የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን አዋጅ እንዲያሻሽል፤ የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ለተቆጣጣሪ መስሪያ ቤት አቅጣጫ ሰጠ
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የቦርድ ውክልናን ጨምሮ “በርካታ ክፍተቶች አሉበት” ያለውን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ እንዲሻሻል ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ።
ባለስልጣኑ “አላሰራ ያሉ አዋጆችን እንዲሻሻሉ ለማድረግ” ለሚያከናወናቸው ስራዎች፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት “ተገቢውን ድጋፍ” እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ይህ የተገለጸው የፓርላማው የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንን የስራ እንቅስቃሴ ትላንት ሰኞ ጥር 26፤ 2017 ተዘዋውሮ በተመለከተበት ወቅት ነው።
በመስክ ምልከታው የተገኙ አምስት የቋሚ ኮሚቴው አባላት፤ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን የስራ ኃላፊዎች፣ ሰራተኞችን እና ተገልጋዮችን ማነጋገራቸውን ከተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በዚሁ ጊዜ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንን ያለፉትን የስድስት ወራት የስራ እንቅስቃሴ በተመለከተ፤ የመስሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ገለጻ አድርገዋል።
አቶ ሳምሶን በዚሁ ገለጻቸው፤ ባለስልጣኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅን ለማሻሻል “እየሰራ” እንደሆነ መናገራቸውን የተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት በማህበራዊ የትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ ላይ አስፍሯል።
🔴 ለዝርዝሩ ▶️ https://ethiopiainsider.com/2025/14994/
@EthiopiaInsiderNews
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የቦርድ ውክልናን ጨምሮ “በርካታ ክፍተቶች አሉበት” ያለውን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ እንዲሻሻል ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገለጸ።
ባለስልጣኑ “አላሰራ ያሉ አዋጆችን እንዲሻሻሉ ለማድረግ” ለሚያከናወናቸው ስራዎች፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት “ተገቢውን ድጋፍ” እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ይህ የተገለጸው የፓርላማው የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንን የስራ እንቅስቃሴ ትላንት ሰኞ ጥር 26፤ 2017 ተዘዋውሮ በተመለከተበት ወቅት ነው።
በመስክ ምልከታው የተገኙ አምስት የቋሚ ኮሚቴው አባላት፤ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን የስራ ኃላፊዎች፣ ሰራተኞችን እና ተገልጋዮችን ማነጋገራቸውን ከተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
በዚሁ ጊዜ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንን ያለፉትን የስድስት ወራት የስራ እንቅስቃሴ በተመለከተ፤ የመስሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ቢራቱ ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ገለጻ አድርገዋል።
አቶ ሳምሶን በዚሁ ገለጻቸው፤ ባለስልጣኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅን ለማሻሻል “እየሰራ” እንደሆነ መናገራቸውን የተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት በማህበራዊ የትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ ላይ አስፍሯል።
🔴 ለዝርዝሩ ▶️ https://ethiopiainsider.com/2025/14994/
@EthiopiaInsiderNews