ከመጽሐፍት መንደር💠


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


አንብብ አዕምሮህ ልክ አንደባህር ይሰፋል። ወንዞችም ለአንተ መገበር ይጀምራሉ። አንተ ወደ ሰዎች ሳይሆን ሰዎችም ወደአንተ ይመጣሉ። ማንብብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!! አንብብ ብታነብ የሚቀርብህ ድንቁርና
🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩
🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨
🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥
ለማንኛውም አስተያየት
@manbabemuluyadergal_bot

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ጎራቤቶችን በመስደብ አቀያይሞታል… .ውበቷን አርግፎታል..አቅሞን አክስሟታል…እና ይሄን ሁሉ ስለሚያውቅ እንደውም በራሱ ጊዜ እቤቱን ለቆ ባይወጣ አንድ ቀን በተኛበት አንቃ ሁሉ ልትገድለው ትችላለች የሚል ተስፋ ነበረው፡፡እናትዬው ግን በዛ ሁሉ መከራ ውስጥም ሆና ከእሱ ጋር መኖር መቀጠሉን  እንዲህ አምርራ መፈለጎን ሲያይ ‹‹አባቴ ብቻ ሳይሆን እናቴም በሽተኛ ነች ››የሚል እምነት አደረበት፡፡‹‹አባቴ ሰውን በማሰቃየት የህይወት እርካታ የሚያገኝ ሲሆን እናቴ ደግሞ በገዛ ባለቤቷ በመሰቃየት የምትደሰት ነች ›› የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሰ፡፡

የአባትዬውን ቤቱን ለቆ ከወጣ በኃላ የተፈጠረው ሁለተኛው ችግር የኢኮኖሚ ነው፡፡አባቱ ከሚያገኘው ደሞዝ ቢያንስ ግማሹን ለቤት ወጪ ይሰጥ ስለነበርና ከቤት ከወጣ በኃላ ያ ስለተቆረጠ በቤት ውስጥ የኢኮኖሚ ችግር ተከሰተ… ምክንያቱም እናቱ ምንም ስራ ያልነበራት የቤት እመቤት ስትሆን ልጆቹም ገና ትምህርት ላይ የሚገኙ ነበሩ፡፡
አላዛር ግን ወዲያው አሰበና የእናቱ እናት አያቱ ጋር በመሄድ ሁኔታውን በማስረዳት የተወሰነ የመነገጃ ብር በመቀበል እቤታቸው ፊት ለፊት አንድ አነስተኛ ሱቅ ሰርቶ ሸቀጣ ሸቀጥ መነገድ እና ቤተሰቡን በገቢ መደጎም ጀመረ..ግማሽ ቀን ይማራል ግማሽ ቀን ደግሞ ይሰራል፡፡እሱ ትምህርት ቤት በሚሆንበት ጊዜ እህቶቹ ወይም እናቱ ይሸጡለታል…እና ቤተሰቡን በመደጎም እራሱንም ማሳደግ ጀመረ፡፡

አባትዬው ለቀው ከወጡ በኋላ ግን እናትዬ ሁለት አመት ሳይቆዩ ሞቱ፡፡የሀያ አምስት አመት ዱላ..ስድብና ስቃይ ያልገደላቸው.. የሁለት አመት የባላቸው ናፍቆት ነፍሳቸውን አሳጣቸው፡፡ይሄ አላዛርን ይበልጥ አባቱን እንዲጠየፍና እንዲጠላ ልክ አንደእናቱ ገዳይም እንዲያያቸው ዋና ምክንያት ሆነው ፡፡ከዛ በኋላ ትልቅ ሰው ለመሆን ወሰነ..ካለጊዜው አድጎ የራሱንም ሆነ እህቶቹን ኃላፊነት ወሰደ፡፡ንግዱ ላይ ጠንክሮ መስራት ቀጠለ..ተሳካለትም፡፡

💫
ይቀጥላል💫
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር


#Share #like እያደረጋቹ።



#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች


#ክፍል_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================

አላዛር አባቱን በጣም ይጠላል፡፡ለአባቱ ያለው ጥላቻ ለሰሎሜ ካለው ፍቅር ጋር በግራና  እና ቀኝ ጫፍ ላይ ካለው የሚዛኑ ዘንግ ላይ ቢንጠለጠሉ በእኩል ሌቭል ላይ ተንሳፈው ነው የሚታዩት፡፡ሰሎሜን መቼ ማፍቀር እንደጀመረ እንደማያውቀው ሁሉ አባቱንም መቼ መጥላት እንደጀመረ አያውቅም፡፡ብቻ ለአባቱ ያለው ጥላቻም ሆነ ለሰሎሜ ያለው ፍቅር በእድሜ ዘመኑ ሁሉ የነበረና ከእሱ የአካልና የአእምሮ እድገት ጋር ተያይዞ እያደገና እየጠነከረ የመጣ  ባለሁለት መልክ ስሜት  ነው፡፡

ሁል ጊዜ ስለአባቱ ሲያስብ አንድ የሚያስጨንቀው ነገር‹‹አሁን አባቴ ቢሞት አለቅሳለሁ?…››የሚለው ጥያቄ ነበር፡፡ ምክንያቱም በአባቱ መሞት ውስጡ እንደማያዝን ያውቃል…፡፡ካላዘነ ደግሞ እንዴት ብሎ እንባው  ሊመነጭለት ይችላል….?ለገዛ አባቱ ደግሞ ማልቀስ ካልቻለው  ቀሪው  ማህበረሰቡ ምን ይለዋል…?ይሄ ጉዳይ ሁል ጊዜ እንዳሳሰበው ነው፡፡ግን ደግሞ የሚፅናናው‹‹አረ እሱ አይሞትም….እንደእሱ አይነት ክፉና ፀያፍ ሰው እንኳን ሰው ሞት እራሱ ይሸሸዋል ››በሚለው እምነቱ ነው፡
አላዛር አባቱን ለመጥላት የቻለበት ዋናው ምክንያት ከህፃንነቱ ጀምሮ በሚወዳት እናቱ ላይ ያደርሰው የነበረውን ድብደባና በደል ጥርቅም ትውስታ በአእምሮው ስለታጨቀ  ነው፡፡አባትዬው በሳምንቱ ውስጥ ካሉ ሳባት ቀኖች ቢያንስ ስድስቱን እኩለ ለሊት ካለፈ በኃላ ሰክሮና ጥንብዝ ብሎ ነው ወደቤት የሚመጣው፡፡መስከሩና ውድቅት ለሊት በራፍን እያንኳንኳ የተኛውን የሰፈሩን  ሰው ሁሉ መቀስቀሱንና መረበሹ ብቻ አይደለም የሚያበሳጨው፡፡ተከፍቶለት ወደቤት ከገባ በኋላ ለአንድና ሁለት ሰዓት የሚያደርጋቸው ድርጊቶች ናቸው ይበልጥ አስፀያፈዎች፡፡ልክ እንደጀማሪ ሰባኪ ድምጽን ከጣሪያ በላይ ከፍ በማድረግ  በቀኝ ያለው ጎረቤቱን ወይም በግራ ያለውን ስም እየጠራ ጥንብርኩስን አውጥቶ ይሳደባል፡፡ስድቡን ከአባወራው ከጀመረ ወደሚስትዬው ይሸጋገርና ልጆቹ ላይ ያበቃል.፡፡በዚህ ጊዜ ታዲያ የአላዛር እናት ዙሪያውን እየተከተለች በመሳቀቅ ልታስቆመውና ዝም ልታስብለው ትጥራለች፡፡በዚህን ጊዜ በቡጢ ሲላት ከግድግዳ ጋር ትላተማለች፡፡.ትንሽ ትረጋጋና አሁንም ልታስተኛው ትጥራለች..በጠራባ ሊያነሳት ይልና እራሱ ተንሸራቶ ወለሉ ላይ ይዘረጋፋል…እንዳይጎዳባት ሮጣ ሄዳ ከወደቀበት ልታነሳው ስትሞክር በጥፊ አይነ-ስቧዋን ያቃጥልላታል … ያዞራትና ስሩ ሄዳ ዝርግት ትላለች፡፡

ይሄንን በየቀኑ መኝታው ላይ ሆኖ..ድብን ያለ እንቅልፍ ውስጥ ያለ ይመስል ዝርግትግት ብሎ..ትንፋሹን ለራሱ እንኳን እንዳይሰማ ወደውስጥ ውጦ.. በለበሰውን ብርድልብስ ቀዳዳ አይኖቹን አጨንቁሮ ይመለከታል…ተነስቶ እራስጌው ባለው የብረት ዘነዘና ሰካራም አባቱን  አናቱን መፈርከስና አናትዬውን ነፃ ማውጣት ይፈልጋል…ግን ምኞት ብቻ ነበር፡፡ያንን ለማድረግ ወኔ አልነበረውም፡፡አይደለም እንደዛ ለማድረግ ሞክሮ ይቅርና ድንገት እንቅስቃሴ ቢያሳይ እንኳን አባትዬው ትኩረቱን ከጎረቤት ወደእሱ ይመልስና ጎትቶ ከአልጋው ያስነሳዋል…በዛ ውድቅት ለሊት የሆነ ሰበብ ፈጥሮ ተንበርከክ ይለዋል…ሲንበረካክ በኩርኩም አናቱን ያነደዋል..እናትዬው እንዳይጎዳባት በመሀከላቸው ስትገባ ቡጢውናና ጥፊውን ያለስስት ይሸልማታል… መጮጮኸና ትርምሱ በእጥፍ ይበዛል፡፡
ያንን ስለሚያውቅ ገና የአባቱን ድምፅ ከውጭ ሲሰማ በድን ሆኖ እራሱን ይቀብራል…በምንም ነገር ጣልቃ ላለመግባት እስከመጨረሻ ከስሜቱ ጋር ይታገላል.. እናቱም እንደዛ እንዲያደርግ ነው የምትመክረው..ዘወትርም የምትለምነው፡፡
አላዛር….አባቱ በእውነታው አለም ተጫባጭ ሰው አይመስሉትም፡፡.የሆነ ንክ ደራሲ ለገፀ ባህሪነት ፈልጎ አጣሞና አወላጋግዶ  የሳላቸው ንክ ሰው ነው የሚመስሉት፡፡ ምክንያቱም ሲጠጡ ሰይጣን …መጠጥ ባልቀመሱበት ሰዓት  ደግሞ ፍጽም መልአክ መሰል ሰው ናቸው፡፡
ሲሰክሩ ለሊቱን ሙሉ ሲሰድብት ያደሩትን ጎረቤት ጥዋት ተነስተው ወደስራ ሲሄዱ በራፍ ላይ ካገኙት መሬት እስኪደርሱ ለጥ ብለው ሰላም ብለውት ፤አቅፈው ተከሻውን ወዝውዘውት …ቸገረኝ ካለ ኪሳቸው ገብተው ሸጎጥ አድርገውለት …የሚስቱን ደህንነት የልጆቹን ሰላም መሆን ጠይቀውት መንገዳቸውን ይቀጥላሉ፡፡
‹‹ማታ ምነው እንዳዛ የሰደብከኝ?››ብሎ ሚጠይቃቸው ካለ…‹‹አረ በፈጣሪ..ምን ይሁነኝ ብዬ አንተን የመሰለን ወዳጄን ሰድባለው…?.እማይሆነውን››ከማለት ውጭ አንድም ነገር አያስታውሱም፡፡ብዙውን ጊዜ እንደውም ጥዋት ሲነሱ የሚስታቸው ጉንጭ አብጦ ..ወይም አይኖቻቸው ቀልቶ….ወይንም ደግሞ እጆቾ ተስብረው…ሲያዩ ኡኡ አገር ይያዝልኝ..ሚስቴን ማነው እንዲህ ያደረጋት? ብለው እስከማልቀስ ይደርሳሉ፡፡ሁለተኛ መጠጥ ላለመቅመስ ምለው ይገዘታሉ፡፡ በከንፈራቸው መሬት ስመው የሚስታቸውን ይቅርታ ጠይቀው በፀፀት እያጉረመረሙ ወደስራ ይሄዳሉ…ማታ ሲመጡ ግን እንደተለመደው ጥንብዝ ብለው  ነበር ወደቤታቸው የሚመለሱት፡፡››
በዚህም የተነሳ የሰፈር ሰው ሆነ ወዳጅ ዘመድ ሁሉ‹‹ እሱ እኮ መጠጥ ሲጠጣ አብሾ ስላለበት ነው…››በሚል  የሽፋን ምክንያት ጥፋቱን ሁሉ ይቅር ይሉታል፡፡አላዛር ግን ይሄ የአባቱ የማጭበርበሪያ ዘዴ  እንደሆነ አድርጎ ነው የሚቆጥረው… ከለሊቱ ድርጊታቸው በላይ የጥዋት ማስመሰላቸውና እንደተፀፀቱ ጠብ እርግፍ የሚሉት የማስመሰያ ድራማ እና የማደናገሪያ ዘዴያቸው እንደሆነ ስለሚያምን  ይበልጥ ይበሽቅባቸዋል፡፡የት እንዳነበበው ባያውቅም ‹‹እንደምትቀየር እርግጠኛ ካልሆንክ ይቅርታ አትጠይቅ››የሚል አባባል እንዳለ  ያስታውሰዋል፡፡አባቱ ሁል ጊዜ ጥፋት እንደሰሩ… ቀጥሎ ይቅርታ እንደጠየቁ ነው፡፡.ግን አንድም ቀን ቅንጣት ያህል እንኳን የመለወጥ ተነሳሽነት አግኝቶባቸው አያውቅም፡፡

አላዛርና እህቶቹ እያደጉ ሲመጣ ግን አባትዬውን ለመታገስ ያላቸው ትዕግስት እየተመናመነ ሄደ…አባትዬውን መክሰስ እና  ማሳሰር ….እናትዬውን ሊያጠቃ ሲል መሀከል መግባት ሲጀምሩ የአባትዬውም ተስፋ እየተሞጠጠና ብስጭታቸውም ከእለት ወደእለት እየጨመረ ሄደ፡፡በስተመጨረሻ እቤቱን ለቆላቸው ወጣና  ሌላ ሰፈር ሌላ ቤት ተከራይቶ ገባ፡፡

በዛን ጊዜ የአላዛር እድሜ 14 ዓመት አካባቢ ነበር እህቶቹ ደግሞ 19 እና 24 ዓመታቸው ፡፡በቤቱ በዘመናቸው አይተው የማያውቁት ነፃነትና ሰላም ሰፈነ…ግን ደግሞ ሌላ ሁለት ችግር ተከሰተ ፡፡አንደኛ በአባትዬው እቤቱን ለቆ መውጣትና ትዳሩን ማፍረስ እናትዬው በጣም ሀዘንተኛ ሆነች፡፡ከአሁን አሁን ተመልሶ ይመጣል ብላ በተስፋና በናፍቆት መጠበቅ..ተስፋዋ አልሰምር ሲል አይኗ እስኪደክም ማልቀስ…የነፍስ አባታቸውንና ሌሎች ሽማግሌሎችና የአባቱን ጎደኞች በየተራ  እየለመነችና እየተማፀነች ባለቤተዋ ጋር ሽምግልና መላክ…ቆሚ ስራዋ ሆነ፡፡

ይሄ የእናትዬው ድርጊት ከአላዛር የማሳብ አቅም በላይ ነበር የሆነበት፡፡አባትዬው እቤቱን ለቆ መውጣቱን ሲያውቅ መጀመሪያ በአእምሮ የመጣለት እናቱ እንዴት ከመጠን በላይ  ደስታኛ ሴት እንደምትሆን ነበር፡፡ምክንያቱም ይሄ ሰው እናቱን ቢያንስ ከሀያ አመት በላይ አሰቃይቷታል..ከሚወዷትና በድሎት ሊያኖሯት ከሚችሉ ሀብታም ቤተሰቦቾ አቋራርጧታል… ደብድቧታል….. አቁስሏታል.. አስርቧታል… ልጆቾን በመደብደብ አሳቆታል..


አለቅየው የሚወዳት ጸሐፊውን..."ቀጣይ ሳምንት እረፍት ስለሆንኩኝ ወደ ውጪ ሀገር እንሄዳለን ተዘጋጂ" ...ይላታል

ጸሐፊዋም ወደ ባሏ ደውላ... "እኔ እና አለቃዬ ቀጣይ ሳምንት የሥራ ጉዞ አለን...ልጆቹን ትንከባከባለህ"...ትላለች

ባልየውም ውሽማው ጋር ደውሎ "ሚስቴ መንገድ ልትሄድ ነው ቀጣይ ሳምንት በነጻነት አብረን ነን..."ይላል።

ውሽማዋ ደግሞ በግል የምታስጠናው ልጅ ጋር ደውላ "ቀጣይ ሳምንት ሌሎች ፕሮግራሞች አሉብኝና ጥናት አይኖረንም" ብላ አመቻቸች...

ትንሹ ልጅ አያቱ ጋር ደውሎ "አያቴ..! አስጠኚዬ ቀጣዩን ሳምንት አልኖርም ብላለችና ከአንተ ጋር ባሳልፍ ደስ ይለኛል..."

አያትየው ጸሐፊዋ ጋር ደውሎ "የነገርኩሽን ጉዞ መሄድ የምንችል አይመስለኝም...የልጅ ልጄ ሳምንቱን ከእኔ ጋር ማሳለፍ ይፈልጋል... ስለዚህ ሰርዢው..."ይላታል።

ጸሐፊዋም ባሏ ጋር ደውላ "አለቃዬ የግል ጉዳይ ገጥሞት ጉዞውን ሰርዞታል...ስለዚህ እዚሁ ነኝ ስለልጆቹ አታስብ..."ትለዋለች።

...ባልየውም ውሽማው ጋር ደውሎ "ቀጣይ ሳምንት አብረን እንሆናለን ያልኩሽን ተይው ባለቤቴ ጉዞውን ሰርዛለች..."ይላታል።

ውሽማዋ የምታስጠናው ልጅ ጋር ደውላ "ፕሮግራሜ ተስተካክሏል ቀጣይ ሳምንት ጥናታችንን እንቀጥላለን ተዘጋጅ..."ትላለች።

ልጅም አያቱ ጋር ደውሎ "አስተማሪዬ ደውላ ቀጣይ ሳምንት ጥናት እንዳለብን ነግራኛለች እና አብረን ማሳለፍ እንደማንችል ልነግርህ ነው አያቴ..."ይለዋል።

አያትየው በድጋሚ ጸሐፊዋ ጋር ደወለ..."የልጅ ልጄ ቀጣይ ሳምንት አብረን እናሳልፍ ብሎኝ ነበር ነገር ግን አስተማሪው ደውላ ትምህርት እንዳለ ነግራዋለች....ስለዚህ...

ማነው ይህንን አዙሪት እያጦዘው ያለው?
🤔😂😂😂
(በዘመላክ እንድርያስ)


እንደምን ዋላችሁ ዛሬ አዲስ ትረካ ለመጀመር አስበናል ምረጡ ከፍተኛ ድምፅ ያገኘው ዛሬ ይጀመራል
Poll
  •   የድንግሊቷ አፍቃሪ ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ
  •   ዲያሪው ደራሲ ፍስሃ ክፍሌ
22 votes


እዚህ ይገኛሉ ..የእኛና የአቶ ለሜቻ ቤተሰብ፡፡ይሄ ሁለት ቤተሰብ የተሳሰረው ዛሬ አብራን በሌለችው በበሬዱና አጠገባችን ባለችው በፀሎት ነው፡፡የእኔ ልጅ ዛሬ በህይወት ያለችው ከበሬዱ በተሰጣት ልብ ነው፡፡እዚህ እነአቶ ለሜቻ ቤት ለሟች ልጃቸው የሙት አመት መታሰቢያ ሲከበር በእኛ ቤት ግን ለልጃችን ንቅለ-ተከላ ተደርጎላት ዳግም የመኖር እድል ስላገኘች ድል ያለ የምስጋና ድግስ እናዘጋጅ ነበር ..ዘንድሮ ግን በፀሎት ውሳኔ እንደዛ ማድረግ አልቻልንም…እዚህ ግቢ አንድ ላይ መታሰቢያውንም ምስጋናውንም አብረን እንድናከብር ወስነናል..አሁን ሁላችንም ወርደን የተዘጋጀውን ዝግጅት እንታደም፡፡››የሚል ንግግር ካሰሙ በኃላ በራፉ ተከፈተ …
ዛሬ እየሆነ ያለው ነገር በጠቅላላ ምንም ያልገባቸው አቶ ለሜቻና ወ.ሮ እልፍነሽ አቶ ኃይለልኡልንና ባለቤታቸውን ተከትለው ከባስ ወረዱ፡፡ይሄንን ሰፈራ የሚገኘው በገዛ ቀበሌያቸውና በሰፈራቸው ስለሆነ በደንብ ያውቁታል፡፡ግቢው ንብረትነቱ የቀበሌው ሲሆን  ባለ5 ሺ ካሬ ግዙፍ ጊቢ ነው…ከመኪና ወርደው ሲመለከቱ ግቢው በሰዎች ታጭቆል ፡፡ ሰዎቹ ደግሞ አብዛኛው ጎዳና ተዳዳሪዎች፤የኔ ቢጤዎች የደከሙና የተጎዱ አቅመ ደካሞች…..ለአይን እንኳን ተቆጥሮ የማያልቅ የእንጀራ ክምር ..በበርሜል የተደረደረ ልዩ ልዩ የወጥ አይነት…ራቅ ብሎ ደግሞ በተንጠልጣይ ብረት ላይ የተደረደረ ጥሬ ስጋ እንደተራራ የተቆለለ የታሸገ ውሀ……

በሌላ ጎን ከአዳራሹ ፊት ለፊት ግዙፍ ፖስተር ይታያል…በፖስተሩ ላይ በቀኝ የበሬዱ ፎቶ በስተግራ ደግሞ የበፀሎት ፎቶ መሀከል ላይ የበሬዱ በፀሎት የምገባ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ይላል፡፡ብዛት ያላቸው ጋዜጠኛች ከወዲህ ወዲያ እየተዘዋወሩ ፎቶ ያነሳሉ ኢንተርቪው ያደርጋሉ፡፡
ማታ በሁለት ሰዓት ዜና ላይ በኢትዮጴያ ቴሌቭዝን የቀረበው ዜና የሚከተለው ነበር….
‹‹የታዋቂ የቢዝነስ ማን አቶ ሃይለልኡል ብቸኛ ልጅ ከጠፋችበት መገኘቷ ታወቀ…በፀሎት ከሶስት አመት በፊት ልቧ መስራት አቁሞ የነበረ ሲሆን በዛን ወቅት የመኪና አደጋ ደርሶባት አብራት ለህክምና ወደ ታይላንድ የሄደችው በሬዱ ለሜቻ ህይወቷ በማለፉ አባትዬው በሰጡት ፍቃድ መሰረት ልቧን ለበፀሎት በመለገሷ የልብ ንቅለ-ተከላ ሊደረግላትና ድና ወደሀገር ልትመለስ ችላለች…ባለፈው ወር የጠፋችው በፀሎት ኃይለልኡል የተገኘችው በእነዚሁ በአቃቂ ክፍለከተማ በሚኖሩት ልብ በለገሰቻት ልጅ ቤተሰቦች ቤት መሆኑ በጣም አነጋጋሪና አስደማሚ ታሪክ ሆነዋል፡፡
በዛሬው እለት የበሬዱ የሶስተኛ አመት የሙት አመት መታሰቢያ የነበረ ሲሆን በተመሳሳይ ሁኔታ ባለፉት ሁለት አመት እንደተደረገው በአቶ ኃይለልኡል ቤት የምስጋና ድግስ ሲደገስ የቆየ ቢሆንም..ዛሬ ግን ይሄ ቀርቶ አቶ ኃይለልኡልና ቤተሰባቸው በቤታቸው የደገሱትን ድግስ ሙሉ በሙሉ ሰርዘው በሞች በሬዱ ለሜቻ የትውልድ አካባቢ ለስሟ መታሰቢነት እንዲሆን ከዛሬ ጀምሮ በአካባቢው አቅም የሌላቸውና ችግረኞችን በቀን ሁለት ጊዜ የሚመግብ በሬዱ በፀሎት ምገባ ተቋምን ከፍተው ያስመረቁና በቦታውም ከ500 በላይ ሰዎችን በመመገብ ማስጀመራቸውን ማወቅ ተችሏል፡፡
በዚህም የሞች አባት የሆኑት አቶ ለሜቻ ስለሁኔታው ሲናገሩ‹‹በእውነት ልጄ ዛሬ ሞትን ድል ነስታ እንደተነሳች ነው የምቆጥረው..ልጄ በህይወት እያለች ለተቸገረ ሁሉ የምታዝን የዋህ ነበረች..አሁንም ከሞተች በኃላ ይሄው በስሟ ብዙዎች ጠግበው እንዲያድሩ ምክንያት ስለሆነች ኮርቼለሁ….ይሄንን እውን ያደረጉትን አቶ ኃይለልኡል እና ባለቤታቸውን አመሰግናለሁ….የእነሱ ልጅ የሆነችው በፀሎት ለእኔም ልጄ ነች….ከአሁን በኃላ በሬዱ ሞተች ብዬ አላዝንም…. ስትናፍቀኝ በፀሎትን አቅፌ አፅናናለሁ…ደግሞ እዚህ ስፍራ መጥቼ በስሟ ሰዎች ምግብ ቀምሰው ሲያድሩ ተመልክቼ ረካለው››በመላት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል…የሚል ነበር፡፡

ከድግሱ በኃላ አቶ ኃይለልኡልና ወ.ሮ ስንዱ ወደቤታቸው ሲሄዱ በፀሎት ግን ለሊሴን ተከትላ ወደእነሱ ቤት ነበር የሄደችው…በማግስቱ ግን ቤተሰቡ በአጠቃላይ ተሰብስበው ወደቦሌ ሄዱ ፡፡ሲደርሱ ሰለሞንም ነበር….ይህ ዝግጅትና ግንኙነት ለሁለቱም ቤተሰብ ልክ እንደቅልቅል ነው፡፡በዚህ ደግሞ ቁጥር አንድ የፈነጠዘችው በፀሎት ነች፡፡የእሷን ደስታና ፈንጠዝያ ሲከታተል የነበረው ሰለሞን ‹‹እሺ ይህቺን ልጅ ለማግባት ልጃችሁን ስጡኝ ብዬ ሽማግሌ ምልከው ለየትኛው ቤተሰብ ነው፡፡ብሎ እራሱን ጠየቀና ፈገግ አለ፡፡‹‹ግድ የለም እሷ ትስማማ እንጂ እኔስ ሁለት የሽማግሌ ቡድን ማቋቋም አያቅተኝም፡፡›› ሲል ለራሱ መልስ ሰጠ፡፡በተመሳሳይ ሁኔታ ፊራኦልም ከሰለሞን ጎን ተቀምጦ ፊት ለፊቱ በፀሎትን እየተመለከተ በውስጡ ‹‹እሺ አሁን የእህቴን ልብ ተሸክማ እህቴ ስለሆነች ልደሰት ወይስ. ፍቅሬን ተቀብላ ፍቅረኛዬ መሆን ስለማትችል ልከፋ?››በውስጡ የሚያመነዥገው ጥያቄ ነበር፡፡‹‹ፍቅሯ በዚሁ ቀጥሎ ከባሰብኝ ምንድነው የማደርገው?››በጣም ተጨነቀ፡፡

ተፈፀመ።

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


አስታየታችሁን አስፍሩልን አዲስ ትረካ ለመጀመር ስላሰብን


‹‹ከመቀመጫዋ ተነሳችና እላዩ ላይ ተጠምጥማ ጉንጩን እየሳመችው‹‹….የእኔ ወንድም
…..በጣም ነው የምወድህ……››አለችው
‹‹እኔም እህቴ በጣም ወድሻለው…አሁን እራት እየቀረበ ነው መሰለኝ ወደቤት እንግባ…››
‹‹እሺ እንግባ››ተባባሉና ተያይዘው ወደቤት በመግባት ከቀረው ቤተሰቡ ጋር ተቀላቀሉ፡፡
//
አቶ ለሜቻና ቤተሰባቸው በአጠቃላይ ሙሉ ትኩረቱ የበሬዱ የሶስተኛ አመት የሙት አመት መታሰቢያ ላይ ነው፡፡ይሄ ባለፈው ሁለት አመት በተመሳሳይ የመታሰቢያ ድግስ የተደገሰ ቢሆንም የዘንድሮ ግን በተለየ ሁኔታ ትኩረት ተሰጥቶታል ፡፡የዚህም ምክንያት በቤተሰቡ ውስጥ ተአምራዊ በሆነ መንገድ በፀሎት የምትባል ልጅ ስለተጨመረችና ከዛም ተያይዞ ከሞላ ጎደል የቤተሰቡ የገንዘብ ችግር ስለተሻሻለ፤ ከዚህ በፊት ከነበረው ከፍ ባለ ሁኔታ ለመደገስና በሟቾ ስም በርከት ያሉ ችግረኞችን በማብላት ነፍስ ይማር በማሰኘት የተወሰነ የመንፈስ እረካታና የአእምሮ መረጋጋት ለማግኘት ጠንክረው በጥሩ ሞራል እየደገሱ ነው፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ አቶ ኃይለልኡል ቤት በአይነቱ ለየት ያለ ድብልልቅ ያለ ድግስ እየተደገሰ ነው፡፡የእነሱ ምክንያት ደግሞ ሚያዚያ 20 ቀን የልጃቸው በፀሎት የልብ ንቅለተከላ ያደረገችበትና ሁለተኛ የመኖር እድል ያገኘችበት ስለሆነ ያንን ቀን በፌሽታና በምስጋና የማሳለፍ አላማ ያለው ነው፡፡ይሄንን ድግስ ያለፉትን ሁለት አመታት አድርገውታል፡፡ የዘንድሮው ግን በአይነትም ሆነ በመጠን ከፍ ያለ ነው፡፡ይሄም ዘንድሮ ሁኔታዎች የተለዩ

ስለሆኑ ነው፡፡ከቤታቸውም ከፊታቸውም የተሰወረችው የልጃቸው በፀሎት ከወር በኃላ ወደቤቷ ምትመለስበት ቀን ይሆናል የሚል ጉጉት ስላላቸው ልጃቸውን እጥፍ ድርብ በሆነ ፌሽታ ለመቀበል ያደረጉት ነው፡፡ከዚህም በተጨማሪ ሌላ የተለየ ምክንያት አላቸው ፡፡ባልና ሚስቶቹ ለአመታት ከገቡበት አስጠሊታ ግንኙነት እና የእርስ በርስ ጥላቻ ተገላግለው. ቀሪ ህይወታቸውን በመከባበር እና በፍቅር ለማሳለፍ ወስነውና ተስማምተው ቀሪ እንደአዲስ ለመጀመር የወሰኑበት ወቅት ስለሆነ ለእነሱም እንደ ዳግማዊ ሰርግ ነው…ለዛ ነው የተለየና እንከን አልባ ድግስ እንዲሆን እየጣሩ ያሉት…ያው እንደተለመደው የድግሱን ቅንጅት በሀላፊነት የወሰዱት ፕሮፌሽናል ባለሞያዎች ናቸው፡፡
የጭንቁ ቀን ደርሶል ፡፡አቶ ለሜቻና ወይዘሮ እልፌ ከሌሎች ጎረቤቶች ጋር በለሊት ነው ወደ ቤተክርስቲያን ሄደው ቅዳሴ የገቡት…በጸሎትን ጨምሮ ሌሎቹ ልጆች ግን ወደ ቤተክርስቲያን የሚወሰደውን ምግብና መጠጥ ሲያዘጋጁ ከቆዩ በኃላ አንድ ሰዓት ተኩል ሲል ዳቦ፤ እንጃራና ጠላውን በፒካፕ መኪና እስጭነው ቤተክርስቲያን በመውሰድ ለቄሶቹ የተዘጋጀውን ወደሰንበቴ ቤት አስገብተው ሌላውን ውጭ አስቀምጠው ቅዳሴው እስኪገባደድ መጠበቅ ጀመሩ ፡፡ልክ ቅዳሴው ተጠናቆ ሁሉም እንደወጣ አቶ ለሜቻና ወይዘሮ እልፌ ከቄሶቹ ጋር ወደሰንበቴ ቤት ቄሶቹንና ሌሎች ምዕመናንን ለማሰተናገድ ሲገቡ፡፡ በፀሎትና እና ለሊሴ ደግሞ ከሌሎች የሰፈር ወጣቶች ጋር በመሆን ቤተክርስቲያኑ የውጭ አጥር ጋር ተኮልኩለው ለሚገኙ የእኔ ቢጤዎችና፤ ምፅዋት ጠያቂዎች አንድ እንጀራ በወጥ ፤አንድ ጉማጅ ዳቦና አንድ ሀይ ላንድ ጠላ ለእያንዳንዱ እያደሉና ነፍስ ይማር እያስባሉ ካጠናቀቁ በኃላ ዕቃቸውን ሰብስበው እነአቶ ለሜቻ ከሰንበቴ ቤት እስኪወጡ መጠበቅ ጀመሩ…ሁሉ ነገር ከተጠናቀቀ በኃላ ቤተሰቡ ወደቤታቸው ከመመለሳቸው በፊት ቀጥታ ተያይዘው ወደበሬዱ መቃብር ነው የሄዱት፡፡የእሷ ምስል ያለበት ጥቁር ቲሸርት የለበሱት አስራ ምናምን ሰዎች የሀውልቱን ዙሪያ ገባ ከበው በዝምታ ሲፀልዩና አንዳንዱም ሲያነባ ከቀዩ በኃላ ሁሉም ቀስ በቀስ ስፍራውን እየለቀቁ ሄዱ…በመጨረሻ የቀሩት በፀሎት አቶ ለሜቻና ወ.ሮ እልፍነሽ ነበሩ፡፡
በፀሎት ይሄንን የልጅቷን ሀውልት ስታይ በጣም ትልቅ የሆነ ሀዘን ነው የተሰማት…‹‹በእሷ ምትክ..እኔ ነበርኩ እዚህ ስፍራ ከዚህ ሀውልት ስር መተኛት የሚገባኝ››ብላ ስታስበው እራሱ ዝግንን አላት…ልክ እንደሁል ጊዜውም የሌላን ሰው ህይወት ሰርቃ እየኖረች እንዳለች አይነት ስሜት ነው እተሰማት ያለው….የሚቀፍ አይነት ስሜት…›

አቶ ለሜቻ በዝምታ ሲያስተውሏት ስለቆዩ ያመማት መሰላቸው…‹‹ለማታውቃት ልጅ ይሄን ያህል ሀዘን ከየት የመጣ ነው?››በውስጣቸው ያብሰሰሉት ሀሳብ ነበር፡፡ በዝምታ ወደእሷ መጥተው ትከሻዋን በመያዝ…‹‹ልጄ በቃ እንሂድ ይበቃል››ሲሏት ከገባችበት ጥልቅ የመደንዘዝ ስሜት ባነነችና ቀና ብላ አየቻቸው…ትከሻዋን አቅፈው በፍቅር እየተመለከቷት ነው፡፡በሶስት ሜትር ርቀት ፈንጠር ብለው ወ.ሮ እልፍነሽ እያነቡ ይታዬታል…የአቶ ለሜቻን እጅ ያዘችና ‹‹አባዬ ና..››ብላ ወስዳ ከባለቤታቸው ጎን አቆመቻቸውና…ሁለቱም እግር ስር ድፍት ብላ አንድ አንድ እግራቸውን በመያዝ…‹‹አባዬ እማዬ እኔን ይቅር በሉኝ….በበሬዱ ይዣችኃለው ይቅር በሉኝ….ይቅር ካላላችሁኝ መኖር አልችልም….የእውነቴን ነው የምላችሁ ይቅርታችሁን ካላገኘው ሞታለው፡፡››ስትል ሁለቱም በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ…ምንም እየገባቸው አይደለም….‹‹ምን አጥፍታ ነው…?ምንስ ብታጠፋ ይቅርታ መጠየቂያው ቦታና ጊዜው ትክክል ነው?፡፡››በውስጣቸው የተፈጠረ ጥያቄ ነበር…ሁለቱም ግራና ቀኝ ትከሻዋን ይዘዘው ቀና ሊያደርጎት ሞከሩ ..ግን እልቻሉም፡፡
‹‹ይቅርታ ካላደረጋችሁልኝ አልነሳም››
‹‹ምን አጥፍተሸ ነው? ምንም አልገባንም እኮ››አቶ ለሜቻ ጠየቋት፡፡
‹‹አጭበርብሬችኃለው ..ዋሽቼያችኃለው..እኔ እናንተ ጋር የመጣሁት ከእንጀራ አባቴ ጠፍቼ አይደለም….››
‹‹እና ምን ሆነሽ ነው?፡፡››ወ.ሮ እልፍነሽ ጠየቁ፡፡
‹‹እኔ ማለት …የልጃችሁን ልብ በውስጤ ተሸክሜ የምዞር..በእሷ ምክንያት እየተነፈስኩ ያለው ልጅ ነኝ…..፡፡››
ሁለቱም የሚሰሙትን ለማመን አልቻሉም ..አቶ ለሜቻ ቀስ ብለው ትከሻዋን ይዘው አስነሷት…ፊቷን የተሻፋፈነችበትን ሻርፕ ቀስ ብለው ከላዮ ገፈፉና ጣሉት.. ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ ፊቷን ተመለከቱት‹‹አዎ እራሷ ነች››ትከሻዋን ያዙና ደረታቸው ላይ ለጠፏት…ግንባሯን፤ ጉንጮን፤ ፀጉሯን እየደጋገሙ ሳሟት‹‹….ልጄ አዎ አውቄው ነበር..አንቺ ወደቤቴ ያለምክንያት እንዳልመጣሽ ታውቆኝ ነበር….ከዛሬ ነገ ጥላኝ ትሄዳለች በሚል ስጋት ስሳቀቅ ነበር..አሁን ግን የራሴው ልጅ ነሽ የትም አትሄጂም..አዎ የራሴው ልጅ ነሽ››ተንሰፈሰፉላት….ፍፁም ያልጠበቀችውን ምላሽ ነው ያገኘችው፡፡
‹‹አዎ አባዬ ያንተው ልጅ ነኝ…ዘላለም ካአንተ መለየት አልችልም…እማዬ እኔ ልጅሽ ነኝ››ሶስቱም አንድ ላይ አርስ በርስ ተቃቅፈው ለበርካታ ደቂቃ ተላቀሱ ..በመከራ ነበር አካባቢውን የለቀቁት…ሁሉም የቤተክርስቲያኑ በራፍ ላይ ተሰብስበው እየጠበቋቸው ነበር….ግን በፊት ከነበሩት በተጨማሪ የበፀሎት እናትና አባት ልዩ አይነት ባስ መኪና አጠገብ ቆመው በራፍ ላይ ሲጠብቋቸው ነበር..ይሄ ደግሞ እነአቶ ለሜቻን ብቻ ሳይሆን በፀሎትንም ጭምር ነበር ያስደነቃት…እርስ በርስ ተቀራርበው ሰላምታ ከተለዋወጡ በኃላ ሁሉም በመኪና ውስጥ እንዲገቡ ተደረገ…በመኪና ውስጥ ጠቅላላ 25 የሚሆኑ ሰዎች ገቡ…ሹፌሩ መኪናውን ወደእነ አቶ ለሜቻ ቤት አቅጣጫ መንዳት ጀመረ…ቤታቸው ለመድረስ ግማሽ ኪሎ ሜትር ያህል ሲቀረው ግን ወደግራ ተጠመዘዘና አንድ ግቢው ውስጥ ገባ..ሁሉም ግራ ተጋባ….አቶ ኃይለልኡል መኪናው እንደቆመ በራፈ ከመከፈቱ በፊት ከተቀመጡበት ተነሱና መናገር ጀመሩ‹‹ ..ይቅርታ የማታውቁኝ ካላችሁ ኃይለልኡል እባላለሁ…የበፀሎት አባት ነኝ…በዛሬው ቀን በደም የተጣመሩ ሁለት ቤተሰቦች


የመጨረሻ ክፍል
ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያስምንት

ድክምክም ብሎታል፡፡ግን ደግሞ አልጋው ላይ ተኝቷ በሀሳብ እየተንገላታ ነው፡፡ ሰለሞን በሁለት በኩል ስለት ባለው ሰይፍ የሚጫወት ህፃን አይነት ሰው እንደሆነ እየተሰማው ነው፡፡ሞያውን በተመለከተ ለሶስት አመት በከፍተኛ የፕሮፌሽናል ደረጃ በምድረ-አሜሪካ ሲሰራ አንድም ጊዜ እንደዚህ አይነት ክፍተት ተከስቶበት አያውቅም..በዛም በራሱ ሲመካና ሲኮራ ኖሮ ነበር፡፡አሁን ግን ወደሀገሩ ተመልሶ ባጋጠሙት የመጀመሪያ ደንበኞቹ ከፍተኛ የሚባል ሽንቁር ተከስቶበታል፡፡አንድ ባለሞያ የሞያውን ስነምግባር አክብሮ ስራውን መስራት የሚገደደው ለደንበኞች ደህንነትንና ጥቅም ሲባል ብቻ አይደለም…ለራሱ ለሞያው ክብርና ተቀባይነትም እያንዳንዱ ባለሞያ የስራ-አፈፃፀም ሁኔታ ትልቅ ድርሻ አለው፡፡በሙስናና በጥቅማጥቅም የሚታለሉ ዳኞችና አቃቢ-ህጎች በሞሉበት ሀገር ፍርድቤት ሊከበርና ሊታመን አይችልም፡፡ሌላውም ሞያ እንደዛው ነው፡፡ ይህን ስራ ከጀመረ ያጋጠመችው ትልቋ ደንበኛው በፀሎት ነች፡፡እርግጥ ቀጥታ ደንበኛው እሷ ሳትሆን ወላጆቾ ናቸው፡፡ከእነሱ ጋር እየሰራ ያለውን ስራ የሞያው ስነምግባር በሚፈቅደው መንገድ ጥርትና ጥልል አድርጎ እየሰራ ነው፡፡ቢሆንም ቀጥታ ቀጣሪው ልጃቸው በፀሎት ነች፡፡እሷ ፍላጎቱን ተረድታ አፈቅርሀለው ብትለው እንኳን ፍቅሯ እሱ ለወላጆቾ በሚያደርገው የሞያ ድጋፍ ተፅዕኖ ስር የወደቀ ወይንም በይሉኝታ ስሜት የተቀነበበ ሊሆን ይችላል…ይሄንን ማንም በእርግጠኝነት ማወቅ አይችልም…በዚህም ምክንያት ከእሷ ጋር ደግሞ ያለው ግንኙነት እየሄደ ያለበት መንገድ ትክክል እንዳልሆነ ያውቃል፡፡ከሞያ ስነምግባር ውጭም እንደሆነ ያምናል፡፡ይሄ ጉዳይ ነው በጣም እያስጨነቀው ያለው፡፡ ከበፀሎት ጋር የፍቅር ስሜት በተሰማበት ቅፅበት ሁለት ምርጫ ነበረው፡፡አንድም በእሷ ቀጣሪነት ወላጆቾን ለማከም የተዋዋለውን የስራ ውል አፍርሶ ነፃ መውጣትና.. ከልሆነም ልቡን ገስፆ እና ፍቅሩን በውስጡ አክስሞ ስራው ላይ ብቻ አትኩሮ መቀጠል፡፡ቢያንስ ስራውን በተዋዋለው መሰረት ሙሉ በሙሉ አጠናቆ እስኪጨርስ ድረስ እንደዛ ነበር ማድረግ ያለበት፡፡ግን ይሄው ሁለቱንም ማድረግ አልቻለም፡፡ ‹‹ግን እኮ ይሄ በስራ አለም ቆይታዬ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈፀምኩት የሞያ ስነምግባር ጥሰት ነው››ሲል እራሱን ለማፅናናት ሞከረ…..፡፡ንግግሩ ግን እራሱንም ሊያሳምነው አልቻለም፡፡ ‹‹ስህተት የመጀመሪያም ሆነ የመጨረሻ ያው ስህተት ነው››የገዛ አእምሮ መልሶ የነገረው ነበር፡፡ ‹‹አሁን ወደኃላ መመለስ አልችልም…ይሄንን ጉዳይ ከዳር ላድርስና ..ከእሷ ጋር ያለኝ የፍቅር ግንኙነት የሚደርስበትን ከፍታ አይቼ ውጤታማ የሚሆን ከሆነ ምን አልባት ሞያውን በክብር ብለቅና ወደሌላ ዘርፍ ብሸጋገር እንኳን ያዋጣኛል››ሲል ለጊዜው የታየውን መፍትሄ አስቀመጠ…የገዛ አእምሮው ግን ወዲያው ነበር አፍራሽ የሆነ ሀሳብ የሰጠው‹‹ሰውዬ ምን ነካህ..?ይሄንን ሞያ ለቀህ…ነጋዴም ብትሆን …ወይም ደራሲ… ሁሉም ሞያ አይነቱ እና ተጋላጭነቱ በመጠኑ ይለያይ እንደሆን እንጂ የራሱ ህጋዊም ሆኑ ሞራላዊ የስነምግባር ገደቦች አሉበት…በተለይ ፍቅርን በተመለከተ ሁሉም ሞያ ይፈተናል…አስተማሪ ብትሆን ተማሪህ ላይ አይንህን መጣል የለብህም…ማናጀር ሆነህ ፀሀፊህን መጎነታተል ስህተት ነው፡፡ሞያህን ሳይሆን አመለካከትህን ነው መቀየር ያለብህ… ራስህን አታሞኝ፡፡››አለው…. ለጊዜው በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ በላይ ማሰብ አልፈለገም….ጉዳዩን ለጊዜ አሳልፎ ሰጠና ብድርብሱን ተከናንቦ እራሱን ለእንቅልፉን አሳልፎ ሰጠ ....ወዲያው ነበር ያሸለበው…የሚገርመው ደግሞ አይኖቹ በተከደኑ ከሁለት ደቂቃ በኃላ ነበር በፀሎት ነጭ ቬሎ ለብሳ ጭንቅላቷ ላይ የሚያብረቀርቅ የወርቅ አክሊል አጥልቃ ግራና ቀኝ ጎኗ ላይ የበቀሉ ውብ ክንፏቾን እያማታች ከሰማዩ ላይ ሰንጥቃ መጥታ እቅፉ ውስጥ ስትገባ በህልሙ ያየው፡፡
///
በፀሎትና ለሊሴ ከወንጪ ከተመለሱ ሁለት ቀን ሆኗቸዋል፡፡መሽተዋል…አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ነው…በፀሎት እና ፊራኦል ግቢው ውስጥ ካለ ግዙፍ የመንጎ ዛፍ ስር ጎን ለጎን ቁጭ ብለው እያወሩ ነው፡፡
‹‹እንዴት ነበር ወንጪ?››
‹‹ውይ ሲዊዘርላድ በለው፡፡››
‹‹እኔ ወንጪን እንጂ ሲዊዘርላንድን አላውቃትም፡፡››
‹‹አኔ ደግሞ አውቃታለዋ ለዛ ነው ያነፃፀርኩልህ..ደግሞ ዘመዶቻችን እንዴት ደግና ቀሽት መሰሉህ?፡፡››
‹‹የእኔም ዘመዶች እኮ ናቸው አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ቢሆንም ..አንተ ምንአልባት ከልጅነትህ ጀምሮ ስለምታውቃቸው …ብዙም ጣእም ላይሰጥህ ይችላል..ማለት ሁለም ሰው እንደእነሱ አይነት ዘመድ ያለው ስለሚመስልህ ተራ ነገር አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ….እንደእኔ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደዛ አይነት ዘመድ ሲኖርህ ግን በቃ ..ከአሁኑ እንዴት እንደናፈቁኝ ብታውቅ››
‹‹ገና በሁለት ቀን››
‹‹አዎ በሁለት ቀን››
‹‹አሁን ከእኛ ስትለይና ወደቤትሽ ስትሄጂ እንናፍቅሻለን ..?ማለት እኔ ናፍቅሻለሁ?››ለቀናት በውስጡ ሲያብሰለስለው የነበረውን ጥያቄ ጠየቃት፡፡
‹‹ምን ማለት ነው….?ወደየትኛው ቤቴ ነው የምሄደው?››
‹‹ወደቦሌው ቤትሽ››

‹‹ምን….ለሊሴ ነገረችህ››
‹‹እሷ ታውቃለች እንዴ?››
‹‹እሷ ካልነገረችሽ ታዲያ ማን ነገረህ?››
‹‹እራሴ ነኝ የደሰረስኩበት ..ወደ ወንጪ ከመሄዳችሁ በፊት ነው ያወቅኩት››
‹‹እኮ እንዴት ልታውቅ ቻልክ?››
‹‹ያው እንዳልኩሽ የእህቴን ልብ ከተቀበልሽ በኃላ በሩቅ ሆኜ ለረጅም ጊዜ ስከታተልሽ ነበር..ስለዚህ በደንብ አውቅሻለው…እዚህ ቤት ከመጣሽ ከሳምንት በኃላ ጀምሮ ከፍተኛ ጥርጣሬ አድሮብኝ ነበር..ከዛ ምን አደረኩ አንድ ቀን ስትተኚ ሻርፕሽን ሙሉ በሙሉ ከፊትሽ ላይ ገፍፌ ተመለከትኩሽ…እና ኦርጅናለዋ በፀሎት መሆንሽን አረጋገጥኩ፡፡
‹‹ትገርማለህ..ከዛ ፀጥ አልክ?››
‹‹ምን ላድርግ…ምንም ማለትና ምን ማድረግ እንዳለብኝ አላወቅኩም ነበር፡፡››
‹‹አሁንስ አወቅክ?››
‹‹አይ….አንቺ ንገርኝ እስኪ …ምን ልታደርጊ ነው…?እስከመቼ ነው ከወላጆችሽ ምትደበቂው?››
‹‹ወላጆቼን በቀደም አግኝቼቸዋለው..እዚህ መሆኔን ያውቃሉ››ብላ ያልጠበቀውን ዜና ነገረችው፡፡
‹‹ጥሩ..እሺ እነአባዬን እንዴት ልታደርጊ ነው….?እንደዋሸሻቸው ሲያውቅ በጣም ነው የሚያዝኑብሽ…በአንቺ ብቻ ሳይሆን እኛም አውቀን ከነሱ ደብቀን ዝም በማለታችን ምን እንደሚወጥን አላውቅም? በጣም ጨንቆኛል›ብሎ እውነተኛ ስሜቱን ነገራት፡፡
‹‹ይቅርታ ፊራኦል..እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ስላስገባዋችሁ በጣም አዝናልው…ግን በዚህ ሁለት ሶስት ቀን ውስጥ እፈተዋለው…ማለት እናንተ ቀድማችሁ እንደምታውቁ ሳላሳውቅ እፈተዋለው››
‹‹እስኪ እናያለን…››

‹‹እኔ የእህትህን ልብ የተሸክምኩ በፀሎት መሆኔን እርግጠኛ ስትሆን ምን ተሰማህ?››
‹‹ግማሽ ሀዘን ግማሽ ደስታ››
‹‹አልገባኝም››
‹‹ለረጂም ጊዜ ላናግርሽና ቀርቤ ላወራሽ የምመኝሽ የእህቴን ከፊል አካል የተሸከምሽው በፀሎት የገዛ ቤቴ መጥተሸ ከእኔ ጋር አንድ መአድ እየቆረሽ መሆንሽን ሳውቅ ፍጽም ድስታ ነው የተሰማኝ…በሌላ ጎኑ ደግሞ ያችኛዋን በፀሎት አፍቅሬት ስለነበር….ሌላ በፀሎት እንዳልሆንሽ ሳውቅ ቅር ብሎኛል››


ተናጋ…አቶ ኃይለ ልኡል ከተቀመጡበት ተነስተው ልጃቸውን በማቀፍ ልክ እንደባሌት ዳንስ በአየር ላይ ነው ያሽከረከሯት…..ለሊሴ እና ሰሎሞን ትዕይንቱን በተመስጦ እየተከታተሉ ነው፡፡

ይሄንን ትዕይንት ለሚከታተል ሰው ልጃቸው ለአለፈው አንድ ወር ብቻ ተለይታቸው የቆየች ሳይሆን በአራስነቷ ተሰርቃባቸው ከሀያ አመት በኃላ በተአምር የተገኘች አይነት ነው የሚመስለው፡፡
በነጋታው አምስቱም በቻርተር አውሮፕላን ተጭነው ወደአዲስ አበባ ተመሱ፡፡በፀሎት ግን ቀጥታ ወደቤቷ ሳይሆን ወደ ለሊሴ ቤት ነው መሄድ የፈለገችው..ውሳኔዋን ስትነግራቸው ሁለቱም ወላጆቾ ክፉኛ ተቃውመው ነበር፡፡
‹‹አባዬ እማዬ.ስሙኝ…እኔን ወደቤት ለመመለስ ባደረጋችሁት ነገር በጣም ኮርቼባችኃላው በጣም እንደምትወዱኝም አውቄለው…ግን አሁን መጀመሪያ ያበላሸሁትን ነገር ማስተካከል አለብኝ…ከአሁን ወዲህ እንድታውቁት ምፍልገው እናንተ ብቻ ሳትሆኑ እነሱም ወላጆቼ ናቸው….ከአሁን ወዲያ ብቸኛ ሳልሆን ወንድምና እህት አለኝ…ቦሌ ያለው የተንጣለለ ቪላ ብቻ ሳይሆን አቃቂ ያለውም ደሳሳ ቤት ቤቴ ነው፡፡እና የግድ አሁን ከለሊሴ ጋር ወደቤት መሄድ አለብኝ…ከዛ እስከአሁን የዋሸዋቸውን ናግሬ ይቅርታ ካገኘሁ በኃላ እመጣለሁ››
‹‹እንዴት አድርገሽ ነው የምትነግሪያቸው…?.››
‹‹አላውቅም… ብቻ የሆነ መንገድ ፈልጋለው››
‹‹ካልሽ እሺ ልጄ….ግን ታውቂያላሽ ከአምስት ቀን በኃላ ቤት ድግስ አለ…ንቅለ ተከላ የተደረገልሽ ቀን ነው..ያው እንደተለመደው ዘንድሮም እየተደገሰ ነው፡፡
‹‹አዎ አውቃለው…..የሚገርመው እነዛኞቹም ቤተሰቦቼ ጋር ድግስ አለ….በዛው በተመሳሳይ ቀን የሙት አመት መታሰቢያ ድግስ አለባቸው…የማ ለእኔ ልቧዋን የሰጠችኝ የበሬዱ የሙት መታሰቢያ….››ስትናገር የሚረግፈውን እንባዋን መገደብ አልቻለችም….እናትና አባቷም በሰሙት ነገር ሽምቅቅ ነው ያሉት….፡፡
‹‹እና በእለቱ የትኛውን ድግስ እንዳምሳተፍ ግራ ገብቶኛል..ግን አታስቡ ጥዋት እዚህ ቆይና ከሰዓት እናንተ ጋር መጥቼ የእኔን የምስጋና በአል አከብራለው….አዎ እንደዛ አደርጋለው››
በቃ የእኔ ቆንጆ …እንደሚሆን እንደርጋለን..አንቺ ምንም አትጨነቂ…አሁን ሹፌሩ እናንተን ቤታቸው ያድርሳችሁ እኛ ከሰለሞን ጋር በራይድ እንሄዳለን፡፡››አሉ አቶ ኃይልኡል

‹‹አረ አባዬ ግድ የለም እኛ በራይድ ብንሄድ ይሻላል፡፡››ለሊሴና በሬዱ ፈጠን ብለው አካባቢው ወደአለ ራይዱ ሄዱና .ውስጥ ገብተው ወደአቃቂ ሲያመሩ ሰለሞን እና ባልና ሚስቶቹን ሊቀበላቸው በመጣ መኪና ቦሌ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ሄዱ፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያሰባት

ጨጓራው ሲለበልበው ይታወቀዋል…በቃ ውስጡ እየነደደ ነው…አሁን ምንም የማያውቀውን አዲስ ነገር አልነገረችውም…ምን እንዳበሳጨው ለራሱም አልገባውም….ሌላ ቢራ ከፈተና አንደቀደቀው…ስልኩን ደግመኛ አነሳና ደወለ…
‹‹ሄሎ ሶል ምነው?››
‹‹እባክሽ ስለሆነ ነገር ላማክርሽ ነበር… እኔ ክፍል ድረስ መምጣት ትችያለሽ?››
‹‹መቼ አሁን?››በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ አሁን››
‹‹እሺ በቃ መጣሁ››
‹‹ስልኩን ዘጋና ከተቀመጠበት ተነሳ…መልሶ ቁጭ አለ‹‹ሰለሞን ምን እያደረክ ነው…?በዚህ ሰአት ስለምን ጉዳይነው የምታወራት.?›እራሱን በብስጭት ጠየቀ፡‹‹፡መልሼ ደውዬ በቃ ተይው ነገ ይደርሳል ማለት አለብኝ..››ወሰነና ስልኩን አነሳ….ቁጥሩን ከመጫኑ በፊት የመኝታ ቤቱ በራፍ ተቆረቆረ…..
ስልኩን ወደ አልጋው ወረወረና ተንደርድሮ ሄዶ ከፈተላት…በፀሎት ሮዝ ቀለም ያለው ስስና ልስልስ ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች… ፀጉሯን ወደላይ ጠቅልላ በሻሽ አንድ ላይ ጠፍራ አስራዋለች…ውብና መራኪ ሆና ነው እየመጣችው …ወደውስጥ ዘልቃ ገባች‹‹….ምነው በሰላም ነው…?አስደነገጥከኝ እኮ››
ፊት ለፊቷ ተገትሮ ቆመ….ግራ ገባት
‹‹ሶል ምን ሆነሀል…?.ምንድነው የምትነግረኝ?››ጉጉትና ፍራቻ በተቀየጠበት ስሜት ጠየቀችው፡፡

ተንደረደረና በሁለት እጆቹ አገጯን ግራና ቀኝ ክንዶን ይዞ ወደእሱ አስጠጋት… ከንፈሯ ላይ ተጣበቀ….በቀላሉ አለቀቃትም…ምን ይህል ደቂቃ እንደተሳሳሙ ሁለቱም አያቁም …ምን አልባት አንድ ደቂቃ ሊሆን ይችላል …ምን አልባትም ዘላለምም ሊሆን ይችላል….ግን የሁለቱም ልብ በየውስጣቸው ሲንፈራፈር ታውቋቸዋል…ሁለቱም በአየር ላይ የሚንሳፈፉበት ክንፍ እንዳበቀሉ አይነት ስሜት ተሰምቷቸዋል….ለሁለቱም ያልተጠበቀና ልዩ ክስተት ነበር….ሁለቱም ደግሞ ከገዛ ራሳቸው ጋር እንኳን ተነጋግረው ሳይወስኑ በነገሩ መሆን ተስማምተው በደስታ ፈንጥዘዋል፡፡በፀሎት አራት ተኩል ላይ ሰለሞን ክፍል የሄደች ስድስት ሰዓት ሲሆን ነበር ወደክፍሏ የተመለሰችው፡፡እሱንም ለሊሴ ምን ትለኛለች የሚል ይሉኝታ ቀፍድዷት እንጂ እዛው እቅፉ ውስጥ ሟሙታ እየቀለጠች ቢነጋ ደስ ይላት ነበር፡፡እሱም እንደዛው፡፡
በማግስቱ እስከአራት ሰዓት ከአልጋቸው መውረድ አልቻሉም ነበር፡፡
‹‹ልጁ ምን ይለናል ብዬ ነው እንጂ ቀኑን ሙሉ ከዚህ አልጋ ባልወርድ ደስ ይለኝ ነበር››ወ.ሮ ስንዱ ተናገሩ
‹‹ከአልጋው መውረድ ነው ወይስ ከእኔ እቅፍ መውጣት ነው ያስጠላሽ?››
‹‹አንተ ደግሞ…ለምን ታሳፍራኛለህ?››
‹‹ይሄውልሽ ነገ ወደአዲስአበባ እንመለስ የለ ..የልጃችንን የንቅለተከላ የተደረገላትን አመታዊ የመታሰቢያ በአል ድል አድርገን ከደገስን እና አንዳንድ ነገሮችን ካስተካከልን በኃላ..ለአንድ ወር ሲዊዘርላንድ እንሄዳለን፡፡›
‹ማ እና ማ?››
‹‹እኔ እና አንቺ..፡፡ያው አሁን ዳግመኛ እንደተጋባን እና ጉዞውንም ልክ እንደጫጉላ ሽርሽር ቁጠሪው››
‹‹በጣም አጓጓኸኝ ..ግን እኮ ይሄ ያለንበትም ስፍራ ከሲዊዘርላንድ አይተናነስም››
‹‹ገባኝ… ግን ራቅ ብዬ ካንቺ ጋር መጥፋት ነው የምፈልገው…››

‹‹ውይ የፍቅር ግርሻ እኮ መጥፎ ነገር ነው…ግን እንደምታየው ከልጄ ጋር ላለፈው አንድ ወር አልተገናኘሁም…እኔ ለሌላ አንድ ወር ከእሷ ውጭ ማሳለፍ አልችልም››
‹‹አንቺ ደግ…በቃ ይዘናት እንሄዳለን…ሶስታችን እንደቤተሰብ ከእንደገና አብርን በፍቅር እንቆማለት….››
‹‹እሱ ያስማማኛል፡፡››አሉና ከአልጋቸው ላይ ወረዱ…ተጣጥበውና ተዘጋጅተው ከክፍላቸው ሲወጡ አምስት  ሠዓት ሆኖ ነበር፡፡የሰለሞንን ክፍል ሲያንኳኩ አልነበረም…ደወሉለት
..በደቂቃዎች መጣላቸው፡፡
‹‹እንዴት ነበር አዳር?››
‹‹ዕድሜ ላንተ ሁሉ ነገር ውብና ማራኪ ነበር››አቶ ኃይለልኡል መለሱ፡፡
‹‹ጥሩ …አሁን እርግጠኛ ነኝ እርቦችኃላ?››
‹‹አዎ …የራበን ይመስለኛል›››
‹‹በሉ ተከተሉኝ …ቆንጆ ቁርስና ምሳ አንድ ላይ እንዲዘጋጅላችሁ አድርጌለው…››ብሎ ይዛቸው ሄደ..፡፡
በቀይ መንጣፍ ያሸበረቀ ግዙፍ የሞጃ ሳሎን የመሰለ ክፍል ውስጥ ነው ይዞቸው የገባው….ልክ አዲስ ሙሽሮች እንደሚስተናገዱበት አዳራሽ ውብና ልዩ ተደርጎ ዲኮር ተደርጓል….ግዙፉ ጠረጴዛና ጠረጴዛውን የከበቡት ወንበሮች ከቆዳ የተለበጡ ውብና ልዩ ናቸው…ልዩ ልዩ ባህላዊ ቅርሶች ግድግዳው ሞልተውታል፡፡እየመራ ወሰደና ወንበሩን እየሳበ ሁለቱንም አስቀመጣቸውና ..ከፊት ለፊታቸው ዞሮ ቆመ….
‹‹አቶ ኃይለልኡልና ወ.ሮ ስንዱ…ዛሬ የመጨረሻ ቀናችን ነው፡፡ማለቴ ከአሁን በኃላ ያለውን ቤታችሁ ተመልሳችሁ መደበኛ ስራችሁን እየሰራችሁ የምናከናውነው ይሆናል፡፡እስከአሁን ላለው ግን በእውነት እናንተ ለእኔ ትልቅ ውለታ ስለዋላችሁልኝ ላመሰግናችሁ እወዳለው..ይሄንን ስራ ከልጃችሁ ከበፀሎት ስቀበል በከፍተኛ ፍራቻና በወረደ የራስ መተማመን ነበር…እናንተ ግን ለልጃችሁ ስትሉ ጠንክራችሁ አጠነከራችሁኝ….በሶስት ወርና በአራት ወር እፈተዋላው ያላልኩትን በመሀከላችሁ ያለውን ውስብስብ ችግር በአንድ ወር አዚህ ደረጃ እንዲደርስ አድርጋችሁ አስደመማችሁኝ..ይህ አንድ ወር ለእኔ ታላቅ ትምህርት

ያገኘሁበት ነው..በሀገራችን የማህበራዊ ስሪትና ባህል የጋብቻ አማካሪ ብሎ ዘመናዊ አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ውጤታማ አይሆንም ተጠቃሚም አይኖርም ብዬ ተስፋ ቆርጬ ድርጅቴን ልዘጋ እያሰብኩ ባለሁበት ወቅት ነው የእናንተን ስራ ያገኘሁት…አሁን ግን ዘመናዊውን ሳይንስ በሀገራችን ተጫባች ሁኔታ አንፃር ቃኝተን በጥበብ ከተጠቀምነው የብዙ ውስብስብ ጋብቻዎችን ችግር ለመቅረፍ እንደሚቻልና ስራዬም ለማህበረሰቡ ጠቃሚ እንደሆነ እንድረዳ አድርጋችሁኛልና አመሰግናለው….በአጭር ቀናት ውስጥ ባሳያችሁት ውጤት ልጃችሁ ብቻ ሳትሆን እኔም ደስተኛ ነኝ፡፡
‹‹ልጄ ..አንተም እንደምትረዳው ወደእዚህ ጉዳይ ስንገባ ..አንተ ስለምትለው በእኔና ስንዱ መሀከል ስላለው ግንኙነት ማሻሻል ምንም አይነት ፍላጎትም ሆነ እምነት የለኝም ነበር…ልጄን ለማግኘት ስል ነበር ሳልወድ በግዴ የተስማማሁት…እያደረ ግን ሀሳቤን ሙሉ በሙሉ እንድቀይር አድርገሐኛል…ጋብቻዬ ጥሩ ባለመሆኑ ሕይወቴም ምን ያህል የተዛባ እና በጭንቀትና በሀዘን የተሞላ እንደሆነ እንዳስተውል አድርገሐኛል…እኔ ምን የህል አጥቼ ቤተሰቦቼንም ምን ያህል እንዳሳጣኋቸው እንዳስብና ወደቀልቤ እንድመለስ አድርገኀኛል..እኔ ነኝ አንተንም ሆነ ስንዱን ማመስገን አያለብኝ…በእውነት የእድሜ ልክ ባለውለታዬ ነህ…አንተ ከአሁን ወዲያ ልክ እንደልጄ ነህ….በማንኛውም ህይወት ጉዞህ እኔም ሆንኩ ቤተሰቦቼ ከጎንህ እንደሆን ልታውቅ ይገባል፡፡እርግጠኛ ነኝ ነገ ተነጋ ወዲያ አዲስአበባ እንደተመለስን ልጃችንም ወደቤቷ ትመለሰላች ብዬ ተስፋ አደርጋለው…እሷ ስትመለስ የተቀረውን ነገር እናወራለን፡፡››
ሰለሞን‹‹እሺ ጥሩ አሁን ስለራባችሁ …ከዚህ በላይ በወሬ አልያዛችው ››እጁን ሲያጨበጭብ ነጭ ዩኒፎርም የለበሰ አስተናጋጅ መጣ…..‹‹ምግብ ይቅረብ…መጀመሪያ የእጅ ውሀ አምጡ በላቸው››ሲል አዘዘው…ልጁ በቆመበት በራፍ ላይ ላሉት ልጆች ምልክት ሰጠው፡፡ውብ የሆነ ባህላዊ ነጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ወጣት ሴቶች ውብ የሆነ ወርቅ ቅብ ማስታጠቢያ በእጃቸው ይዘው መጡና….አንደኛዋ አቶ ኃይለልኡልን ሌለኛዋ ወ.ሮ ስንደን ለማስታጠብ ጎንበስ አሉ…ሁለቱም ታጥበው..ቀና ሲሉ በተመሳሳይ ቅፅበት ነው የአንደኛዋ ፊት ላይ አይናቸው ያረፈው….ከዛ በኃላ ያለው ነገር ለመግለፅ ሚያስቸግር ነበር..ምግብ አዳራሹ በወ.ሮ ስንዱ እልልታና ጩኸት




‹‹ጥሩ ..እኔም ቢጃማ ነገር ብለብስ ደስ ይለኛል…››አሉና ሁለቱም ወደ የሻንጣቸው ሄዱ…ከ10 ደቂቃ በኃላ ሁለቱም በለሊት ልብሳቸው ለበሱና እጃቸውን ታጥበው የምግብ ጠረጴዛው ፊት ለፊት ተቀመጡ…ከአመታት በኃለ አንደኛው በሌለኛው እጅ በፍቅርና በሳቅ ታጅበው ራታቸውን በሉና ሻምፓኛቸውን ከፈቱ..ሁሉ ነገር ውብ ነበር…ልክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተያዩ ነው የሆነው…የሁለቱም ልብ ምት እንደወጣት ልብ ነው ከቁጥጥር ውጭ የሆነው…ከአመታት በኃላ ነው የአንዳቸው ገላ ለሌለኛቸው ምላሽ በመስጠት እንደ እሳት ጎመራ መንቀልቀል የጀመረው….ከአስራ ምናምን አመት በኃላ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የአንደኛቸው ከንፈር ሌላኛቸው ላይ ያረፈው….የአንዳቸው እጅ የሌለኛቸውን ፓንት ወደታች አንሸራቶ ያወለቀው፡፡
///
በፀሎት እና ለሊሴ ዛሬ የመጨረሻ ቀን የወንጪ ቆይታቸው ነው፡፡በዚህም የተነሳ ቀኑን ሙሉ ላለፉት 15 ቀን ሲያስተናግዶቸው የነበሩትን ዘመዶቻቸውን በጠቅላላ እየዞሩ ተሰናብተው ጨለምለም ሲል ቀጥታ ሻንጣቸውን አንጠልጥለው የመጨረሻ አዳራቸውን በፓርክ ውስጥ ለማድረግ  እነአቶ ኃይለልኡል እንዳያዮቸው እየተጠነቀቁ ቀጥታ ሰለሞን ወደ ያዘላቸው ሎጅ ነው ያመሩት፡፡ክፍላቸው ከሰለሞን ክፍል ቀጥሎ የሚገኝ ሲሆን በለሁለት አልጋ ክፍልነው፡፡
ሰለሞን አቶ ኃይለልኡልና ባለቤታውን ራት ካበላና ወደ መኝታ ቤታቸው ካስገባቸው በኃላ ሌሊሴንና በፀሎትን እራት ለመጋበዝና ውቡን የመጨረሻውን ምሽት አብሮቸው ለማሳለፍ ይዞቸው ወጣ፡፡
ከሎጃቸው ፊትላፊት ባለው ጉብታ ላይ ቁጭ ብለው ሀይቁን ቁልቁል እያዩ እያወሩ ነው፡፡
‹‹በእውነት በሕይወቴ እንደዘንድሮ አስደማሚና አስደናቂ ነገር ገጥሞኝ አያውቅም›› በማለት የጫወታውን ርዕስ የመረጠው ሰለሞን ነበር፡፡
‹‹እንዴት ማለት?››አለችው ለሊሴ፡፡
‹‹እንዴ ..ይታይሽ አንድ ሴት ዝም ብላ በስልኬ በመደውል ስራ ልቀጥርህ እፈልጋለው
…አሁን  መቶ ሺብር  ልላክልህ  ፣  ስራውን  ስትጨርስ  5  ሚሊዬን  ብር  እንድታገኝ

አደርጋለው››ስትለኝ መጀመሪያ ቀልድ ነበር የመሰለኝ…ይገርምሻል የባንክ ቁጥሬን አንኳን ስልክላት ቆይ እስኪ ጉዷን አያለው ብዬ ነበር…እሷ ግን ብሩን ልካ አስደመመችኝ፡፡ወዲያው ከወላጆቾ ስር ጠፍታ በሀገር አቀፍ ደረጃ የምትፈለግ ልጅ ሆና አገኘኋት..በእውነት ያንን ሳውቅ በጣም ፈርቼ ነበር፣በዛ ተገርሜ ሳልጨርስ እንቺ ለማሪያም ድግስ በጠራሽኝ ጊዜ እናንተ ቤት ቁጭ ብላ አገኘኋት….ከዛ የሁሉ ነገር መነሻ አንቺ እንደሆንሽ ተረዳሁ…ምክንያቱም ስለእኔ ከአንቺ ባትሰማና ስልኬንም ካንቺ ዘንድ ባታገኝ ይሄን ሁሉ ታሪክ አምልጦኝ ነበር…ከዚህ ሁሉ የሚገርመው ደግሞ አሁን የምሰማው ነገር ነው…የአንቺ እህት ለእሷ ልቧን መለገሷ……ይገርምችኋላ ለቀናት እንዴት ያንን ቤት መረጠች …?ብዬ ስብሰለሰል ነበር..ለካ ከዛ ቤተሰብ ጋር ያላታ ትስስር ጥልቅና በደም የተገመደ ነበር›››
‹‹ታድዬ ደግሜ ደጋግሜ ነው ያስደመምኩህ ማለት ነው››አለችው በፀሎት
‹‹በጣም..እንጂ››
‹‹ምን እሱን ብቻ እኔንም ነው ስታስደምሚኝ የከረምሽው…በተለይ በቀደም ማንነትሽን ስትነግሪኝ….አብጄ እየቃዠው ነበር የመሰለኝ››አለች ለሊሴ፡፡
ለተወሰነ ጊዜ ዝም ተባባሉና በለሊሴ ጥያቄ ሌላ ርዕስ ተከፈተ
‹‹ሶል አሁን ቤተሰቦቾን የምታገኘው ከዚህ እንደተመለስን ነው እንዴ?››ስትል ያሳሰባትን ጥያቄ የጠየቀችው፡፡
‹‹ምነው ጠየቅሽኝ?››
‹‹እኔ እንጃ የእኛ ቤተሰብ በፀሎትን እንዲህ በቀላሉ ለማጣት ዝግጁ የሚሆኑ አይመስለኝም…በተለይ ስለማንናቷ እነ አባዬ ሲያውቁ በጣም ነው የሚከብዳቸው..››
‹‹በፀሎት ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደለሊሴ ተጠጋችና አቅፋ እየወዘወዘቻት‹‹‹እህቴ ስለምን ማጣት ነው የምታወሪው…?ከአሁን ወዲህ እኔ ሁለት ቤተሰብ ነው ያለኝ…አንድ ቀን እዚህ ቤት ካደርኩ በሚቀጥለው ቀን እዛ አድርለሁ….ከተቻለ እና ሁሉም ከተሳማማ ደግሞ ሁላችንም ተሰብስበን አንድ ቤት ውስጥ እንድንኖር ነው የምፈልገው…እርግጥ ይሄ በአንዴ አይሆንም አውቃለው…ግን ሁለቱም ቤተሰቦቼ ቀስ በቀስ በደንብ እንዲተዋወቁና እንዲግባቡ ካደረግኩ በኃላ አንድ ላይ ሰበስባቸዋለው…የቦሌው ቤታችን እኮ አርባ ምናምን

ክፍል ነው ያለው…ከዛ ውስጥ አስሩን አንኳን አንጠቀምበትም…..እና እህቴ ስለመለያየትና ስለማጣት ምንም አታስቢ››
ለሊሴም‹‹እህቴ  በጣም  ነው  የምወድሽ….ከእህቴ  ሀዘን  እንድፅናና  ስላደረግሺኝ አመሰግናለው፡፡››ብላ እሷም በተራዋ አቅፋ ጉንጮን ሳመቻት፡፡
‹‹በቃ በቃ…መላቀሱ ይብቃችሁ…ለማንኛውም በፀሎት ቤተሰቦችሽን የምታገኝው እንዴት እና መቼ እንደሆነ ነገ ጥዋት ቁርስ እየበላን እናወራለን፡፡››
‹‹ለምን አሁን አናወራም… ?››መለሰችለት
‹‹አይ አሁን መሽቷል…ተነሱ እናንተም ወደክፍላችሁ ግቡ››ብሎ ቀድሞ ተነሳ..ለሊሴና በፀሎትም ተከትለውት ተነሱ
ሰለሞን እነሱን ወደክፍላቸው አስገብቶ ወደገዛ ክፍሉ ገባና ቢጃማውን ቀይሮ ቀድሞ ያዘጋጀውን ቢራ ከፈፍቶ መጠጣት ጀመረ…ሁለት ጠርሙስ ካገባደደ በኃላ አስቴር ትዝ አለችው፡፡ ሞባይሉን አነሳና ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ ከምሽቱ አራት ሰዓት አልፏል…ደወለ….ከበርካታ ጥሪዎች በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ሄሎ ኪያ ተኝታሻል እንዴ ?ቀሰቀስኩሽ?››
አስቴር መለሰችለት‹‹አይ ወንድሜ ገና ለመተኛት እየተዘገጃጀው ነበር፡፡››
‹‹ደህና ነሽ?››
‹‹ደህና ነኝ…ምነው ቆየህ እኮ !አልጨረስክም አትመጣም እንዴ?››
‹‹ነገ ከሰዓት የምመጣ ይመስለኛል፡፡››
‹‹ጥሩ ነው…ልደውልልህ ነበር…››
‹‹ምነው በሰለም…፡፡››
‹‹አይ የፊታችን እሁድ የመስፍኔ ልደት ስለሆነ ሰርፕራይዝ ላደርገው አስቤላው…አንተም እንድትገኝ እፈልጋለሁ››
‹‹እንዴ እስከአሁን ወደመጣበት አልሄደም እንዴ?››

‹‹አይ ቀረ እኮ ….በፊትም ጥዬሽ የሄድኩት እየቆጨኝ ነው….ትዳሬን አክብሬ እዚሁ እየሰራሁ ከአንቺ ጋር ልጄን አሳድጋለው አለኝ››
‹‹እና መፋታቱን ሙሉ በሙሉ ተዋችሁት ማለት ነው?››
‹‹አንተ ደግሞ ስለምን መፋታት ነው የምታወራው….?በቃ ደህና እደር በሰላም ተመለስልኝ…መስፍኔ ከመኝታ ቤት እየጠራኝ ነው…››ብላ ስልኩን ዘጋችው፡፡
ጨጓራው ሲለበልበው ይታወቀዋል…በቃ ውስጡ እየነደደ ነው…አሁን ምንም የማያውቀውን አዲስ ነገር አልነገረችውም…ምን እንዳበሳጨው ለራሱም አልገባውም….ሌላ ቢራ ከፈተና አንደቀደቀው…ስልኩን ደግመኛ አነሳና ደወለ…

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍ መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያስድስት

//
የባልና ሚስቶቹ የምክር አገልግሎት እንደቀጠለ ነው…ዛሬ ወንጪ ከከተሙ አስራአራተኛው ቀን ላይ ሲሆኑ በዚህ የ14 ቀን ጉዞቸው ከፍተኛ ለውጥ ላይ ደርሰዋል…
አሁን በዚህ ሰአት ከሁለቱም ፊት ለፊት ተቀምጦ ተራ በተራ እያያቸው እያተናገረ ነው..
‹‹ሰው ምን ጊዜም ከስህተት ጋር ሚኖር ፍጡር ነው፡፡ከሰው ጋር ስንኖር ስህተት ፈላጊ ከሆን በማንኛውም ሰው ላይ ከመጠን ያለፈ ስህተቶችን በቀላሉ ማግኘት እንችላለን…..ያ ደግሞ ከሰው ጋር አያኖረንም…አንዳችን የሌላችንን ክፍተት ለመድፈን መፈጠራችንን እስካላሰብን

ድረስ ምንም ነገር ሰላም ሊሆን አይችልም፡፡ደግሞ አስቡት የጋብቻ ዋናው አስፈላጊነትም ይህ ነው ፡፡ወንድ ልጅ በራሱ ፍፅም ወንድ ብቻ አይደለም..75 ፐርሰንት የወንድነት ሆርሞን ሲኖረው 25 ፐርሰንት ግን የሴት ሆርሞን በውስጡ ይዞል..ሴቷም በተመሳሳይ 75 ፐርሰንት የሴት ሆርሞን ሲኖራት 25 ፐርሰንት የወንድ ሆርሞን ይዛለች…አያችሁ የተፈጥሮን ረቅቂነት ..ሁለቱ ሲጣመሩ ...አንድ ሙሉ ወንድና አንድ ሙሉ ሴት ይገኛል ማለት ነው፡፡ለመዋሀድ ደግሞ ፍቅር ዋናው አገኛኝ መሰላል ነው፡፡››
‹‹ግልፅ ነኝ አይደል?››
‹‹አዎ .. ቀጥል››ሲሉ የተናገሩት አቶ ኃይለ ልኡል ናቸው
ሰለሞን ንግሩን ቀጠለ‹‹በአንድ መንደር ውስጥ ትኖር የነበረች ሴት ሶስት ሽማግሌዎች ከቤቷ አካባቢ ከውጭ በፀጥታ ተቀምጠው ተመለከተች። ሴትዬዎም ከቤቷ ወጣችና ወደሽማግሌዎቹ ቀርባ" እናንተን ከዚህ በፊት አይቼያችሁ አላውቅም።ግን እዚህ በደጃፌ ለረጅም ጊዜ ተቀምጣችኋል። እርግጠኛ ነኝ እርቦችኋል። እባካችሁ ወደቤቴ ዘልቃችሁ ግብና ቤት ያፈራውን ቅመሱ››አለቻቸው።
ከመካከላቸው አንደኛው ሽማግሌ‹‹የቤቱ አባወራ በቤት አለ?››ሲሉ ጠየቋት። እሷም መለሰች‹‹አይ የለም››ስትል መለሰች።
ሽማግሌውም"ስለዚህ ወደቤት መግባት አንችልም።"ሲሉ መለሱላት።
ሴትዬዋም ወደውስጥ ተመልሳ ገባች ።መሸቶ ባሏ እንደመጣ ስለሰዎቹ ነገረችው። ባሏም
‹‹በይ አሁን ሂጂና ወደውስጥ እንዲገብ ጋብዢያቸው››አላት።
እሷም ወጣችና ወደውስጥ እንዲገብ በድጋሚ ጠየቀቻቸው‹‹ባለቤቴ ቤት ነው ያለው..ወደውስጥ እንድትገብም ጋብዛችኋል...እባካችሁ ወደ ውስጥ ዝለቁና የሆነ ነገር ቅመሱ››
‹‹እኛ በአንድ ላይ ወደውስጥ መግባት አንችልም››አሏት
‹‹ለምን ?››ግራ ገብቷት ጠየቀች።

ከሽማግሌዎቹ አንድ መመለስ ጀመረ "ይሄውልሽ ..."ወደአንደኛው ጓደኛው በጣቱ እየጠቆመ "..እሱ አቶ ሀብት ነው ወደቤትሽ ከገባ ቤትሽ በሀብት ለዘላለም እንደተሞላ ይዘልቃል።...ይሄኛው ደግሞ አቶ ስኬት ነው ከአንቺ ጋር ተከትሎ ወደውስጥ የሚገባው እሱ ከሆነ ቤትሽ በስኬት ይሞላል።እኔ ደግሞ አያ ፍቅር እባላለሁ። እኔ ከገባሁ ደግሞ በዘመንሽ ሁሉ በቤትሽ ፍቅር ሞልቶ ይፈሳል።ክፍቱ ግን አስቀድመን እንደነገርንሽ ሶስታችንም በአንድ ላይ ወደውስጥ መግባት አንችልም። ስለዚህ ወደቤትሽ ተመለሺና ከባልሽ ጋር በመማከር ከሶስታችን ማንኛችንን ወደውስጥ እንደምታስገብ ወስኑ "በማለት አብራሩላት።
እሷም እንደተባለችው ወደውስጥ ተመልሳ የሰማችውን ሁሉ ለባሏ አስረዳችው። ባሏ በሰማው ነገር ፈነጠዘ‹‹አቶ ሀብትን እንጋብዘው ፤ይግባና ቤታችን በሀብት ይሙላው፤ከእሱ የሚበልጥ ምን አለ?።››አላት።
ሚስትዬው ግን ውሳኔውን ተቃወመች"ለምን ስኬትን አንጋብዘውም፤ከሀብት ይልቅ ስኬት ነው የሚጠቅመን"አለች። እቤት ውስጥ የነበረች የልጃቸው ሚስት ወሬቸውን ስታዳምጥ ስለነበረ ወደእነሱ ቀረበችና‹‹ለምን ፍቅርን አንጋብዘውም..ከሁሉም በላይ በቤታችን ፍቅር ቢሞላ ይሻላል››የሚል ሀሳብ አቀረበች።
ጥቂት ካሠላሠሉ እና ከተከራከሩ በኃላ ባልና ሚስቶቹም በሀሳቧ ተስማሙ ፤ሚስትም ተመልሳ ወጣችና ወደእንግዶቹ ሄደች። ‹‹ከመካከላችው ፍቅርን ለመጋበዝ ወስነናል፤አያ ፍቅር እባክህ ተነስና ወደቤታችን ዘልቀህ ግባ...የተዘጋጀውን መአድም አብረኸን ተቋደስ..ሌሎቻችሁ ስላልመረጥናችሁ ይቅርታ "ስትል ተናገረች።
ፍቅር ተነሳና ወደቤት ለመግባት መንቀሳቀስ ሲጀምር ስኬትና ሀብትም ከተቀመጡበት ተነስተው ከኃላው ተከተሉት። ሴትዬዋ ግራ ገባት ‹‹አብረን መግባት አንችልም.. ከመሀላችን አንዳችንን ምረጪ አላላችሁኝም ነበር እንዴ?"ስትል ጠየቀች።
ከመሀከላቸው አንደኛው ማስረዳት ጀመረ‹‹ልጄ ስትመርጪ ስኬትን ወይም ሀብትን መርጠሽ ቢሆን ኖሮ አንዳችን ብቻ ነበር ወደቤትሽ የምንገባው።አሁን ግን የመረጥሽው ፍቅርን ነው። እኛ ደግሞ ፍቅር በገባበት ሁሉ ተከትለን መግባት ግዴታችን ነው።እኛም እራሳችን የፍቅር ምርኮኞች ነን።በዚህ ምክንያት ሶስታችንም የግድ ወደቤትሽ እንገባለን። ካዘጋጀሽውም መአድ እንቋደሳለን።ቤትሽንም ዘላለም በሚትረፈረፍ ሀብት ፤ስኬትና ፍቅር እንሞላዋለን።"አሏት። እሷም በደስታ እየፈነጠዘች ወደቤቷ ይዛቸው ገባች።

አያችሁ እናነት ሀብታም ናችሁ ስኬታማም ናችሁ…አሁን እየጣርን ያለነው ከመሀከሏችሁ ሾልኮ ተሰዶ ነበረውን ዋናውን ፍቅር ለመመለስ ነው..ፍቅር ከተመለሰ ሁሉ ነገር ሙሉ ይሆናል››
ዛሬ በዚህ በሰጠኋችሁ ምሳሌ በመሀከላችሁ፤በቤታችሁና በአካባቢያችሁ ፍቅር ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ እያሰላሰላችሁ እንድታድሩ እፈልጋለው…ነገ እዚህ የምናሳልፍበት የመጨረሻ ቀናችን ነው…ተነገ ወዲያ ወደአዲስ አበባ እንመለሳለን….አሁን ዋናውን ነገር አጠናቀናል…በቀጣይ ቤታችሁ ሆናችሁ ልጃችሁም ተመልሳ ስራችሁን እየሰራች የምናደርገው ይሆናል…››በማለት የእለቱን ፕሮግራም አገባደደ
ባልና ሚስቶቹ ክፍላቸው ተያይዘው ሲገቡ የጠበቃቸው የተለየ ነገር ነበር፡፡የመኝታ ክፍላቸውን ግራና ቀኝ ግድግዳ ታኮ የነበረው ሁለት አልጋ ሁለቱም ወደመሀል ተስቦና አንድ ላይ እንዲገጥም ተደርጎ አንድ አልጋ ሆኗል….ግዙፉ የተዋሀደው አልጋ በነጭ ውብ አልጋ ልብስ ተሸፍኗል.. አልጋ ልብሱ መሀል ላይ በልዩ ዲዛይን የተሰራ ባለቀይ ቀለም የልብ ቅርፅ ይታያል..ሙሉ ወለሉ በቀይ ፅጌረዳ አበባ ከመሞላቱም በተጫማሪ ባለቆርቆሮ ልዩ ሻማ በመሀከል መሀከል ጣልቃ በማስገባት የተለያ ቀለም ያው ብርሀን እየረጩ ነው፡፡አደኛውን ግድግዳ ተጠግቶ በሚታይ ጠረጴዛ ላይ ሻማፓኝ መጠጥ ከውብ ብርጭቆዎች ጋር ይታያል…በሚገፋ ተሸከርካሪ ጠረጴዛ ላይ አስጎምዢ ምግቦች ተደርድረዋል…
ሁለቱም ባልና ሚስት በመጀመሪያ የተሳሳተ ክፍል የገቡ ነበር የመሰላቸው….የገዛ ሻንጣቸውንና ሌሎች የግል እቃዎችን ሲያዩ ተረጋጉና ወደውስጥ ዘልቀው በራፉን ዘጉት፡፡
‹‹ስንድ ይሄ ጉደኛ ልጅ የ20 አመት ጎረምሳ አደረገን እኮ..››
ወ.ሮ ስንዱ እንባቸው እየረገፈ ተናገሩ‹‹ያበቃልኝ መስሎኝ ነበር….እድሜ ለልጄ ይሄው ዳግመኛ ልጃገረድ ሆንኩ››
‹‹እንዴ ስንድ ዛሬ ሳቅና ፈንጠዝያ ነው እንጂ የምን ለቅሶ?››አሉን እጃቸውን ወደባለቤታቸው ጉንጮች በመላክ እንባቸውን ጠረጉላቸውና አቅፈው ሳሞቸው….‹‹በይ ዛሬ ምሽቱ የእኛ መሰለኝ..እንቀመጥ››
‹‹መጀመሪያ ልብሴን ልቀይርና ቀለል ያለ ልብስ ልልበስ…እስከዛ እንተ ቁጭ በል››


የቀጠለ ምንሆኛለሁ Book.Review

አንዲት ደንበኛዬ(ስነ ልቦና ምክር ፈልጋ የመጣች) ሴት አለች፡፡

ከዩኒቨርሲቲ ሁሉንም ትምህርት "A›› አምጥታ ነው በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀችው፡፡ እንደተመረቀችም ሥራ ተቀጥራ ጥሩ ደመወዝ ታገኛለች፡፡

ነገር ግን በሕይወቷ ደስተኛ
አይደለችም፡፡ የምረቃዋ ዕለት እናት፣ አባት፣ ወንድም፣ እህት ሁሉም በደስታ ሲስክሩ እሷ ግን ደስተኛ አይደለችም፡፡ በተለይ ማህበራዊ ሕይወት ደስተኛ አይደለችም፡፡

የምታወራው ከእናቷ ጋር ብቻ ነው፡፡ ከሥራ  ውስጥ እናቷን በስራ ማገዝ ነው ደስታዋ፡፡ እናቷ ያለችው ነገር ተፈጻሚ ይሆናል፡፡ ‹‹ሥራሽን ልቀቂ›› ብትላትም ለመልቀቅ አታመነታም፡፡ በዚህ ባህሪዋ ሁሉም የቤተሰብ አባላትና ጓደኞቿ ይገረሙባታል፡፡

ይህቺ ደንበኛዬ ልጅ በነበረች ጊዜ እናቷ ሲበዛ አኩራፊ ነበረች፡፡ ደንበኛዬ እንደነገረቺኝ እናት ቤት ውስጥ የሆነ ጥፋት ካየች ያጠፋውን ሰው ወርና ሁለት ወር ልታኮርፈው ትችላለች፡፡

ልጅ ሆና እናቷ በምክንያት ስታኮርፋት እሷን ለማስደሰትና የእናቷን ኩርፊያ ለማስቀረት የማታደርገው ነገር የለም፡፡ ለዚህ ስትል ከአቅሟ በላይ ትሰራለች፡፡ የታዘዘችውን ታደርጋለች፡፡ ሳትታዘዝም ትሰራለች፡፡ እናቷ ከዚያ ኩርፊያ እንድትወጣ ማድረግ ያለባትን ብቻ ሳይሆን የሌለባትንም ታደርጋለች፡፡


እንግዲህ ደንበኛዬም አድጋ ያንኑ ነው የቀጠለችው፡፡ አሁንም አድጋ የልጅነት አስተሳሰቧ ውስጥ ናት ማለት ነው፡፡ በትምህርታ: በጣም ጎበዝ ናት፡፡ በሌላው አስተሳሰቧ ግን ገና ልጅነቷ ላይ ነው ያለችው፡፡ በታመመ ቤተሰብ ውስጥ በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር እንግዳ ጉዳይ ነው፡፡ ድርጊቶች በኃይል ነው የሚፈፀሙት፡፡

ችግር ሲፈጠር መነሻና ግዙ አይታወቅም፡፡ ለሁኔታዎች ማን ኃላፊነት እንደሚወስድ አይታወቅም። ከኃላፊነት አለመውሰድ ውጭም ከተፈጠረው ጭማር ትምህርት መውሰድ የሚባል ነገር የለም፡፡ ስለዚህ ደግሞ ደጋግሞ የማጥፋት እድል ነው ያላቸው፡፡  ካደጉ በኋላም ያንኑ ስህተትየማረምና የማስተካከል እድል የለም፡፡

ይህቺ ደንበኛዬ ዛሬም እንደ ልጅነቷ ግንኙነቷ ከእናቷ ጋር ብቻ ነው፡፡ አሁንም እናቷ ያለችውን ፈጥና ታደርጋለች። ሌላው ማህበራዊ ግንኙነቷ ጠቦ የእናቷ ታዛዥና አድራጊ የሆነችው አሁንም አስተሳሰቧ የልጅነቷ በመሆነ ነው፡፡ በዩኒቨርሲቲ የማዕረግ ተመራቂና በመ/ቤቱ ብርቱ ሠራተኛነቷ ቢመሰከርላትም ቤት ስትገባ ግን ያቺ የልጅነቷን ነች፡፡

በስነልቦና የተደመደመ አውነት የለም። የመሆን ዕድል ነው ያለው፡፡ ይህች ደንበኛዬ ወይም በእሷ አይነት አስተዳደግ ውስጥ የመጣ ወንድ የአንድ መ/ቤት ስራ አስኪያጅ ቢሆኑም የበታች ሠራተኞችና መምሪያ ኃላፊዎች ያዘዟቸውን ሳይሰሩ ቢቀሩ ቢሯቸው ጠርተው ችግሩን (በመነጋገርከመፍታት ይልቅ ማኩረፍ ነው የሚቀናቸው፡፡

በስሜታዊነት ነው ምላሽ የሚሰጡት፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ግን በልጅነታቸው የተፈጠረባቸው የአዕምሮ ቁስለት አሁን በጉርምስናቸውና በጉልምስናቸው ችግር እየፈጠረባቸው መሆኑን አያውቁም፡፡ ለምን ይህን እንደሚያደርጉም አያውቁም፡፡

ግን መቆጣጠር በማይችሉበት መንገድ ያደርጉታል። ብዙ ሰዎች የስነልቦና ባለሙያዎች ጋ ሲመጡ ነው መነሻ ምክንያቱን የሚያውቁት፡፡ ሰው ከወላጆቹ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ችግርንም፣ ባህሪንም ይወርሳል፡፡

የታመመ ቤተሰብ ውስጥ ቁጭ ብሎ፣ በስርዓት መነጋገር የለም፡፡ ቀደምቶቹ ወላጆች ሁሉንም እንደሚቆጣጠሩት ሁሉ እነዚህ ደግሞ ዝም በማለት ወይም በማኩረፍ ነው ምላሽ የሚሰጡት፡፡ ማኩረፋቸውን ያምነብታል፡፡ አንዳንዴም በኩራት ያወሩታል፡፡ “ዝግት ሳደርጋት ልክትገባለች›› ይላሉ፡፡ ቤቱን በዝምታ ነው የሚያስጨንቁት፡፡


ፀጉር ቆራጩ ደምበኛውን ያዝናናል ብሎ ያሰባቸውን ነገሮች በሙሉ ያደርጋል...

“ያ.. ይታይሃል..?...አስፖልቱ ዳር የተቀመጠው ልጅ..?”

“አዎ”

“ከምታስበው በላይ ጅል ነው..”

“እንዴት? ”

“ቆይ ላሳይህ”....ብሎ ወጣና ልጁን ጠርቶ ወደ ውስጥ አስገባው።

“ተመልከት እንግዲህ...”

ከኪሱ አንድ የአምስት ብር እና አንድ የአስር ብር ኖት አወጥቶ ሁለቱንም መሬት ላይ ጣላቸው ከዛ ልጁን “ ከሁለቱ ትልቁን ብር አንስተህ ሂድ” አለው።

... ይሄኔ ያ ልጅ አምስቷን ብር ብድግ አርጎ ወደ መጣበት ይመለሳል...

“አየህ ይሄን ደደብ...?

በዚህ ዕድሜው አምስት ብርና አስር ብርን መለዬት አይችልም...!!”ሲል ተናገረ።

“በጣም ሚገርም ነው” አለ ፀጉሩን ሊቆረጥ የመጣው ሰውዬ ባዬው ነገር የእውነት ተገርሟል...

ፀጉሩን ተቆርጦ ጨርሶ ከፀጉር ቆራጩ ጋር ተሰነባብተው ተለያዩ።

ይሁን እንጂ ሰውዬ ቅድም ባየው ነገር ተገርሞ ብቻ ሊቀር አልፈለገም።

በቀጥታ ወደ ቅድሙ ልጅ ሄዶ ያሳሰበውን ነገር ጠየቀው...

“እውነት አንተ...አስር ብር እና አምስት ብርን መለየት አትችልም..?”የሰውየው ጥያቄ ነበር...

“አዪዪ..” አለ ልጁ ፊቱ ላይ የአሸናፊነት ፈገግታ እያሳየ...

“አዪዪ...10 ብሩን ያነሳሁ ቀንማ ጨዋታው ያበቃል” ብዬ ነው ሲል መለሰ


‹‹አሁን ክፍላቸው አረፍ ብለዋል….ለሚቀጥሉት ሁለት ሶስት ሰዓት እረፍት ነኝ….›› በፀሎት‹‹እና ታዲያ ወደፍል ውሀ ለምን አንሄድም?››የሚል ሀሳብ አቀረበች፡፡ ‹‹በጣም የተቀደሰ ሀስብ ነው››ቀድሞ የተነሳ ሰለሞን ነው..ሴቶቹም ተከተሉት፡፡እያተሳሳቁና እየተጫወቱ በእግሩ ጉዞ እስካይ ብሪጁ ጋር ደረሱ…..
ለሊሴና ሰለሞን ቀድመው የብረት ተንጠልጣ ድልድዩ ላይ ቢወጡም በፀሎት ግን ልትደፍር አልቻለችም..‹‹ምነው ፈረራሽ እንዴ?››
‹‹ለምን አልፈራም…እየው እስኪ ቁልቁል በሆነ ተአምር ቢበጠስስ?››
‹‹አንቺ ደግሞ በለሊት ሞተር የምታበሪ ጀግና እዚህ ድልድይ ላይ መውጣት ትፈሪያለሽ?››ለሊሴ በትዝብት ጠየቀቻት፡፡
ወደተሸፈነ ፊቷ እያመለከተች‹‹በለሊት ሞተር መንዳቴ ያመጣብኝን ጣጣ አትመለከቺም?››አለቻት፡፡
ወደኃላ ተመለሰና እጇን ይዞ እየጎተተ አስወጣት ….ተጠመጠመችበትና እጆቾን በወገቡ ዙሪያ አዙራ ተለጠፈችበት፡፡ልክ የመጀመሪያ ልጁን ዳዴ እንደሚያስተምር አባት ቀስ ብሎ እየጎተተ ይዞት ይጓዝ ጀመረ…እንደምንም ድልድዩን ተሻግራ እግሮቹ መሬት ሲረግጡ እፎይ አለችና በረጅሙ ተነፈሰች….ሁለቱም ተሳሳቁባት፡፡
‹‹ተፈጥሮ እኮ ምትገርም ነች ..ከጎንና ጎን ሁለት መለስተኛ ኩሬዎች አሉ…ሁለቱም በተለያየ አይነት ቀለም ባላቸው ውሀዎች ተሞልተዋል ..አንደኛው ፈዛዛ አረንጓዴ አይነት ቀለም አለው…ውሀው በጭቃ የተሞላ እና ሙቅ ነው…በህመም የሚሰቃዩና ፈውስ ሚፈልጉ ሰዎች ውስጡ ይገቡና ሰውነታቸውን በጭቃ በመለቅለቅ ይዘፈዘፋሉ…ከዛ ቀላ ያለ ድፍርስ መሳይ ኩሬ ውስጥ ገብተው ይዘፈዘፋሉ..ደግሞ ከተራራው ላይ እየተንፏፏ የሚፈልቅና ውብና ንፅህ ሙቅ ፏፏቴ አለ…በአካባቢው ባለው ወንዝ አጎንብሰው ከወንዙ ሚጠጡ ፈረሶችና ከብቶች ዙሪያውን ያለው ጫካ ከዛፍ ዛፍ ሚዘሉ ዝንጀሮዎች ጦጣዎችና ጉሬዛዎች አካባቢውን በውብ ዜማ የሚያደምቁ የወፍ ዝርያዎች ሁሉም ድንቅ ነው፡፡
ጉብኝታቸውን አገባደው ሰለሞንም ወደሎጁ በፀሎትና ለሊሴም ወደአረፉበት የዘመድ ቤት ጉዞ ጀመሩ…ግን ማረፊያቸው ከመደረሳቸው በፊት ከተለያዩ 20 ደቂቃ በኃላ ነበር ሰለሞን

ለበፀሎት የደወለላት..ስልኩን አነሳችና ከለሊሴ ወደኃላ ቀረት ብላ አዋራችው…ጨርሳ እንደተመለሰች ወዲያው ነበር ለሊሴ በነገር የተቀበለቻት፡፡
‹‹እኔ ይሄ ሰውዬ ምኑም አላማረኝም?››
‹‹የትኛው ሰውዬ?››በፀሎት ያልገባ መስላ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ሀለቃዬ ነዋ››
‹‹ደግሞ ምን አደረገ?››
‹‹አንዴ …እዚህ ያለንበተ ድረስ መጣ …አብረን ረጅም ሰዓት አሳለፍን ..አሁን ከተለያየን ገና አንድ ሰዓት እንኳን አልሞላም …ግን ይሄው ደወለልሽ››
‹‹እና?››
‹‹እናማ …አፍቅሮሻል እያልኩሽ ነው…››
‹‹ጥሩ ነዋ››
ለሊሴ ያልጠበቀችውን መልስ ስላገኘች ይበልጥ ተገረመችባት‹‹ጥሩማ ጥሩ ነው…ግን አንቺስ ታፈቅሪዋለሽ ወይ…?››
‹‹አፈቅረዋለው እንዴ ?››እራሷን ጠየቀች..ቁርጥ ያለ መልስ ለማግኘት አልቻለችም››
ለሊሴ መልስ ስታጣ ንግግሯን ቀጠለች..‹‹ቅድም እንደነገርኩሽ ሁለታችሁም አብራችሁ ብትሆኑ እንደእኔ ደስተኛ የሚሆን ሰው የለም…ሀለቃዬ በጣም የማከብረው ሰው ነው፡፡ አንቺም የምወድሽ እህቴ ነሽ፡፡ የሁለታችሁ አንድ ላይ መሆን ልዩ ነው..ግን አንቺ ፍላጎት ማይኖርሽ ከሆነ ከአሁኑ ነው ግንኙነታችሁን ማቆም ያለብሽ…ምከንያም ከዚህ በላይ ስር እየሰደደ ሄዶ እሱ ሙሉ በሙሉ ፍቅር ውስጥ ከተዘፈቀ በኃላ አይሆንም ዞር በል ብትይው…በእኔ ስራ ላይም ከፍተኛ ተፅእኖ ይፈጥርብኛል..ታውቂያለሽ ስራውን በስንት መከራ ነው ያገኘሁት..በእናንተ ጉዳይ እንዲበላሽብኝ አልፈልግም፡፡››
በፀሎት በፀጥታ አሰበች..ሆነም ቀረ በቅርብ ቀን ሁሉ ነገር ፍርጥርጥ ማለቱ አይቀርም
..ታዲያ ለምን ልጅቷን አጨናንቃታለሁ? ስትለ አሰበችና ወሰነች..ወደማረፊያችው ሊደርሱ

የ10ደ ደቂቃ መንገድ ነበር ሚቀራቸው…‹‹ነይ እስኪ እህቴ ወደቤት ከመግባታችን በፊት እዚህ ዛፍ ስር ትንሽ እንቀመጥ…››
‹‹ምነው ቤት ብንገባ አይሻልም ..?ደርሰናል እኮ››
‹‹ገብቶኛል…የምነግርሽ ነገር ስላለነው፡፡››
‹‹እሺ›› አለችና ከመንገድ ዳር ወዳለች ዛፍ ሄዱና ጎን ለጎን ሳር ላይ ተቀመጡ….
‹‹ለሊሴ እኔ ሰለሞንን የማውቀው በቀደም ለማሪያም ቀን ሲመጣ አይደለም.››
‹‹ምን ማለት ነው?››
‹‹ማለቴ እርግጥ በአካል ፊት ለፊት የተገናኘነው የዛን ቀን ነው…..ግን ከዛን በፊትም  እንደዋወል ነበር››
‹‹የምታወሪው ምንም እየገባኝ አይደለም፡፡››
‹‹ትዝ ይልሽ ከሆነ ስራ የጀመርሽ ሰሞን ስለ እሱ ጥሩነት ደጋግመሽ ታወሪኝ ነበር..ለሆነ ስራ ስለምፈልገው ስልኩን ከአንቺ ሞባይል ወሰድኩና ደወልኩለት …ተነጋግረን ትስማማንና ቀጠርኩት፡፡››
‹‹ቀጠርኩት››
‹‹አዎ ቢሾፍቱ ለ15 ቀን የቆየበት ስራና አሁንም እዚህ የመጣበት ስራ የእኔ ስራ ነው….እርግጥ እዚህ እንደሚመጣ እኔም ከአንቺ እኩል ነው ያወቅኩት ቢሆንም የእኔን ወላጆች ይዞ ነው የመጣው››
ለሊሴ ከመገረምና ከመደንጧ የተነሳ ከተቀመጠችበት ተነሳች፣ጭንቅላቷን ያዘች፡፡‹‹እህቴ ቁጭ በይ ዋናውን ነገር አልነገርኩሽም››
‹‹ከዚህም በላይም ዋና ነገር አለ?››
‹‹አዎ ቁጭ በይ›› ቁጭ አለች…

‹‹እኔ ማለት….››
‹‹አንቺ ማለት?››
እጇን ያዘችና ጎትታ ደረቷ ላይ አስቀመጠች….‹‹ይሰማሻል?››
‹‹ምኑ?››
‹‹የልብ ምቴ››
‹‹አዎ ይሰማኛል….አመመሽ እንዴ? በፍጥነት ነው የሚመታው››
‹‹አይ ደህና ነኝ…እንዴት እደምነግርሽ ስለጨነቀኝ ነው ..ምን መሰለሽ…ይሄ አሁን ውስጤ የሚመታው ልብ የእህትሽ ልብ ነው፡፡››
‹‹አዎ፣ እሱማ አውቃለው የእህቴ ልብ ነው››
‹‹ማለቴ የበሬዱ ልብ ነው….እኔ ይሄንን ልብ ከእህትሽ ነው የተለገሰኝ››
‹‹ወይኔ  በፈጣሪ..ምን  እያልሽኝ  ነው….?አንቺ  ማለት….ወይኔ  በፈጣሪ…ለምን  ዋሸሺን
…..አሁን አባዬ ሲሰማ ምን ይላል….?››
በፀሎት ለሊሴን ለማረጋጋትና ሙሉን ታሪኳንና እቅዷን ለማስረዳት ከአንድ ሰዓት በላይ ነው የፈጀባት…ሁሉ ነገር ተስተካክሎና በመሀከላቸው የነበረው የተካረረ ስሜት ረግቦና ሰላም ወርዶ ወደቤት ተቃቅፈው ሲመለሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት አልፎ ነበር…
ወደመጨረሻው እየተንደረደርን ነው

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያአምስት

ሰለሞንና የበፀሎት ቤተሰቦችን አብዛኛውን ጊዜያቸውን አካባቢውን ያለውን እያንዳንዱን መስህብ በመጎብኘት ነው የሚያሳልፉት….እያንዳንዱ ውይይትና ምክረ-ሀሳብም በመዝናናት ውስጥ ሆነው የሆነ ቦታ አረፍ ሲሉ ወይም ብና ለመጠጣት የሆነ ካፌ ሲቀመጡ በውይይትና በጫወታ መልክ የሚሰጥ ስለሆነ እንደ ቢሾፍቱ አስጫቂና ጭንቅላት የሚይዝ አይነት አልነበረም፡፡
በወንጪ ኢኮ ቱሪዝማ ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት እና ለጉብኝት ዝግጁ ከሆኑት ዋና ዋና አይን ሳቢና ቀልብ አስደንጋጭ የቱሪስት መስህቦች ውስጥ ጥቂቶቹ
ጎሮ በሚባለው ስፍራ የተገነባው ጎሮ ካልቸራል ሴንተር የወንጪ ኢኮቱሪዘም ፓርክ አንዱ መገለጫና ውበት ነው፡፡ በህንፃው ላይ ባህላዊ ምግቦች የሚገኙበት ውብ የሆነ ሬስቶራንት..ባህላዊ የሆኑ የእጅ ስራ ውጤቶች የሚሸጥባቸው ሱቆች…የተለያዩ ዝግጅቶችን ለማዘጋጀት የሚያገለግል እስከ 3መቶ ሰዎች ማስተናገድ የሚችል ውብ የሆነ አምፊ ትያትር ከአካባቢው ከሚገኙ አገልግሎቶች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ እና አካባቢው ላይ ሆኖ ቁልቁል ወደታች ሀይቁንና ከማዶው ያለውን ተራራ ሲያዩት ልብን ስውር የሚያደርግ የተለየ አይነት አስደማሚ እይታ አለው፡፡
ከጎሮ 2.3 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ነዲ ካልቸራል ሴንተር ደግሞ ሌላው ልብ ሰዋሪ ቦታ ነው፡፡ነዲ ከስሙም መረዳት እንደሚቻለው በአካባቢው የሚመረት የወንጪ ማር እና የማር ውጤቶች እንደብርዝና ጠጅን ጨምሮ መሸጫ እንዲሆን ታስቦ የተገነባ ህንጻ ነው…የህንፃው ጠቅላላ ዲዛይን አገልግሎቱን ታሳቢ ተደርጎ የተሰራ ስለሆነ ውብ ነው፡፡በማር እንጀራ ቅርፅ የተሰራ ሁለት ሶስት ጓደኛሞች ተቀምጠው ቁልቁል ሚታየውን ውብ እይታ ዘና እያሉ ወሬያቸውን የሚጠረቁበት ውብ ስፍራ አለ፡፡

ሙለታ ወንጪ ሬስቶራንት ሌላው በስፍራው የሚገኝ ውብ ቦታ ነው …በዚህ ስፍራ ሬስቶራንቶችና ሱቆች የፈረስ ማስዋቢያና ባህላዊ እቃዎች የሚሸጡበት ሱቆች ሲኖሩ ኩኪስ ብስኩት የመሳሰሉትም ቀላል ምግቦችን ማግኘት ይቻላል ፡፡
ነዲ ሰስፔንድድ የመስታወት ቴራስ ሌላው በአካባቢው ያለ ውብ ህንፃ ነው፡፡ይህ የመስታወት ወለል ግማሽ ክብ አይነት ቅርፅ ሲኖረው በሶስት ድርብርብ ተደርጎ የተሰራና እላዩ ላይ ወጥታው በመስታወቱ አሻግረው ወደታች ሲመለከቱ ከስር የሚታየው አስፈሪ ገደል መሳይ ግን በአረንጓዴ ሳርና ተክሎች የተሸፈና ውብ ስፍራ በማዶ የሚገኘው የጠራ ሀይቅ …በቃ አስፈሪ ግን ደግሞ አስደሳች እይታ ነው፡፡ይህ የመስታወት ቴራስ በአንድ ካሬ ሜትር ላይ 400 ኪ.ግራማ የመሸከም አቅም እንዳለው ቢታወቅም በርከት ያለ ሰው ከወጣበት ግን ከአሁን አሁን መስታወቱ ተፈርክሶ ሾልከን ወደገደሉ ብንንከባለልስ? የሚል የፍራቻ ስሜት ሰቅዞ የሚያሲዝ አይነት ነው፡፡ከዚህ አስደማሚ የመስታወት ቴራስ ጎን አምፊትያትር ያለ ሲሆን በተያያዥነትም…ልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚሰጥ ካፍቴሪያ አለ፡፡ከዚህ ስፍራ ቀጥታ ወደሎጅ የሚወስድ የመኪና መንገድ ከላይ የመስታወት ቴራሱ ላይ ሆነው ከስር ማየት ይቻላል፡፡
ከዛ ደግሞ የተፈጥሮ ፍል ውሀ ያለበት በደን የተሸፈነ ሲሆን በአካባቢው ጉሬዛ ፤ጦጣ አእዋፍት ፤አምቦ ውሀ የተፈጥሮ ፏፏቴ ይገኛል …ጎን ለጎን ያሉ ሙቅና ቀዝቃዛ ኩሬ የኬብል ድልድይ ፤ወንዝ ..ብዙ ብዙ አስደማሚ ተፈጥሯዊ ነገር ይገኛል፡፡የነዲ መዝነኛ ስፍራን እና የተፈጥሮ ፍል ውሀን የሚያገናኝ በብረት የተሰራ እስካይ ብሪጅ አለ፡፡ብሪጁ 72 ሜትር ርዝመትና ኖሮት ሀምሳ ሜትር ከፍታ እንዲኖረው ተደርጎ የተሰራ አስፈሪ ግን ደግሞ የራሱ የሆነ ውበትና የተለየ ስሜት የሚያጭር ልዩ ድልድይ ነው፡፡
እነዚህን ሁሉ ባለፈው አንድ ሰምንት ውስጥ የጎበኞቸው ቦታዎች ናቸው፡፡ በስምንተኛው ቀን ከቀኑ 9ሰዓት አካባቢ ለበፀሎት ደወለላት
‹‹ሄሎ..እንዴት ነሽ?››
‹‹አለሁልህ…ገነት ገብቼለሁ››
‹‹ወደድሽው ማለት ነው››

‹‹እንዴ ትቀልዳለህ እንዴ …?አካባቢው እኮ እንኳን እንደእኔ አፍጥጠው የሚያዩ ሁለት አይኖች ላሉት ሰው ይቅርና አይነ-ስውር ቢመጣበት እንኳን ውበቱ በሽታ ሳይቀር ይታወቀዋል፡፡››
‹‹ዋው ድንቅ አገላለፅ ነው….በጣም ማርኮሻል ማለት ነው…እኔንም አንድ ቀን ወስደሽ እንደምታስጎበኚኝ ትስፋ አለኝ፡፡››
‹‹በደንብ እንጂ…ለዛውም በቅርብ ነዋ››
‹‹አሁን የት ነሽ…?ላለፉት አንድ ሰዓት ለሊሴ ጋር በሳይክል አካባቢውን ስናካልል ነበር.. አሁን ድክም ብለን ነዲ ካልቸራል ሴንተር የሚባለው ስፍራ ላይ ነን ፡፡
‹‹ምነው…ጠጅ እየጠጣችሁ ነው እንዴ?››ሲል ጠየቃት
‹‹አይ ትኩስ ወለላ ማር እየበላን››
‹‹በቃ ..ሰዓታችሁን አልውሰድባችሁ…..ዘና በሉ››
‹‹እሺ ቸው…ለሊሴ ሀይ እያለችህ ነው፡፡››
‹‹ሀይ በይልኝ‹‹ስልኩ ተዘጋ፡፡
‹‹አንቺ ሀለቃዬን ምን ልታደርጊው ነው?››ለሊሴ በመገረም ውስጥ ሆና ጠየቀቻት፡፡
‹‹ምን አደረኩብሽ…?››
‹‹እንዴ እያየሁ…ከተዋወቃችሁ ገና ሳምንት ነው..ግን ይሄውና በየቀኑ ይደውልልሻል፣ ገባሽለት እንዴ?››
‹‹አረ አንቺ ደግሞ…››በፀሎት እንደማፈር ብላ ተሸኮረመመች፡፡
‹‹ምነው..ቢሆን ደስ ይለኛል..ምርጥ ሸበላና የተማረ ሰው ነው..በዛ ላይ ትህትና አለው…እና አንቺን እህቴን ብድርለት በጣም ደስ ይለኛል››
‹‹በይ አንቺ ካዳመጡሽ …ብዙ ታወሪያለሽ››

ለደቂቃዎች ሁለቱም ዝም ተባባሉና በየግላቸው ሀሳብ መብሰልሰል ጀመሩ፣…በፀሎት ድንገት‹‹አካባቢው ግን አያስደንቅም?››ብላ አዲስ የመወያያ ርዕስ ከፈተች፡፡
‹‹ በጣም እንጂ…እያንዳንዱ ስፍራ የራሱ የሆነ እይታ አለው…አሁን ጎሮ ጋር ሆነሽ ቁልቁል ስታይ የተለየ አይነት እይታ..ከሊበን ሆነሽ ስታይው ደግሞ የተለየ አይነት እንደምታይው እዚህ ሆነሽ ስትመለከቾ ደግሞ ሌለ አይነት…በእውነት ይሄ በጣም አስገራሚ ነው፡፡ቦታ በቀየርሽ ቁጥር የምታይውም ነገር ይቀየራል…››
‹‹አዎ እንግዲህ …አምላክ ሲጠበብ ወሰን የለውም….››
‹‹እውነት ነው አምላክ ሲጠበብ ወሰን የለውም››የሚል ጣልቃ ገብ ዓ.ነገር  ሁለቱንም ከተቀመጡበት በርግገው እንዲነሱ አደረጋቸው፡፡ሌላ ሰው ነበር ከጀርባቸው የተናገረው፡፡
‹‹አንተ….እንዴት?››
‹‹ያው እንደዚህ››አለና ሁለቱንም በየተራ ሰላም አላቸው፡፡ተያይዘው ተቀመጡ፡፡
‹‹እዚህ ሆነህ ነበር እንዴ የምትደውልልኝ…?››በፀሎት በገረሜታና ባለማመን ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ…››
‹‹እኔ ደግሞ ምን አይነት ሞኝ ነኝ ..የት ነሽ ስትለኝ ያለሁበትን በየዋህነት መዘርዘሬ››
‹‹ምነው ስለመጣው ከፋሽ እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም››
የሰለሞንንና የበፀሎትን የማያቆርጥ ጥያቄና መልስ በዝምታ እየታዘበች በውስጦ እነዚህ ሰዎች ምንድነው እንዲህ ያቀራረባቸው..?ሰውዬውስ እሷን ፍለጋነው እንዴ እዚህ የመጣው
?እያለች በውስጦ ተብሰለሰለች ፡፡ልክ ልቧን እንዳነበበ ለጥያቄዎቾ መልስ ይሰጣት ጀመር…‹‹ያው ባለፀጋዎቹ ደንበኞቼ እዚህ ካልመጣን ሲሉ ተከትያቸው መጠሁ..ያው አስገድደው ሲያስደስቱኝ ምን ላድርግ..እየመጣሁ ሳለሁ ደግሞ እናንተ እዚህ እንዳላችሁ ትዝ ሲለኝ..የበለጠ ዘና አልኩ››
‹‹እና ታዲያ ሰዎችህ የታሉ?››በፀሎት ከወላጆቾ ጋር ድንገት ፊት ለፊት የመፋጠጥ ስጋት አስጨንቋት ጠየቀች


ጌዲዮን በፍቅረኛው ምክንያት ከእንዴም ሦስት ጊዜ ራሱን ሊያጠፋ ሞክሯል።

  ጌዲዮን የተባለ አንድ ደንበኛዬ ነበረ፡፡ ከፍቅረኛው ጋር ሲጋጩ በእግሩ ከሳሪስ ኮተቤ ሊገባ ይችላል፡፡ ይህ ደንበኛዬ ከእሷ በመለየቱ ራሱን ሊያጠፋ ብሎ ቤተሰቦቹ ናቸው ያመጡት፡፡ በምክክር ወቅት በጣም ነው የምወዳት፡፡ ከእሷ ተለይቼ መኖር አልችልም፡፡›› ነው ያለኝ፡፡

ቀጠለና ደግሞም ብዙ ሀያላን እኮ በፍቅር ምክንያት ሞተዋል›› ብሎ ነው የጠቀለለልኝ፡፡ እንግዲህ ዓለም ላይ ያሉ ሀያላን ለፍቅር መስዋዕት መሆናቸውን ኪነጥበቡ ነው የነገረው። ጌዲዮን ራሱን ለማጥፋት ከአንዴም ሦስት ጊዜ ሞክሯል፡፡ ይህ ደንበኛዬ በፍቅር ስም መታመምም መሞትም ልክ እንደሆነ አድርጎ ተቀብሏል፡፡ ለፍቅር መታመም ልክ ከሆነ ለምን ወደ ህክምና ይሄዳል? ለፍቅር ሲባል መስዋት ልክ ከሆነ ለምን መኖርን ይመርጣል? ችግሩ ይህ ነው፡፡

ለፍቅር ሲሉ ራሳቸውን መስዋዕት ያደረጉ በድራማ፣ በልብወለድ ወይም በእውኑ ዓለም ያሉትን ሰዎች እንደ ጀግና ነው የምንቆጥራቸው፡፡ እናጨበጭብላቸዋለን፡፡ “ጀግና” እንላቸዋለን፡፡ ናቸው ግን? የፍቅር ግቡ ራስን ማጥፋት ነው? ፍቅር ራስን ከማጥፋት ሳይሆን ከማኖር፣ ራስን ከመውደድ፣ ራስን ከማክበር ነው የሚጀምረው እንደውም፡፡

ጀግንነት ያለው ራስን በመውደድና በማክበር ውስጥ ነው፡፡ ፍቅር ማለት መስጠትና መቀበል ነው፡፡ ሰጥቶ መቅረት አይደለም፡፡ መቀበል ብቻም አይደለም፡፡ ለመስጠት መጀመሪያ አንተ ራስህ ሊኖርህ ይገባል፡፡ ኖሮህም ደግሞ ስመስጠት መፍቀድ አለብህ፡፡ በመስጠትህ ልትደስት ይገባሃል፡፡ ራስህን ልታዋርድ ሳይሆን ልታከብር ነው የሚገባህ፡

ጌዲዮን በፍቅረኛው ምክንያት ከእንዴም ሦስት ጊዜ ራሱን ሊያጠፋ ሞክሯል። ጌድዮን በሦስተኛው ጊዜ ራሱን ሊያጠፋ ሊሞክር ቤተሰቦቹ አይተው አተረፉት እናት አለቀሰች። ቤተሰቡ ሁሉ ተከዙ ከዚያ ቤተሰቡ ተሰብስቦ ‹ለምንድነው እዚህ ውሳኔ ላይየደረስከው አሉት፡፡

እኔ እወዳታለሁ፡፡ እሷ ደግሞ አልፈልግህም አለችኝ አለ፡፡ እናት በመጀመሪያ ልጀቷ ጋ ሄደው እግሯ ላይ ወድቀው ለመኗት። እሷ በጭራሽ አለች በልጅቷ በኩል የተሞከረው ስላልተሳካ በድጋሚ እንዲያደርገው የስነልቦና ባለሙያዎች ጋ መውሰድ የተሻለ መፍትሔ እንደሆነ አውቀው ነው ያመጡት፡፡

በመጀመሪያ ከጌድዮን ጋር ያደረግነው እንዲረጋጋና ነገሮችን በጤናማ አዕምሮ እንዲያስባቸው የተረጋጋ ሁኔታን መፍጠር ነው፡፡ ይህን ማድረግ ቀላል የማይባል ጊዜ ወስዶብናል፡፡ ከተረጋጋ በኋላ ደንበኛዬ እንደነገረኝ ምን ገጥሞታል መሰለህ?

ጌዲዮን በልጅነቱ በጣም የሚወዳቸው አባት፣ ሁለት ወንድምና እህቶች ነበሩት፡፡ 7 ኛ ዓመቱ ላይ በጣም የሚወዳቸው አባቱ ሞቱ፡፡

እናት የቤት አመቤት ስለሆኑ  በምን ሁኔታ ቤተሰቡን መምራት እንዳለባቸው ስለማያውቁ እዚህ ቤተሰብ ውስጥ ብዙ የተመሰቃቀሉ ሁኔታዎች ተፈጠሩ፡፡ እናት ገቢ ስላልነበራቸውና ልጆቹን ማሳደግ ስላልቻሉ ሁለቱን ሴቶች ለአንድ ዘመድ ፣ ቀሪዎቹን ሁለት ወንዶች ደግሞ ለሌላ ዘመድ እንዲያሳድጉላቸው ሰጧቸው።

ይህን ልጅ ስታየው መጀመሪያ አባቱን (በሕይወት) አጣ፡፡ ቆጥሎ እናቱን አጣ፡፡ ቀጥሎ ሁለት እህቶቹን አጣ፡፡ ቀጥሎ ደግሞ እሱና ወንድሙን የወሰዷቸው ዘመድ ‹‹ሁለቱን ማሳደግ አልችልም›› አሉና ወንድሙን ለሌላ ዘመድ ሰጡት፡፡ ወንድሙንም አጣ ማለት ነው፡፡ እሱ ባደገበት ቤተሰብ ውስጥ ልብስም፣ ምግብም ከሌሎቹ የተረፈው ነው የሚሰጠው፡፡ ምግብም እንደነገሩ ነው፡፡

ጌዲዮን “እልህ ያዘኝ አለ። ይህን ሁሉ ም ስቅልቅል መለወጥ የሚችለው ራሱን በትምህርት ሲያበለጽግ ብቻ መሆኑን ስለተረዳ መማርለድርድር የማይቀርብ የሕይወት ጉዳዩ አድርጎ ያዘው፡፡ እንዳሰበውም በትምህርቱ ጎልቶ የሚታይ ልጅ ሆነ።

9ኛ ክፍል ሲገባ ከአንዲት ቆንጆ ኮረዳ ጋር ይቀራረባል፡፡ “እፎይ! አንድ የማምነው ሰው አገኘሁ አልኩ ይላል። አባቱን፣ እናቱን፣ ቤተሰቦቹን አጥቶ ይህቺ ልጅ ናት በቅርቡ ያለችውና የሆዱን ሊያወራት የምትችል ብቸኛ ልጅ፡፡ ይህቼም ልጅ ግን እንዴት እንደሆነ ሳያውቀው እዚያው ክፍላቸው ውስጥ ካለ እንዱ ጎረምሳ ጋር ፍቅር ይይዛትና ጌዲዮንን “አልፈልግህም›› ትለዋለች፡፡

እንደገና ሌላ ማጣት በሕይወቱ ውስጥ መጣ ማለት ነው፡፡ አራተኛ ወይም አምስተኛ ማጣት፡፡ ከዚያ ሕይወት ቀጠለና ዩኒቨርሲቲ ገባ፡፡

ዩኒቨርሲቲም ሌላ ፍቅረኛ ያዘ፡፡ እሷም በማያውቀው ምክንያት እየሸሸችው፣ እየሸሸችው ትመጣለች። እንደገና ሌላ ማጣት፡፡ ከዩኒቨርሲቲ ከወጣ በኋላ “እፎይ! ሕይወትን ማሸነፍ ቻልኩ›› ብሎ እናቱን ማገዝ ጀመረ፡፡ እህትና ወንድሞቹም ደረሱ። የፈረሰው ቤተሰብ እንደገና መቋቋም ቻለ ማለት ነው፡፡

ከዚያ በኋላ ይህቺን ራሱን ለማጥፋት ሙከራ ያደረገባትን ልጅ ተዋወቃት፡፡ ጌዲዮን ለፍቅረኛው ደውሎ ልጅቷ ስልክ ካላነሳች ወይም ትንሽ ዝም ካለች በጣም ነው የሚናደደው፡፡ ሰውነቱ ይንቀጠቀጣል፡፡ በጣም ይበሰጫጫል፡፡

አንድ ዕለት ፍቅረኛው ጋ ደውሎ ስልክ ሳታነሳ ስትቀር እየበረረ ቢሮዋ ሄደ፡፡ እሷ ትልቅ ድርጅት ውስጥ ነው የምትሰራው፡፡ ጌዲዮን በስሜት ተሞልቶ ጥበቃውን ገፈታትሮ ነው የገባው፡፡ ጭንቅላቱ ውስጥ ያለው “ከሌላ ወንድ ጋር ትሆናለች›› ወይም «ጥላኝ ሄዳለች የሚል ሀሳብ ነው፡፡ ቢሮዋ ሲደርስ ግን ስልኳን ቻርጅ ልታደርግ ሰክታው ያገኛል፡፡ ፍቅረኛው ይህ ሁሉ ከምትችለው አቅም በላይ ስለሆነባት ‹‹ከአንተ ጋርመቀጠል አልፈልግም፤ እንለያይ›› ትለዋለች፡፡

ቲጂ  የምፈልጋቸውን ሰዎች ማጣት ለእኔ አዲስ ነገር አይደለም፡፡ ይህቺን ልጅ ማጣት ግን ለምን አዲስና የማልችለው እንደሆነብኝ አላውቅም.. አለኝ፡፡

ጌዲዮን ይህቺን ልጅ ማጣቱ በራስ የጎዳው መስሎት ነው የተሰማው፡፡ ይህቺን ልጀ ማጣት አዲስና የማይችለው ሆኖበት አይደለም እሱ እንደሚለውም ፍቅረኛውን ማጣቱ የጎዳው እሱ እንደሚያስበው ከሌሎቹ ሁሉ እሷ በልጣ አይደለም፡፡ እሷ የተጠራቀመው የአዕምሮ ቁስለቱ ውጤት ናች።  ይህ ስሜት አባቱን በሞት፣ እናቱን፣ እህትና ወንድሞቹን በኑሮ፣ ናቅረኛውን በመለየት ከማጣቱ ጋር በቀጥታ የተያያዘ ነው፡፡ የእሷ ጉዳይ የዛራ ብቻ አይደለም:: በ7 ዓመቱ አባቱን በሞት ከመነጠቁና ቤተሰቡ ከእራሱ ጋር ይያያዛል። ውስጡ ያላወቀው የማጣት ፍርሀት አለበት፡፡

ፍቅረኛ ስልክ ባለማንሳቷ ከቢሮ ወጥቶ ቢሮዋ ድረስ የሄደው በዚህ ፍርኮት ተገፍቶ ነው። እሱ ማጣት አዲሴ አይደለም፡፡ ለምን እዚህችኛዋ ላይ አዲስ ሆነብኝ? ነው ያለው፡፡ ውጤቱ ግን በግልባጩ እዚህችኛዋ ላይ ጉዳቱን ያበረታበት ማጣት አዲሱ አለመሆነ ነው፡፡ አዲሱ ስላልሆነ የተለማመደው መስሎታል። ግን መለማመድ ሳይሆን ይበልጥ ፍርሀት ውስጥ ነው የከተተው፡፡ ያ ፍርሀት ነው ዛሬ ራሱን ለማጥፋት እስኪነሳ ያደረሰው፡፡

ምንሆኛለሁ መፅሃፍ ገፅ 32

አላለቀም አንብበው ከወደዱት እንዲቀጥል 👍👍 React


ትራኦሬ‼

በ 2 አመት የፕሬዝዳንት ዘመኑ ኢብራሂም ትራኦሬ ለቡርኪና ፋሶ ምን ሰራ?

1. የቡርኪና ፋሶ GDP ከ18.8 ቢሊዮን ዶላር ወደ 22.1 ቢሊዮን ዶላር እንድያድግ አድርጓል።

2. ከዓለም አቀፍ ገንዘብ አበዳሪ እና ድጋፍ ሰጪ ተቋማት ገንዘብ አልተበደረም ድጋፍም አላገኘም::

3. የሚኒስትሮችን እና የፓርላማ አባላትን ደም እና ወዝ በ30% በመቀነስ የመንግስት ሰራተኞችን ደሞዝ በ50% ጨምሯል።

4. የቡርኪና ፋሶን የሀገር ውስጥ ዕዳ ከፍሏል።

5. በቡርኪና ፋሶ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለት የቲማቲም ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን አቋቁሟል

6. የአገር ውስጥ የማቀነባበር አቅሞችን ለማሳደግ ዘመናዊ የወርቅ ማዕድን ማውጫ ፋብርካ አስመርቋል።

7. እሴት ያልተጨመረበት የቡርኪና ፋሶ ወርቅ ወደ አውሮፓ እንዳይወጣ አድርጓል

8. የቡርኪና ፋሶ ሁለተኛ ግዙፍ የጥጥ ማቀነባበሪያ ፋብሪካን ገንብቷል።

9. አርሶ አደሮችን የእደ ጥበብ ስራ ለማበረታታት ለመርዳት ለመጀመሪያ ጊዜ ብሔራዊ ለዕደ-ጥበብ ጥጥ ማቀነባበሪያ ከፍቷል።

10. የብሪታንያ ህጋዊ ዊግ እና ጋውንን በአካባቢ ፍርድ ቤቶች እንዳይለብሱ በመከልከል የሀገረው ሰው ባህላዊ የቡርኪናቤ ልብሶችን እንድለብስ አበረታትተዋል።

11. ምርትና ምርታማነትን ለማሳደ እርሻ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ አደርሶ አደሮች ከ400 ትራክተሮች፣ 710 የውሃ ፓምፖች እና 714 ሞተር ሳይክሎች በማከፋፈል ለግብርናውን ነማዘመን ስራ ሰርቷል።

12. የግብርና ምርትን ከፍ ለማድረግ ምርጥ ዘርና ሌሎች የእርሻ ግብአቶችን አቅርቧል።

13. የቡርኪና ፋሶን የቲማቲም ምርት ወደ ስልጣን ስመጣ ከነበረበት 315,000 ሜትሪክ ቶን በ2024 ወደ 360,000 ሜትሪክ ቶን አሳድጓል።

14. የሩዝ ምርት በ2022 ከነበረበት 280,000 ሜትሪክ ቶን በ2024 ወደ 326,000 ሜትሪክ ቶን አሳድጓል።

15. የፈረንሳይ ሚዲያን በቡርኪና ፋሶ አግዷል።

17. የፈረንሳይ ወታደሮችን ከቡርኪና ፋሶ አስወጥቷል።

18. መንግስታቸው አዳዲስ መንገዶችን በመገንባት ነባሮቹን በማስፋት እና የጠጠር መንገዶችን ወደ አስፋልት ደረጃ እያሳደገ ነው።




‹‹እሱማ ምን ጥርጥር አለው….ግን እንደው ትረዳዋለች ወይ የሚለው ጥርጣሬ አድሮብኝ ነው..እሷን ለማታለል ለማስመሰል ያደረግነው መስሎ እንዳይሰማት››ወ.ሮ ስንዱ ጥርጣሬያቸውን አሰሙ፡፡
‹‹እሷ የምታውቀንን ያህል እኛ እኮ ልጃችንን አናውቃትም …..››ሃይለልኡል የሚስታቸው ሀዘንና ጥርጣሬ ውደውስጣቸው እንዳይገባ እየታገሉ መለሱ፡፡
‹‹እሱስ እውነትህን ነው….የልጃችን ትልቅ ውለታ አለብን››
‹‹አዎ .አሁን ልጃችን በጣም በስላለች…ምን አስቤለው መሰለሽ….ካምፓኒው ውስጥ የሆነ ቦታ ይዛ ስራ መጀመር አለባት…እኔ በቅርቡ ጡረታ ወጥቼ ከአንቺ ጋር አለምን እየዞርኩ ዘና

ማለት ነው የምፈልገው…ከአሁን በኃላ በተጨናነቀው የቢዝነስ አለም ውስጥ ቀሪ ህይወቴን ማባከን አልፍልግም››
‹‹እና ስራውን ሙሉ በሙሉ እንድትረከብህ ነው የምትፈልገው?፡፡››
‹‹አዎ ከእኔ ጋር ሆና አንድ ሁለት አመት ከሰራች በቃ ከእኔ በተሻለ ውጤታማ እንደምትሆን እርግጠኛ ነኝ..እይ እስኪ እኔና አንቺን ወደስምምነት ለማምጣት የተጠቀመችበት የረቀቀ ውጤታማ ዘዴ….እንዴት እንዳቀናጀችው…ያን የመሰለ ባለሞያ እንዴት እንደመለመለች
…በእውነት ይህቺ የእኛ ልጅ ነች ብዬ እስክደነቅ ድረስ ነው ያስደመመችኝ፡፡››በንግግራቸው ኩራታቸውን ሲግልፁ ፊታቸውም በደስታ እያበራ ነበር፡፡

…በሶስተኛው ቀን
ሰለሞንና በፀሎት ቢያንስ በቀን አንድና ሁለት ጊዜ እየተደዋወሉ ለረጅም ሰዓት ማውራትና የተለያዩ ርዕሶች እያነሱ መወያየት ልምድ አድርገውታል..ይሄ ደግሞ እርስ በርስ የበለጠ እንዲተዋወቁና በደንበኝነት መልክ ሳይሆን ልክ እንደአንድ የልብ ጓደኛ ወጣ ባለ ርዕሶች ላይም ረጅም ሰዓት ማውራት ጀምረዋል፡፡፡ይሄ ጉዳይ ለሁለቱም በጣም ተመችቷቸዋል፡፡አሁንም ተደዋውለው እያወሩ ነው፡፡
በፀሎት‹‹አንድ ሰው እንዳፈቀረን እንዴት ማወቅ እንችላለን…?ለምሳሌ እኔ አንድ አብሮኝ ያለ ወንድ የእውነት እንደሚያፈቅረኝና በምን ማረጋገጥ እችላለው፡፡››ስትል ያስደነቀውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹ሴት ልጅ ካለገመች በስተቀር አንድ ወንድ እንደሚያፈቅራትና እንደማያፈቅራት በቀላሉ መለየት ትችላለች…አንዳንድ ጊዜ ግን ምን ይሆናል ?እሷ በጣም ካፈቀረችው እሱ እንደማያፈቅራት ብታውቅ እንኳን ሽንፈትን ላለመቀበል ብላ እንደሚያፈቅራት እራሷን ለማሳመን ትጣጣራለች..የዛን ጊዜ የምታያቸውን ምልክቶች ሁሉ በተቃራኒው ተርጉማ ለመረዳት ትሞክራለች››
‹‹እና ምልክቶቹ ምን ምን ናቸው?››

‹‹ለምሳሌ ድምፅሽን ለመስማት ብቻ ይጠራሻል።ስትስቂ ስቆ ስታለቅሺም ያለቅሳል። ከመተኛቱ በፊት በመጨረሻዋ ደቂቃና ከእንቅልፍ በነቃ በመጀመሪያው ደቂቃ ስለአንቺ ነው የሚያስበው።ያለምክንያት ሊያቅፍሽ እና ከሰውነቱ ሊለጥፍሽ ይፈልጋል።አንቺን ከነማንነትሽ ለመቀበል ፍቃደኛ ሆኖ ይገኛል።አንቺን በሌላ ለመቀየር ፍፅም ፍቃደኛ አይደለም።ስህተት ሲሰራ አንቺ እንዲያስተካክል ከመጠየቅሽ በፊት ቀድሞ ለማስተካከል ጥረት ሲያደርግ ታገኚዋለሽ፤ሁል ጊዜ ሊረዳሽ ጥረት ያደርጋል።እንቅልፍ አሸልቦሽ ሊመለከትሽ ነቅቶ ይጠብቃል።ግንባርሽን በስስት ይስማል።መክሳትሽም ሆነ ክብደት መጨመርሽ ከውበትሽ አንፃር ብዙም አያስጨንቀውም፡፡በጓደኞቹ መካከል እጆችሽን ይይዛል።ወይም አቅፎ ጉያው ይሸጉጥሻል።ወዘተ…እንግዲህ እኚንና መሰል ምልክቶችን በማየትና በማመዛዘን አንድ ሰው አፍቅሮሽ ይሁን ወይስ አይሁን መለየት ትችያለሽ››
‹‹እሺ ወሲብስ ምንድነው..?በፍቅር ውስጥ ያለው ድርሻስ?››
‹‹ወሲብን የፍቅር ተጣማሪሽ ጋር ያለሽን ግንኙነት ለማጠንከር እና ለማዋሀድ እንደ ሲሚንቶ የሚያገለግል ተፈጥሯዊ ቅመም ነው፡፡ወሲብ በአግባቡ ከተጠቀምሽበት ፍቅርን በማሳደግና በማጎልበት ትልቅ የሆነ ድርሻ አለው፡፡አይደለም ወሲብ መተሻሸትና መሳሳም እራሱ የፍቅር ግለትን ጠብቆ ለማስቀጠል ትልቅ ጥቅም አለው፡፡››
‹‹እና ከፍቅረኛሽ ጋር ተሳሳሚ እያልከኝ ነው››
‹‹ፍቅረኛው ካለ አዎ በደንብ..ጥናቶች እንደሚያሳዩት ሚስቶች በጋብቻ ውስጥ ከከራረሙ በኃላ ለመሳሳም ያላቸው ፍላጎትና ትኩረት በጣም ይቀንሳል ወይም እስከወዲያኛው ይጠፋል።ላጤዎች ደግሞ ብዙውን ጊዜ በዚህ ረገድ ትኩስና ያልተገደበ ፍላጎት ይኖራቸዋል፡፡ይሄ ግን አግባብ አይደለም ።ባልዬው ድንገት ውጭ ሌላ ላጤ ሴት ቢያጋጥመው ከኤክስፐርት ጋር ነው የሚላተመው...ልዩነቱ ሰፊ ስለሚሆንበት ይከብደዋል።ቶሎ ስህተቱን ለማረም እንዳይችል ይፈተናል።››
‹‹እኔ ግን ሳገባ እንደዛ አላደርግም…ለባሌ በጣም የምመቸው ይመስለኛል›››
‹‹እያስጎመዠሺኝ ነው››
‹‹ምን ያስጎመዠሀል ..አንተን አላገባ?››

‹‹ምን ይታወቃል….ካፈቀርሺኝ ለምን አታገቢኝም?››
‹‹ሳላውቅህ እንዴት ላፈቅርህ እችላለው?››
‹‹ከዚህ በላይ እንዴት ታውቂኛለሽ..ለወራት ድምፄን በስልክ ስትሰሚ ነበር…በቀደም ደግሞ በአካል አይተሸኛል…ምነው አላምርም እንዴ?››
‹‹አረ ቆንጆ ነህ…ግን ቁንጅና ብቻ በቂ አይደለም››
‹‹እስኪ እናያለን››
‹‹ለማንኛውም ለባልሽ መዋብ የምትጀምሪው ከእርቃን ገላሽ ጀምሮ መሆን አለበት...ፓንትሽንና ጡት ማሲያዛሽን የሚያየው ባልሽ ነው።...ለእነሱ ትኩረት መስጠት መቻል በባልሽ እና በአንቺ የፍቅር ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ይፈጥራል።ከላይ ያሉ ልብሶችሽን፣ ፀጉርሽን ፣ጌጣ ጌጦችሽን ለሁሉም ሰው በጋራ የምታደርጊያቸው መዋቢያዎች ናቸው።የውስጥ ልብሶችሽ ጥራት ግን የባልሽ ስሜት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እንደሚኖራቸው ግንዛቤ ሊኖርሽ ይገባል፡፡››
‹‹ገባኝ››

‹‹አይ ስለአንቺ እኮ አይደለም ያወራውት አጠቃላይ ስለፍቅር እና ፍቅረኛሞች ለማውራት ፈልጌ ነው…ባልሽ በአጋጣሚ የሚያገኛቸው እንግዳ ሴቶች ድንገት ፊቱ ልብሳቸውን የማውለቅ እድል ካገኙ እመኚኝ የውስጥ ልብሶቻቸው ብቻ አይደሉም ውብና አማላይ የሚሆነው.. ለሊቱንም ውብና አማላይ እና ያልተለመደ አይነት ያደርጉለታል።አንቺ ሚስቱ ነሽና ብዙ ኃላፊነትና የህይወት ውጣ ውረዶች ስላለብሽ የአመቱን ቀናቶች ሁሉ ውብና አማላይ ልታደርጊለት አትቺይም ግን በሳምንት አንድ ቀን ካልሆነም በወር አንድ ቀን መቼም ሊረሳው የማይችል እንደዛ አይነት ውብ ለሊቶችን በገፀ-በረከትነት ልታቀርቢለት ይገባል።የዛኔ ከውጭ፣በአጋጣሚ የሚፈቱኑትን በልበ ሙሉነት ሊያልፋቸው አቅም ይኖረዋል።››
‹‹ይገርማል …ምንም ሳልከፍልህ በነፃ የቅድመ ጋብቻ ስልጠና እየሰጠኸኝ ነው፡፡››
‹‹ያው ማወቅሽ ዞሮ ዞሮ ጥቅሙ ለእኔው ነው ብዬ ነው››
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹ነገርኩሽ እኮ…ምን አልባት እድለኛው ባልተቤትሽ እኔው ልሆን እችላለሁ››

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት መንደር
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

20 last posts shown.