በሐማስ እና በእስራኤል መካከል አዲስ የተኩስ አቁም ድርድር ሊደረግ ነው
በሐማስ እና በእስራኤል መካከል አዲስ የተኩስ አቁም ድርድር ሊደረግ መሆኑን ምንጮች ለቢቢሲ ገለጹ።
ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ፍልስጤማዊ ባለሥልጣን እንዳሉት የኳታር እና የግብፅ አደራዳሪዎች አዲስ የተኩስ አቁም ድርድር እያረቀቁ ነው።
የተኩስ አቁሙ ከአምስት እስከ ሰባት ዓመታት የሚዘልቅ እንደሚሆን ምንጩ ገልጸዋል። ሁሉም እስራኤላውያን ታጋቾች ተለቀው በምላሹ በእስራኤል እስር ቤቶች የሚገኙ ፍልስጤማውያን ይለቀቃሉ።
ጦርነቱ በይፋ ቆሞ የእስራኤል ወታደሮች ሙሉ በሙሉ ከጋዛ እንዲወጡም ይደረጋል።
በጉዳዩ ላይ ምክክር ለማድረግ የሐማስ ልዑካን ወደ ካይሮ እንደሚሄዱ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ከአንድ ወር በፊት መፍረሱ ይታወሳል። ስምምነቱ ለመፍረሱ ሁለቱ ወገኖች አንዳቸው ሌላውን ሲከሱ፣ እስራኤል ጋዛ ላይ ጥቃት መፈጸም ቀጥላለች።
ነገር ግን አዲስ ድርድር ሊደረግ ስለመሆኑ እስካሁን ከእስራኤል በኩል የተባለ ነገር የለም።
የሐማስ የፖለቲካ ክንፍ ኃላፊ ሞሐመድ ዳርዊሽ እና ዋና ተደራዳሪው ኻሊል አል-ሀያ በካይሮ ለድርድር እንደሚገኙ ተጠቁሟል።
@Ethio_fastnews🤩
@Ethio_fastnews🤩
በሐማስ እና በእስራኤል መካከል አዲስ የተኩስ አቁም ድርድር ሊደረግ መሆኑን ምንጮች ለቢቢሲ ገለጹ።
ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ፍልስጤማዊ ባለሥልጣን እንዳሉት የኳታር እና የግብፅ አደራዳሪዎች አዲስ የተኩስ አቁም ድርድር እያረቀቁ ነው።
የተኩስ አቁሙ ከአምስት እስከ ሰባት ዓመታት የሚዘልቅ እንደሚሆን ምንጩ ገልጸዋል። ሁሉም እስራኤላውያን ታጋቾች ተለቀው በምላሹ በእስራኤል እስር ቤቶች የሚገኙ ፍልስጤማውያን ይለቀቃሉ።
ጦርነቱ በይፋ ቆሞ የእስራኤል ወታደሮች ሙሉ በሙሉ ከጋዛ እንዲወጡም ይደረጋል።
በጉዳዩ ላይ ምክክር ለማድረግ የሐማስ ልዑካን ወደ ካይሮ እንደሚሄዱ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ከአንድ ወር በፊት መፍረሱ ይታወሳል። ስምምነቱ ለመፍረሱ ሁለቱ ወገኖች አንዳቸው ሌላውን ሲከሱ፣ እስራኤል ጋዛ ላይ ጥቃት መፈጸም ቀጥላለች።
ነገር ግን አዲስ ድርድር ሊደረግ ስለመሆኑ እስካሁን ከእስራኤል በኩል የተባለ ነገር የለም።
የሐማስ የፖለቲካ ክንፍ ኃላፊ ሞሐመድ ዳርዊሽ እና ዋና ተደራዳሪው ኻሊል አል-ሀያ በካይሮ ለድርድር እንደሚገኙ ተጠቁሟል።
@Ethio_fastnews🤩
@Ethio_fastnews🤩