በአማራ ክልል ታስረው የነበሩ ሁሉም ዳኞች መለቀቃቸውን የክልሉ የዳኞች ማህበር አስታወቀ
በአማራ ክልል እስከ ትላንት ድረስ በእስር ላይ የነበሩ ዳኞች ሙሉ ለሙሉ መለቀቃቸውን የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር አስታወቀ። ካለፈው ሁለት ወር ወዲህ እስከ አርብ የካቲት 14፤ 2017 ድረስ ባሉት ጊዜያት ከእስር የተለቀቁት ዳኞች ብዛት 36 እንደሆነ የማህበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኑ አሰፋ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
በክልሉ ታስረው የነበሩ ሁሉም ዳኞች መፈታታቸው የተገለጸው፤ የአማራ ክልል ምክር ቤት የዳኞች ያለመከሰስ መብትን ያካተተ የህግ ማሻሻያ ካጸደቀ ከአስር ቀናት በኋላ ነው።
በአማራ በተለያየ እርከን በሚገኙ ፍርድ ቤቶች የሚሰሩ ዳኞች ለእስር ይዳረጉ የነበረው፤ በሚይዟቸው መዝገቦች ላይ በሚሰጧቸው ውሳኔዎች ምክንያት እንደሆነ አቶ ብርሃኑ ገልጸዋል።
“አብዛኞቹ ከስራ ጋር የተገናኘ ነው። ምክንያቱ ‘ዋስትና ጋር ተያይዞ ለምን ፈቀዳችሁ? ለምን ትዕዛዝ ሰጣችሁ? ለምን እግድ ሰጣችሁ?’ [የሚል ነው]። ያው በፍርድ ቤት ዳኞች በህግ የተሰጣቸውን ስልጣን መሰረት አድርገው ሲሰሩ፤ ከአስፈጻሚው ጋር የሚገናኙ አለመግባባቶች ጋር መነሻ በማድረግ የታሰሩ ናቸው” ሲሉ የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት የእስሮቹን መንስኤ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አብራርተዋል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15176/
@EthiopiaInsiderNews
በአማራ ክልል እስከ ትላንት ድረስ በእስር ላይ የነበሩ ዳኞች ሙሉ ለሙሉ መለቀቃቸውን የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር አስታወቀ። ካለፈው ሁለት ወር ወዲህ እስከ አርብ የካቲት 14፤ 2017 ድረስ ባሉት ጊዜያት ከእስር የተለቀቁት ዳኞች ብዛት 36 እንደሆነ የማህበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኑ አሰፋ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
በክልሉ ታስረው የነበሩ ሁሉም ዳኞች መፈታታቸው የተገለጸው፤ የአማራ ክልል ምክር ቤት የዳኞች ያለመከሰስ መብትን ያካተተ የህግ ማሻሻያ ካጸደቀ ከአስር ቀናት በኋላ ነው።
በአማራ በተለያየ እርከን በሚገኙ ፍርድ ቤቶች የሚሰሩ ዳኞች ለእስር ይዳረጉ የነበረው፤ በሚይዟቸው መዝገቦች ላይ በሚሰጧቸው ውሳኔዎች ምክንያት እንደሆነ አቶ ብርሃኑ ገልጸዋል።
“አብዛኞቹ ከስራ ጋር የተገናኘ ነው። ምክንያቱ ‘ዋስትና ጋር ተያይዞ ለምን ፈቀዳችሁ? ለምን ትዕዛዝ ሰጣችሁ? ለምን እግድ ሰጣችሁ?’ [የሚል ነው]። ያው በፍርድ ቤት ዳኞች በህግ የተሰጣቸውን ስልጣን መሰረት አድርገው ሲሰሩ፤ ከአስፈጻሚው ጋር የሚገናኙ አለመግባባቶች ጋር መነሻ በማድረግ የታሰሩ ናቸው” ሲሉ የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት የእስሮቹን መንስኤ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” አብራርተዋል።
🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15176/
@EthiopiaInsiderNews