ከዩ.ኤስ.ኤይድ ገንዘብ የሚያገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ንብረቶቻቸውን እንዳይሸጡ እና እንዳይስተላልፉ ክልከላ ተጣለባቸው
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን፤ ከአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ ድርጅቶች ያለ መስሪያ ቤቱ “ግልጽ ፍቃድ”፤ ንብረት የማስተላለፍ፣ የማስወገድ እና የመሸጥ ድርጊቶችን እንዳያከናውኑ ከለከለ። መስሪያ ቤቱ የሰጠውን “ጥብቅ ማሳሰቢያ” በመተላለፍ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ላይ “ተገቢውን እርምጃ” እንደሚወስድም አስጠንቅቋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ማሳሰቢያውን እና ማስጠንቀቂያውን ያስተላለፈው፤ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 27፤ 2017 ባወጣው “አስቸኳይ መግለጫ” ነው። መስሪያ ቤቱ መግለጫውን ያወጣው፤ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ስራቸውን ለሚከታተላቸው እና ለሚቆጣጠራቸው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሙሉ ነው።
ተቆጣጣሪ መስሪያ ቤቱ በዚሁ መግለጫው፤ ከሰሞኑ በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት በኩል “የእርዳታ ማቆም ውሳኔ” መተላለፉን መረዳት እንደቻለ ጠቅሷል። “ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ” እንደሚገኝ የገለጸው ባለስልጣኑ፤ “ዝርዝር ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ” በቀጣይ ባሉት ጊዜያት ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች “አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል” እንደሚያከናውን አስታውቋል።
እስከዚያው ጊዜ ድረስ ግን ከUSAID የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፤ ያላቸውን ንብረት “ማስተላለፍ”፣ “ማስወገድ” እና “መሸጥ” እንደማይችሉ ባለስልጣኑ ገልጿል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶቹ ከመደበኛ ወይም ፕሮጀክት ስራዎቻቸው ጋር ተያያዥ ከሆኑ ጉዳዮች ውጭ፤ ሃብት እና ገንዘባቸውን “በማናቸውም መልኩ” ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ የተከለከለ መሆኑንም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@EthiopiaInsiderNews
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን፤ ከአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ ድርጅቶች ያለ መስሪያ ቤቱ “ግልጽ ፍቃድ”፤ ንብረት የማስተላለፍ፣ የማስወገድ እና የመሸጥ ድርጊቶችን እንዳያከናውኑ ከለከለ። መስሪያ ቤቱ የሰጠውን “ጥብቅ ማሳሰቢያ” በመተላለፍ በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ላይ “ተገቢውን እርምጃ” እንደሚወስድም አስጠንቅቋል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ማሳሰቢያውን እና ማስጠንቀቂያውን ያስተላለፈው፤ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 27፤ 2017 ባወጣው “አስቸኳይ መግለጫ” ነው። መስሪያ ቤቱ መግለጫውን ያወጣው፤ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ስራቸውን ለሚከታተላቸው እና ለሚቆጣጠራቸው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በሙሉ ነው።
ተቆጣጣሪ መስሪያ ቤቱ በዚሁ መግለጫው፤ ከሰሞኑ በአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት በኩል “የእርዳታ ማቆም ውሳኔ” መተላለፉን መረዳት እንደቻለ ጠቅሷል። “ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ” እንደሚገኝ የገለጸው ባለስልጣኑ፤ “ዝርዝር ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ” በቀጣይ ባሉት ጊዜያት ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች “አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል” እንደሚያከናውን አስታውቋል።
እስከዚያው ጊዜ ድረስ ግን ከUSAID የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፤ ያላቸውን ንብረት “ማስተላለፍ”፣ “ማስወገድ” እና “መሸጥ” እንደማይችሉ ባለስልጣኑ ገልጿል። የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶቹ ከመደበኛ ወይም ፕሮጀክት ስራዎቻቸው ጋር ተያያዥ ከሆኑ ጉዳዮች ውጭ፤ ሃብት እና ገንዘባቸውን “በማናቸውም መልኩ” ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ የተከለከለ መሆኑንም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@EthiopiaInsiderNews