁስአምላኪ ሆኗል….እምነት ..ሀቀኝነት ..ክብር  …እውነት ….የሚባሉ ቦዶ ቃላት ሆነዋል››
‹‹ካልሽ እሺ ልጄ……ለሜቻ ግን ምን ብዬ እንደማስረዳው አላውቅም››

‹‹ግድ የሏትም ጋሼን እኔ አሳምናቸዋለሁ፡፡››
ብሩን ተቀበሏትና..‹‹ልጄ እቤቴን እንዲህ እንደሞላሽው ላንቺም የሞላ ህይወት ይስጥሽ..››አይናቸውን ግድግዳው ላይ ወደተሰቀለው የሞች ልጃቸው ፎቶ ላኩና ፍዝዝ ብለው‹‹ልጄ  እንዲህ ድንገት መጥታ መአት ብር እጄ ላይ በማስቀመጥ ..እማዬ የሚያስፈልግሽን ነገር ግዢበት ..እቤት የጎደለ ነገር ካለ አሟይ…ትለኝ ነበር….አንድ ቀን የራሷን ኑሮ ሳትኖር እንደጓደኞቾ ጌጣጌጥና መዘነጥ ሳያምራት ቤተሰቦቾን እንዳገለገለች ሞተች….አሁን ሳስበው ልጅ ከጊዜዋ ቀድማ እንደዛ በስላ ትልቅ ሰው የሆነችውና በደግነትና ቤተሰቦቾን በማገልገል ብኩን የሆነችው ምን አልባት ቶሎ እንደምትሄድ አውቃ ይሆን እንዴ
?እላለሁ..ብቻ ተይው…..አንቺን እግዜር ይባርክሽ››
‹‹አሜን እማዬ››
‹‹ልጄ››
‹‹ወይ እማዬ››
‹‹እማዬ  ማለትሽ  ካልቀረ  …አንቱታውን  ተይው…ልጆቼ  አንቺ  ነው  የሚሉኝ
…..አባታቸውንም አንተ ነው የሚሉት…እንግዲህ አንቺም ልጃችን ሆነሽ የለ….ከአነሱ ለምን ትለያለሽ..አንቱታውን ተይው››
‹‹አመሰግናለው እማዬ…..በጣም ነው ማመሰግነው..አሁን ትንሽ ልተኛ፡፡››
‹‹ተኚ ልጄ.. ተኚ››አሉና ወደጓዲያቸው ገብተው…አሮጌ ሞባይላቸውን ፈለጉና ለልጃቸው ለለሊሴ ደወሉና ስራ ፍለጋውን ጥላ ወደቤት እንድትመጣ ነገሯት….
እንደመጣች ወደጓዲያ ወስደው ብሩን እያሳዩ የሆነውን ሲነግሯት ከመደንገጧ የተነሳ አፏ እንደኩበት ደረቀና ምላሶን ምታረጥብበት ምራቅ አጣች…ይህቺ ልጅ ለ በቤቱ መከራ ወይ መዘዝ አስከትላ ትመጣለች የሚል ከፍተኛ ፍራቻ በውስጦ ሲገላበጥ ነበር..ተቃውሞዋን እንደወንድሟ አውጥታ አታንጸባርቀው እንጂ በውስጧ ለመቶኛ ጊዜ ደጋግማ አስባበታለች…አሁን ግን እናቷ እየነገሯት ያሉት ተቃራኒውን ነው…መአት ሳይሆን በረከት ነው እጃቸው ላይ ያለው…በዛ ላይ ጥሩ ገድ አላት…ለወር ስራ ፍለጋ ስትኳትን ነበር..አሁን  ግን  የተሻለ  የተባለ  ስራ  ባልጠበቀችው  መንገድ  ለዛውም  በቀላሉ

አግኝታለች፡፡ፀሀፊነት፡፡ስራውን ያገኘችላት..በፊት ትሰራበት የነበረ ፀጉር ቤት በደንብኝነት ታውቃት በነበረች አስቴር በምትባል ሴትዬ አማካይነት ነው፡፡
‹‹እማዬ በቃ እሷንም ሆስፒታል ወስደን ማሳከም እንችላለን ..ብዙ ብር ነው፡፡››
‹አዎ እንደዛ ብያት ነበር..ግን ቦርሳዋ ውስጥ ብዙ ብር አለ ….ይሄንን ለቤት የጎደለ ነገር ግዙበት መታከም ከፈለኩ በዚህ እታከማለው አለችኝ…››አብራሩላት
‹‹ውይ እማዬ እንደዛ ከሆነ ደስ ይላል..አሁን ምን እናድርገው››
‹‹እኔ እንጃ የጠራሁሽ ለዛ ነው…አንቺ ያስፈልጋል የምትይውን ነገር ለቤቱም ለእሷም ገዝተሸ ነይ፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ እማዬ ››አለችና ብሩን ከእጃቸው ላይ ተቀብላ ግማሹን ገመሰችና‹‹..ይሄንን አስቀምጪው..በዚህ የሚያስፈልገንን ነገር ገዝቼ መጣለሁ...ዝም ብለን ብሩን ታቅፈን ከጠበቅነው አባዬ ሁንም ተቀብሎን ነው የሚመልስላት››ስትል ስጋቷን ነገረቻቸው፡፡


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ስምንት

ሰለሞን ለዚህ ነው ከውጭ ከተመለሰ በኃላ ለመደላደል ስራ መጀመር እንዳለበት የወሰነው
‹‹ምንድነው መስራት ያለብኝ?ምን አይነት ዕውቀት ነው ያለኝ?ምን አይነት ጥሪትስ አለኝ?ህብረተሠብስ ምን አይነት ሸቀጥ ወይም አገልግሎት ነው መግዛት የሚፈልገው?። መልሶቹ ቀላል አልነበሩም...ወደ አእምሮው የሚመጣው መልስ ወደግል ስራ የሚያስገባው ሳይሆን እንደውም በተቃራኒው የሚያርቀ ነው የሆነበት።
1/ይሄ የምኖርበት ህብረተሠብ በዚህ ሰአት ግዙፍ ችግሩ ምንድነው...?ወረቀትና እስኪሪብቶ ያዘና ዘርዝሮ መፅፍ ጀመረ
1/ኑሮ ውድነት
2/የሠላም እጦት
3/የፍቅር እጦት
4/ቴክኖሎጂ ቅኝ ግዛት
5/...!!የአየር ፀባይ መዛባት
የፃፈውን መለስ ብሎ አየው ...ለደቂቃዎች ብቻውን ተንከትክቶ ሳቅ ። ዝርዝሩን አንድ አነስተኛ የግል ቢዝነስ ለመክፈት ሳይሆን አዲስ ጠቅላይ ሚንስቴር ሆኖ ተሹሞ በሀገሪቱ ስር ነቀል ለውጥ የሚያመጡ የፓሊሲ አማራጮችን ለማርቀቅ መነሻ ሀሳቧችን እያሰላ ያለ ፓለቲከኛ ነው  የሚመስለው።
‹‹እስቲ የህብረተሠብም የኑሮ ውድነትን የሚቀርፍ ምን አይነት ቢዝነስ ነው የሚኖረው...?ኑሮ ውድነቱ እንኳን ግለሠብ መንግስትስ ለማስተካከል አቅም አለው...?የመለኮት ጣልቃ ገብነት ከሌለስ  መፍትሄ ይኖረዋል?።››ሲል አሰበና በራሱ ድርጊት ዳግመኛ ሳቀ፡፡ ከዘረዘራቸው ሀሳቦች የ3 ተኛው ሀሳቡን ገዛው።‹‹ፍቅር እጦት የእኔም የማህበረሰብም የጋራ ችግር ነው።የፍቅር እጦት ደግሞ የሌሎች ችግሮች ሁሉ መነሻ ምክንያት ነው።ደግሞ በሙሉ አቅሜ መስራት የምችለው ስራ እሱን ነው …ሞያዬም ችሎታዬም እሱ ላይ ነው››ሲል አሰበና ወሰነ፡፡

አሜሪካ እያለ ተቀጥሮ የሚሰረባትን የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ ድርጅት እዚህ ሀገሩ መሀል አዲስ አበባ ላይ በራሱ ለመክፍት ወሰነ…‹‹የራስህን ቢዝነስ ጀምር›› ብላ ስትጨቀጭቀው ለነበረችው አስቴር ነገራት፡፡፡አንገቱ ላይ ተጠምጥማ ጉንጩን እየሳመች በሀሳብ በጣም መደሰቷንና በማንኛውም ነገር ከጓኑ እንደሆነች አበሰረችው…እሷ የተደሰተችበት ነገር ደግሞ በእሱ ህይወት ትልቅ ቦታ ስላለው ወዲያውኑ በደስታ ወደእንቅስቃሴ ገባ……ፍቃድ ለማውጣት ቢሮ ለመከራየትና አስፈላጊ የቢሮ እቃዎችን አሞልቶ ለመክፈት 40- ቀን ብቻ ነበር የፈጀበት፡፡

ይሁን እንጂ ለአንድ ወር ያህል በሰአት ቢሮ እየገባ በሰዓት ቢወጣም አንድም ደንበኛ ማግኘት አልቻለም…ሁሉ ነገር ተስፋ አስቆራጭ የሆነበት፡፡ግራ ጋባው ፣በመጀመሪያውም ዝግና ድብቅ ባህል ባለበት ሀገር የጋብቻና የፍቅር አማካሪ ድርጅት ከፍቶ ውጤታማ ሆናለው ብሎ በማሰብ በራሱ ጅልነት ተበሳጨ…የስድስት ወር የቢሮ ኪራይ ባይከፍልና ለፈርኒቸር እና የቢሮ እቃዎችን ለማሟላት ከመቶ ሺ ብሮች በላይ ባያወጣ ኖሮ ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ ዘጋግቶ ሌላ የቅጥር ስራ ይፈልግ ነበር..ግን ለጊዜው እንደዛ ማድረግ አይችልም…‹‹አዎ ለአስቴር ምን እላታለሁ….?እንድታፍርብኝማ አላደርግም…እሷ ከምታፍርብኝ አለም ጠቅላላ ብትገለባበጥ እመርጣለሁ….ስለዚህ የሆነ ነገር ማድረግ አለብኝ››በማለት ወሰነና ቀኑን ሙሉ ሲያሰላስል ዋለ… የሆነ ነገር ብልጭ አለለት፡ስልኩን አነሳና ደወለ፡፡
ከአራት ጥሪ በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ሄሎ ወንድሜ….›››የሚል ድምፅ በስልኩ እስፒከር አቆርጦ ጆሮው ውስጥ ተሰነቀረ…
‹‹አለሁልሽ››
‹‹ምነው ድምፅህ?››
‹‹ደህና ነኝ….የሆነ ነገር ላማክርሽ ነበር?››
‹‹ይቻላል..ግን ስራ አሪፍ ነው እንዴ?….››
‹‹አሪፍ ነው …አሁን አንድ ደምበኛዬን ወደትዳር ከመግባቷ በፊት ማድረግ ስለሚገባት ቅድመ ዝግጅት ማወቅ ፈልጋ ነበር.. እሷን እንደሸኘሁ ነው የደወልኩልሽ››ዋሻት፡፡
‹‹ደስ ይላል ወንድሜ …ህልምህን መኖር ጀምረሀል ማለት ነው….››
‹‹አንቺ ከጎኔ ሆነሽ እስከደገፍሺኝ ድረስ ምንም ማላሳከው ነገር የለም…..አሁን ለምን መሰለሽ የደወልኩልሽ…ፀሀፊ ብቀጥር ብዬ አሰብኩ…››ያሰበውን ነገራት፡፡
‹‹አዎ አንተ ….እስከዛሬ እንዴት አላሰብንበትም…?ለፕሮቶኮሉ እራሱ አስፈጊ ነው…ባለጉዳዬች እንደመጡ አንተን ማግኘት የለባቸውም በፀሀፊህ በኩል ቀጠሮ ይዘውና ተገቢውን ቅድመ ማሟላት ያለባቸውን ነገር አሟልተው መሆን አለነበት…አሪፍ ነው…››
‹‹እና እንዴት ላደርርግ ?ማስታወቂያ ላውጣ….?››
‹‹አይ እኔ በሶስት ቀን ውስጥ ምርጥ ፀሀፊህ ቀጥርልሀለው….አንተ በዚህ ጉዳይ ምንም አትጨነቅ…..ሶስት ቀን ብቻ ስጠኝ››
‹‹እሺ ማታ እቤት እንገናኝ››
‹‹እሺ ቸው ..ወንድሜ››
‹‹ቸው..››
ወንድሜ የሚለው ቀል ከአንደበቷ በወጣ ቁጥር በአንገቱ የተንጠለጠለ የብረት ሰንሰለት ነው የሚታየው….ሆነ ብላ እሱን ለማጥቃት አስባ ከአንደበቷ የምታወጣው ነው የሚመስለው….‹‹አደራ እኔ እህትህ ባልሆንም ልክ እንደእህትህ ነኝና ሌላ ነገር በአእምሮህ እንዳይበቅል››የሚል ማስጠንቀቂያ ነው የሚመስለው፡፡
የእናትና አባቱ ልጆች የሆኑት እህቱ ወንድሜ የሚለውን ስም በአመት አንዴ እንኳን ሲጠቀሙ አልሰማም….ትዝም የሚላቸው አይመስለውም…እሷ ግን ልክ እንደዘወትር ፀሎት እንደውዳሴ ማርዬም ነው በየእለቱ የምትደግመው፡፡
///
በፀሎት ጥዋት ከእንቅልፏ ስትባንን እቤት ውስጥ ከወ.ሮ እልፍነሽ በስተቀር ሌላ ማንም ሰው አልነበረም፡፡
‹‹እማዬ ሰው ሁሉ የት ሄደ?››እማዬ ብላ መጣራቷን ለራሷም እየገረማት ነው…ደግሞ አፏ ላይ አልከበዳትም…ወላጅ እናቷ…ሌላ ሴት እናቴ እያለች መጥራት መጀመሯን ብትሰማ ልብ ድካም ይዟት ፀጥ እንደምትል እርግጠኛ ነች፡፡
‹‹ወይ ልጄ… ነቃሽ…ልቀስቅሳት ወይስ ትንሽ ትተኛ እያልኩ ከራሴ ጋር ስሟገት ነበር፡፡ በረሀብ ሞትሽ እኮ››ብለው  ወደ ጓዲያ ገብና የእጅ  ማስታጠቢያ  ይዘው መጥተው

ሊያስታጥቦት ጎንበስ አሉ…እንደምንም ከአንገቷ ቀና ብላ ተነሳችና ‹‹ያስቀምጡት እኔ እታጠባለው››
‹‹አረ ችግር የለውም ልጄ ..ችግር የለውም››
‹‹ግድ የሎትም….››.
‹‹እንግዲያው ታጠቢ …ቁርስሽን ላቅርብ ›› ብለው ማስታጠቢያው ስሯ አስጠግተው አስቀመጡላትና ተመልሰው ወደ ጓዲያ ሔድ …….እግሯ በተንቀሳቀሰች ቁጥር ጥዝጣዜው ነፍሶ ድረስ ይሰማታል…..ፊቷ ላይ አሁንም ተራራ የሚያህል ቁስል የተሸከመች እየመሰላት ነው…እንደምንም ተንፏቀቀችና እጇን ታጥባ የሚመጣላትን ቁርስ መጠበቅ ጀመረች…ጩኮ ከእርጎ ጋር ነበር የመጣላት…ጩኮ መች በልታ እንደምታውቅ አታስታውስም….ቤቷ ቁርስ ሲቀርብ አስር …አስራአምስት አይነት ምግብ ጠረጴዛ ሞልቶ ነው….ከዛ ውስጥ ሶስት ወይም አራት አይነቱን አፕታይቷ የፈቀደላትን መርጣ በልታ ሌላውን ትተዋለች..አሁን የቀረበላት ምግብን ያህል ግን አስደሳች አልነበረም…….እርቧት ስለነበረ እየተስገበገበች በላች…
ያጋባችውን ሰሀንና ብርጭቆ መልሳ…እጇን ታጠበችና…..‹‹እማዬ ማንም የለም እንዴ?››ስትል ደግማ ጠየቀች፡፡
‹‹ልጄ ለሊሴ ስራ ፍለጋ ብላ ወጥታለች…ፊራኦል ስራ ነው ..አባትሽም እንደዛው››መለሱላት፡፡
‹‹ለሊሴ ምን አይነት ስራ ነው የምትፈልገው?››


Jawar Mehhamed Altsetsetim አልፀፀትም Book.pdf
10.6Mb
📚ርዕስ : " አልፀፀትም
📝ፀሀፊ: " ጃዋር መሀመድ

📖የገፅ ብዛት:- 433
📆ዓ. ም:-.. 2017

▬▬▬▬▬▬▬

➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
        ➖https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
➖➖➖➖➖➖➖➖➖


…አስቴርን ከአነልጇ ያገባታል ..የልቡም የቤቱም ንገስት ያደርጋታል››ሰው ምን ያላል እቤተሰብ ምን ይላሉ አሁን አይሰራም ..እስከዛሬ እሷ እንደምክንያት የምታቀርባቸው እናትና አባቱም እሷን በዳሩ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ነው ተከታትለው የሞቱባቸው……‹‹አሁን ምክንያት አይኖራትም››ብሎ ወስኗል፡፡
ለዚህ ነው ከውጭ ከተመለሰ በኃላ ለመደላደል ስራ መጀመር እንዳለበት የወሰነው፡፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ግን ደግሞ የአስቴር ወቅታዊ ኩርፊያ አልገባውም ነበር።‹‹መስፍን ደብዳቤ ለፃፈላት እኔን ለምን ልታኮርፈኝ ቻለች?››እራሱን ጠየቀ
"እና እኔ ምን አጠፋው..የምታኮርፊኝ?"ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡ "አይ አንተማ ምንም አላጠፋህ …እኔ ነኝ እንጂ ዘላለም በብላሽ ከአንተጋር የምንዘላዘለው..ነው ወይስ እናቴ የቤታችሁ አገልጋይ ስለሆነች አትመጥነኝም ብለህ አስበህ ነው?"አለቸው።እና እየተመናጨቀች ተለይታው ወደቤቷ አመራች።
ሰለሞንም ደንዝዞ ወደቤቱ ገባና በመጨረሻ ስትለየው የተናገረችውን ዓ.ነገር ሲያሰላስል አደረ።"....እኔ ነኝ እንጂ ዘላለም በብላሽ ከአንተጋር የምንዘላዘለው... ‹‹ምን ለማለት ፈልጋ ነው?ታፈቅረኛለች ማለት ነው?እኔስ አፈቅራታለሁ እንዴ? መስፋን የፃፈላትን ደብዳቤ ሳነብ ለምን ቅር አለኝ,,,?ቀንቼ ነው እንዴ?ፍቅር ሲይዝ እንዴት ነው የሚያደርገው?ስምንተኛ ክፍል ሆኖ ፍቅረኛ መያዝ ይቻላል እንዴ?››እነዚህንና መሰል ጥያቄዎች ባልጠና እና ለጋ ጭንቅላቱ ሲያወርድና ሲያወጣ እንዲሁ እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር ነጋ...፡፡ከዛን በኃላ በማግስቱ አናገራት ….እንደሚያፈቅራትና እሷ ፍቃደኛ ከሆነች ፍቅረኛው እንድትሆን እንደሚፈልግ ነገራት..እሷም በደስታ ፈንጥዛ እላዩ ላይ ተጠመጠመችበት….ከዛ የታዳጊነት ፍቅራቸው እስከ አስረኛ ክፍል ቀጠሉ…የበለጠ ጊዜ በሄደ መጠን በእነሱም መካከል ያለ ፍቅር እየደረጀና ስር እየሰደደ መጣ፡፡አስረኛ ክፍል በጀመሩ በሶስተኛው ወር አንድ ቀን ጥዋት የትምህርት ቤት ሰዓት ደርሶ ቀድሞ ወጥቶ ቢጠብቃት ልትመጣ አልቻለችም...ተማሪ ሁሉ ሄዶ ማለቁንና ሰዓቱ መርፈድንም ከግንዛቤ በማስገባት በለሊት ቀድማ መሄዶን ጠረጠረና በሩጫ ወደትምህርት ቤት...በረፍት ሰዓት ክፍሏ ሄዶ ቢያያት እንዳልመጣች ጓደኞቾ ነገሩት።ግራ ተገባ።
አስቴር ከትምህርት ቤት በቀላሉ የምትቀር አይነት ልጅ አይደለችም። ለትምህርቷ የምትሰጠው ትኩረት ቀላል የሚባል አንዳልሆነ ያውቃል…ታዲያ እንዴት?።እናም ያለ መምጣቷ ዜና አልተዋጠለትምና እሱም እንዳመመው በመናገር አስፈቅዶ ወደቤት ሄደ…ወደቤት የሄደበት ዋና ምክንያት የአስቴር እናት እንጀራ ልትጋግር ወይም ሌላ ስራ
ለመስራት ወደእነሱ ቤት የምትመጣበት ቀን ስለሆነ አስቴር ለምን እንደቀረች ሊጠይቃት ነበር እቅዱ፡፡እቤት ሲደርስ ግን ማንም አልነበረም..የአስቴር እናትም እንዳልመጣች በኩሽናው መቆለፍ አረጋገጠና ደብተሩን አስቀምጦ ወጣና ወደ እነአስቴር ቤት አመራ… ሰፈራቸው ሲደርስ እቤታቸው ፊት ለፊት ድንኳን ተተክሎ ነጠላ ያዘቀዘቁ ሴቶችና ጋቢ የደረብ ወንዶች ሲተረማመሱ ከሩቅ አየ...ሰውነቱ እስኪንቀጠቀጥ ድረስ ነው የደነገጠው፡፡
‹‹አስቱካ ምን ሆነች?››በሩጫ ነበር ተንደርድሮ ድንኳኑ መሀከል የተገኘው...አስቴር በአራት በሚበልጡ ሴቶች ግራና ቀኝ ተደግፋ ‹‹ወይኔ እናቴ እያለች›› ስትንፈራፈር ተመለከታት"ተመስገን"አለና ትንፋሹን ወደውስጥ እየሳበ ለመረጋጋት ሞከረ።‹‹ተመስገን
››ያለው እናቷ ስለሞቱ አይደለም...በፍፁም ።ይልቅ እሷ በህይወት ስላለችልለት ተደስቶ ነው።እንጂማ እናቷ ከህፃንነቱ ጀመሮ ከገዛ እናቱ በመቀጠል ያሳደጉት ያዘሉትና የመገብት ሴት ናቸው…….የእሳቸውም ሞት በጣም አስደንግጦታልም አሳዝኖታልም…
ከዛ ከሀዘን ቤት እስክትወጣም ሆነ ከዛ በኃላ ከስሯ አልተለየም።ግን እሷን ማፅናናት እና ወደ ህይወቷ እንድትመለስ ለማድረግ ቀላል አልሆነለትም።ምክንያቱም ለአስቴር እናቷን ማጣት እናትን ብቻ ሳይሆን መላ ዘር ማንዘሯን ማጣት ማለት ነበር።ምክንያቱም አባቷን ጭራሹኑ እሷ እንደተፀነሰች የሞተ እና ዘመዶቹንም የማታውቅ ሲሆን በተመሳሳይ እናቷም የረባ የቅርብ ዘመድ ያልነበራት ብቻዋን ወልዳ ብቻዋን ያሳደገቻት ነበረች እና እሷም ስትሞትባት ሌላ አይዞሽ የሚላትና የሚያፅናናት አንድም የቅርብ ዘመድ አልነበራትም።በኃላ የእናትና አባቱ ተማከሩና አስቴርን እንደልጃቸው አድረገው ወደቤታቸው አመጧት፡፡
ትዝ ይለዋል የአስራ አምስት አመት ልጅ እና የአስረኛ ክፍል ተማሪ እያለ ነበር…አስቴር የቤተሰቡ አባል ሆና የተቀላቀለች፡፡አዎ እሷ ስትመጣ እሱ ከእህቱ ጋር ከሚጋራው ክፍል ተፈናቀለና ሌላ ትልቁ ወንድሙ ለቆ ዩኒቨርሲቲ በገባበት ክፍል ከአመፀኛው ወንድሙ ጋር ደባል ሆኖ ገባ…
እድሜውን ሙሉ የኖረበትን ክፍልና የተኛበትን አልጋ እንዳለ ለአስቴር አስረከበ….እንደዛ በመሆኑ አልከፋውም….፡፡ለሌላ ሰው ልቀቅ የተባለ ቢሆን ኖሮ ከፍተኛ አብዬት ያስነሳ እንደነበር እርግጠኛ ነው….ለአስቴር ስለሆነ ግን እንደውም ደስ ያለው ይመስላል…እርግጥ እሱ ከመኝታው ሳይፈናቀል በእሱ ምትክ እህቱ እንድትለቅላት ቢደረግ ወይንም ሌላ ሶስተኛ አልጋ ወደክፍሉ እንዲገባ ተደርጎ እሷ እንድትተኛ ቢደረግ በጣም ደስተኛ ይሆን እንደነበር እርግጠኛ ነው..ግን ለምን ተብሎ ሊጠየቅ የማይችለው አባቱ ኮስተር ብሎ የወሰነው ውሳኔ ስለሆነ ያለምንም ማቅማማት ነው ተግባራዊ የሆነው፡፡
አስቴር ከእሱ በአንድ አመት ስትበልጥ ከእህቱ ስህን ደግሞ በሁለት አመት ታንሳለች…..ስለዚህ የሁለቱንም ጓደኛ ነች፡፡
ይሄ ውሳኔ በደስታ እንዲፈነጥዝ እና በወላጆቹም እንዲኮራ አደረገው።እና እህቱም ጓደኛውም ሆነች...።የነካኩት የፍቅር ጉዳይ ግን እንደተዳፈነ ቀረ...።
አስቴር ‹‹ እቤታቸውንም ልባቸውንም ከፍተው እንደገዛ ልጃቸው የተቀበሉኝን ሰዎች ልጃቸው ጋር ባልጌ አላሳዝናቸውም…እኔ እና አንተ ከአሁን በኃላ እህትና ወንድም እንጂ ፍቅረኛሞች መሆን አንችልም›› ብላ ቁርጥ ያለ ውሳኔዋን ነገረችው፡፡እሱ በቀላሉ ውሳኔውን ሊቀበል አልቻለም፡፡ይበልጥ ሊያጣት እንደሆነ ባወቀ ቁጥር ውስጡ የንዴት እሳት እየነደደ ይለበልበው ጀመር፡፡
እና ውሳኔዋን እንድትቀይርና እንድታስተካክል በወጣች በገባች ቁጥር ሲያስቸግራት እሷም እሱን ተስፋ ለማስቆረጥ እርምጃ ወሰደች…ስምንተኛ ክፍል ሆነው ደብዳቤ የፀፈላትን መስፍንን 11 ክፍል ፍቅረኛ አድርጋ ተቀበለችው፡፡
ከዛሬ ነገ እሱን ትታ ወደእኔ ትመለሳለች ብሎ በትእግስ ሲጠብቅ ሁለቱም 12ተኛ ክፍል ማትሪክ ተቀበሉና ዩኒቨርሲቲ ገቡ…ልክ በተመረቁ በ3ተኛ ወሯ መስፍን እነ ሰለሞን ቤተሰቦች ጋር አስቴርን ለማግባት ሽማጊሌ ላከ…ወዲያው ቀለበት አሰሩና ከሶስት ወር በኃላ ተጋቡ፡፡
በዚህን ጊዜ ሰለሞን ሁሉ ነገር አስጠላው…ሁሉን ነገር ጣጥሎ በትምህርት አሳቦ ወደውጭ የተሰደደበት ዋና ምክንያት የእሷ ማግባት ነበር…ለአመስት አመት እዛው ኖረና ድንገት ለመመለስ ወሰነ…ይሄንን ወደሀገር የመመለሱን ውሳኔ የወሰነበት ዋናው ምክንያትም  አስቴር ከ5 አመት የጋብቻ ቆይታ እና አንድ ልጅ ከወለዱ በኃላ ተፋተው እሱም ልክ እንደእሱ አገር ጥሎ እንደተሰደዱ ስለሰማ ምን አልባት ከአመት በፊት የተነጠቅኩትን ፍቅሬን መልሼ የማግኘት እድል ይኖራኛል በሚል ተስፋ ነበር የተመለሰው፡፡ከልጅነት እስከጎልማሳነት የዘለቀ እንቅፋት የበዛበት ውስብስብ ፍቅር…እና ሁሉ ጊዜ ስለራሱና ስለፍቅሩ ሲያስብ ‹‹ጠንቆይ ለራሱ አያውቅም እያለ ››ይተርታል..፡፡
እሱ ለላፉት ሶስትና አራት አመታት ለብዙ ሺ ጥንዶች እንዴት ያፈቀሩትን ሰው ማሳመንና የራሳቸው ማድረግ እንዳለባቸው..ፍቅራቸውን እንዴት መንከባከብ እንደሚገባቸው ውጤታማ ምክር እየሰጠ ተግባራዊ እንዲያደርጉት ሲጫናቸውና ደከም ያሉትንም ሲበሳጭባቸው ከርሞል..ግን የራሱን ከልጅነቱ ጀምሮ ሲያበቅለውና እየተንከባከበ ሲያሳድገው የነበረውን ፍቅር የሆነ ዘዴ ፈጥሮ ፍሬውን ለመብላት ፈፅሞ አልቻለም፣አሁን ግን ቆርጦ ነው የመጣው አዎ

20 last posts shown.