TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
  • flag English
    Site language
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Sign In
  • Catalog
    Channels and groups catalog Search for channels
    Add a channel/group
  • Ratings
    Rating of channels Rating of groups Posts rating
    Ratings of brands and people
  • Analytics
  • Search by posts
  • Telegram monitoring
Ethiopia Insider

6 May, 21:51

Open in Telegram Share Report

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች በጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ተከሰሱ 

የኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ እህት ኩባንያው እና ሶስት የጣቢያው ሰራተኞች የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ወንጀል ክስ ቀረበባቸው። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረበው በዚህ የክስ መዝገብ ክስ፤ ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ፣ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን “ሀሰተኛ ታሪኳ ተሰራጭቷል” የተባለችው ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ ስድስት ተጠርጣሪዎች በሽብር ወንጀል ተከስሰዋል።

በአጠቃላይ 16 ተከሳሾች የተካተቱበትን የክስ መዝገብ፤ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የህገ መንግስት እና ሽብር ወንጀል ጉዳዮች ችሎት ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 28፤ 2017 ያቀረበው የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ነው። ከተከሳሾቹ መካከል ስምንቱ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቢሮ እና በወረዳ ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ናቸው። 

ዐቃቤ ህግ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው መዝገብ ሶስት የክስ አይነቶች ጠቅሷል። የመጀመሪያው ክስ፤ የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በ2011 ዓ.ም. የወጣን አዋጅ በመተላለፍ የቀረበ ነው። ዐቃቤ ህግ በክሱ የጠቀሰው የአዋጁ ድንጋጌ፤ “የሽብር ድርጊት” በመፈጸም “የሰው ህይወትን ለአደጋ ማጋለጥን” ይመለከታል። 

ይህ ድንጋጌ ተጠቅሶ ክስ ከቀረበባቸው ተጠርጣሪዎች ውስጥ በቀዳሚነት የተቀመጡት በአሁኑ ወቅት ነዋሪነታቸውን በውጭ ሃገር ያደረጉት ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ተስፋዬ ወልደስላሴ ናቸው። 

🔴 ለዝርዝሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15811/

@EthiopiaInsiderNews

6.5k 0 7 26
Catalog
Channels and groups catalog Channels compilations Search for channels Add a channel/group
Ratings
Rating of Telegram channels Rating of Telegram groups Posts rating Ratings of brands and people
API
API statistics Search API of posts API Callback
Our channels
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
Read
Blog Telegram Research 2019 Telegram Research 2021 Telegram Research 2023
Contacts
Справочный центр Support Email Jobs
Miscellaneous
Terms and conditions Privacy policy Public offer
Our bots
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot