በባለሀብቶች የታሪፍ ፍራቻ የተነሳ የነዳጅ ዋጋ እየቀነሰ ነው ተባለ
ወደ አሜሪካ በሚገቡ ምርቶች ላይ የሚጣለው ታሪፍ በአለም ኢኮኖሚ እድገት እና በነዳጅ ፍላጎት ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ፣ እንዲሁም ከኦፔክ የነዳጅ አምራች ሀገራት የነዳጅ ምርት እየጨመረ በመምጣቱ፣ ባለሃብቶች ላይ ስጋትን አሳድራል። ያልተጣራው ድፍድፍ ነዳጅ አርብ እለት 90 ሳንቲም በ6 ሳንቲም ቀንሶ ወደ 70.30 ዶላር ዝቅ ብሏል። የዩናይትድ ስቴትስ ዌስት ቴክሳስ ገበያ ድፍድፍ በ ነዳጅ በ66.96 ዶላር በበርሚል የተሸጠ ሲሆን በስምንት ሳንቲን ቀንሷል።
ለሰባተኛ ተከታታይ ሳምንት ነዳጅ ቀንሷል፣ ይህም ከህዳር 2023 ወዲህ ረጅሙ የኪሳራ ጉዞ ተደርጎ ተወስዷል። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና ምርቶች ላይ ግብር መጣላቸው እንዲሁን በዋና ዘይት አቅራቢዎቻቸው ላይ ካናዳ እና ሜክሲኮ የዘገየ ታሪፍ ከጣሉ በኋላ ድፍድፍ ነዳጅ ለሶስተኛ ተከታታይ ሳምንት ቀንሷል። ቻይና በአሜሪካ እና ካናዳ የግብርና ምርቶች ላይ የአፀፋ ታሪፍ መጣሏ ይታወሳል።
ትራምፕ ሞስኮ ከዩክሬን ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻለች ዩናይትድ ስቴትስ በሩስያ ላይ የምትጥለውን ማዕቀብ እንደምትጨምር ከተናገረች በኋላ አርብ እለት የነዳጅ ዋጋ ቀንሷል። ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የምታደርገውን ጦርነት ለማቆም ከተስማማች ዩናይትድ ስቴትስ በሩሲያ የኃይል ማመንጫ ዘርፍ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ለማርገብ የሚያስችል መንገድ እያጠናች ነው ሲሉ ጉዳዩን የሚያውቁ ሁለት ምንጮች ለሮይተርስ ተናግረዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኦፔክ ፕላስ በመባል የሚታወቀው ሩሲያን ጨምሮ የነዳጅ ላኪ ሀገራት ድርጅት እና አጋሮቹ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ በዘይት ምርት ጭማሪ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ኖቫክ እንዳሉት ኦፔክ ፕላስ የገበያ ሚዛን በሚኖርበት ጊዜ ውሳኔውን ሊቀይር ይችላል ሲሉ ተደምጠዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ወደ አሜሪካ በሚገቡ ምርቶች ላይ የሚጣለው ታሪፍ በአለም ኢኮኖሚ እድገት እና በነዳጅ ፍላጎት ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ፣ እንዲሁም ከኦፔክ የነዳጅ አምራች ሀገራት የነዳጅ ምርት እየጨመረ በመምጣቱ፣ ባለሃብቶች ላይ ስጋትን አሳድራል። ያልተጣራው ድፍድፍ ነዳጅ አርብ እለት 90 ሳንቲም በ6 ሳንቲም ቀንሶ ወደ 70.30 ዶላር ዝቅ ብሏል። የዩናይትድ ስቴትስ ዌስት ቴክሳስ ገበያ ድፍድፍ በ ነዳጅ በ66.96 ዶላር በበርሚል የተሸጠ ሲሆን በስምንት ሳንቲን ቀንሷል።
ለሰባተኛ ተከታታይ ሳምንት ነዳጅ ቀንሷል፣ ይህም ከህዳር 2023 ወዲህ ረጅሙ የኪሳራ ጉዞ ተደርጎ ተወስዷል። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቻይና ምርቶች ላይ ግብር መጣላቸው እንዲሁን በዋና ዘይት አቅራቢዎቻቸው ላይ ካናዳ እና ሜክሲኮ የዘገየ ታሪፍ ከጣሉ በኋላ ድፍድፍ ነዳጅ ለሶስተኛ ተከታታይ ሳምንት ቀንሷል። ቻይና በአሜሪካ እና ካናዳ የግብርና ምርቶች ላይ የአፀፋ ታሪፍ መጣሏ ይታወሳል።
ትራምፕ ሞስኮ ከዩክሬን ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻለች ዩናይትድ ስቴትስ በሩስያ ላይ የምትጥለውን ማዕቀብ እንደምትጨምር ከተናገረች በኋላ አርብ እለት የነዳጅ ዋጋ ቀንሷል። ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የምታደርገውን ጦርነት ለማቆም ከተስማማች ዩናይትድ ስቴትስ በሩሲያ የኃይል ማመንጫ ዘርፍ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ለማርገብ የሚያስችል መንገድ እያጠናች ነው ሲሉ ጉዳዩን የሚያውቁ ሁለት ምንጮች ለሮይተርስ ተናግረዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ኦፔክ ፕላስ በመባል የሚታወቀው ሩሲያን ጨምሮ የነዳጅ ላኪ ሀገራት ድርጅት እና አጋሮቹ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ በዘይት ምርት ጭማሪ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ኖቫክ እንዳሉት ኦፔክ ፕላስ የገበያ ሚዛን በሚኖርበት ጊዜ ውሳኔውን ሊቀይር ይችላል ሲሉ ተደምጠዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter