Forward from: Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አንዳንድ እህቶች ኒካሕ ሲቃረብ አባቶቻቸው ሺርክ ላይ እንደሆኑ በመጥቀስ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ይጠይቃሉ።
1- በመጀመሪያ የእውነት ሺርክ መኖሩን በተጨባጭ ማረጋገጥ ይገባል። ኹራፋት፣ ቢድዐዎች፣ ተወሱላት ብቻቸውን ሺርክ ላይ ላይደርሱ ይችላሉ። ችግሩ እዚያ የሚደርስ መሆን አለመሆኑን በትክክል መለየት ይገባል።
2- በተጨባጭ አባት ሺርክ ላይ መሆኑ ከተረጋገጠ ተስፋ ሳይቆርጡ የሚችሉትን ሁሉ ጥረት በማድረግ ለመመለስ መጣር ይገባል። ይሄ የኒካሕ ሰሞን ሳይሆን ቀድሞ ነው ሊሰራበት የሚገባው። ከኒካሑ የበለጠ የሚያሳስበው ይሄ ነው። "ክፉ ደግ አይቶ፣ ለፍቶ ያሳደገኝ አባቴ ኒካሕ አታስርም ሲባል በጣም አዘንኩኝ፣ ከፋኝ፣ ..." የሚል የዓጢፋ (ስሜት) ንግግር ዋጋ የለውም። ሺርክ ከኢስላም የሚያስወጣ፣ ዘላለማዊ ክስረትን የሚያስከትል፣ እስከወዲያኛው ከሚወዱት የሚለያይ ከባድ ጥፋት ነው። ከኒካሑ በፊት ሺርክ ውስጥ ሲኖሩ ያልተሰማን ስሜት "ወሊይ አይሆኑም" ሲባሉ ከተሰማን ችግሩ ከራሳችን ነው። ገና ያልጠራ ነገር አለ ማለት ነው። እናጥራ።
3- በተረፈ ከኢስላም የሚያስወጣው ትልቁ ሺርክ መኖሩ በተጨባጭ ተረጋግጦ፣ ተመክረው ተዘክረው ከተቀበሉ ወሊይ ሆነው ኒካሑን ያስራሉ። ከኢስላም የሚያስወጣው ትልቁ ሺርክ መኖሩ በተጨባጭ ተረጋግጦ፣ ተመክረው ተዘክረው ለመቀበል አሻፈረኝ ካሉ ግን ወሊይ ሆነው ኒካሕ ሊያስሩ አይፈቀድም። ከዚህ ዝቅ ባለ ጉዳይ ሶላት የማይሰግዱ ሆነው እንዲሰግዱ ቢመከሩም ፈቃደኛ ካልሆኑ ግን ለኒካሕ አይሆኑም። የሶላት ጉዳይ በንፅፅር ከተውሒድ ያነሰ ከመሆኑ ጋር ማለት ነው።
4- እንዲህ አይነት ሁኔታ ከገጠመ ወሊይነቱ ወደሌላ ቅርብ ቤተሰብ ይሻገራል። ኒካሑ በነሱ በኩል ይታሰራል። ለኒካሕ የሚሆን ቤተሰብ ከሌለ በቃዲ ይታሰራል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
1- በመጀመሪያ የእውነት ሺርክ መኖሩን በተጨባጭ ማረጋገጥ ይገባል። ኹራፋት፣ ቢድዐዎች፣ ተወሱላት ብቻቸውን ሺርክ ላይ ላይደርሱ ይችላሉ። ችግሩ እዚያ የሚደርስ መሆን አለመሆኑን በትክክል መለየት ይገባል።
2- በተጨባጭ አባት ሺርክ ላይ መሆኑ ከተረጋገጠ ተስፋ ሳይቆርጡ የሚችሉትን ሁሉ ጥረት በማድረግ ለመመለስ መጣር ይገባል። ይሄ የኒካሕ ሰሞን ሳይሆን ቀድሞ ነው ሊሰራበት የሚገባው። ከኒካሑ የበለጠ የሚያሳስበው ይሄ ነው። "ክፉ ደግ አይቶ፣ ለፍቶ ያሳደገኝ አባቴ ኒካሕ አታስርም ሲባል በጣም አዘንኩኝ፣ ከፋኝ፣ ..." የሚል የዓጢፋ (ስሜት) ንግግር ዋጋ የለውም። ሺርክ ከኢስላም የሚያስወጣ፣ ዘላለማዊ ክስረትን የሚያስከትል፣ እስከወዲያኛው ከሚወዱት የሚለያይ ከባድ ጥፋት ነው። ከኒካሑ በፊት ሺርክ ውስጥ ሲኖሩ ያልተሰማን ስሜት "ወሊይ አይሆኑም" ሲባሉ ከተሰማን ችግሩ ከራሳችን ነው። ገና ያልጠራ ነገር አለ ማለት ነው። እናጥራ።
3- በተረፈ ከኢስላም የሚያስወጣው ትልቁ ሺርክ መኖሩ በተጨባጭ ተረጋግጦ፣ ተመክረው ተዘክረው ከተቀበሉ ወሊይ ሆነው ኒካሑን ያስራሉ። ከኢስላም የሚያስወጣው ትልቁ ሺርክ መኖሩ በተጨባጭ ተረጋግጦ፣ ተመክረው ተዘክረው ለመቀበል አሻፈረኝ ካሉ ግን ወሊይ ሆነው ኒካሕ ሊያስሩ አይፈቀድም። ከዚህ ዝቅ ባለ ጉዳይ ሶላት የማይሰግዱ ሆነው እንዲሰግዱ ቢመከሩም ፈቃደኛ ካልሆኑ ግን ለኒካሕ አይሆኑም። የሶላት ጉዳይ በንፅፅር ከተውሒድ ያነሰ ከመሆኑ ጋር ማለት ነው።
4- እንዲህ አይነት ሁኔታ ከገጠመ ወሊይነቱ ወደሌላ ቅርብ ቤተሰብ ይሻገራል። ኒካሑ በነሱ በኩል ይታሰራል። ለኒካሕ የሚሆን ቤተሰብ ከሌለ በቃዲ ይታሰራል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor