TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
  • flag English
    Site language
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Sign In
  • Catalog
    Channels and groups catalog Search for channels
    Add a channel/group
  • Ratings
    Rating of channels Rating of groups Posts rating
    Ratings of brands and people
  • Analytics
  • Search by posts
  • Telegram monitoring
Ethiopia Insider

15 May, 19:16

Open in Telegram Share Report

የአማራ ክልል ዳኞች በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ በማንኛውም ማህበራዊ ሚዲያ ላይ “ሃሳብ እንዳይሰጡ” የሚከለክል ደንብ ወጣ   

በአማራ ክልል የሚገኙ ዳኞች፤ በፖለቲካ፣ በሃይማኖት ወይም “አወዛጋቢ በሆኑ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ “በየትኛውም” ማህበራዊ ሚዲያ “ሃሳብ እንዳይሰጡ” የሚከለክል ደንብ ጸደቀ። ደንቡ በክልሉ የሚገኙ ዳኞች “ሀሰተኛ ማህበራዊ ሚዲያዎችን “እንዳይጠቀሙ”፣ “እንዳይከተሉ” እና “አባል እንዳይሆኑ” ይከለክላል።

የዳኞች እና የጉባኤ ተሿሚዎችን የስነ-ምግባር እና የዲሲፕሊን የሚመለከተው ይህ ደንብ የጸደቀው ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ግንቦት 5፤ 2017 ነው። ደንቡን ያጸደቀው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኞች አስተዳደር አብይ ጉባኤ፤ ደንቡ ከዚሁ ዕለት ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ውሳኔ አስተላልፏል።

የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የዳኞች አስተዳደር ጉባኤን ለማሻሻል በ2014 የወጣው አዋጅ፤ ለዳኞች እና ለጉባኤ ተሿሚዎች የስነ ምግባር እና የዲሲፒሊን ደንብ የማውጣት ስልጣን የሰጠው በጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር ላለው አብይ ጉባኤ ነው። እስካሁን በስራ ላይ የቆየው የስነ ምግባር እና የዲሲፒሊን ደንብ የወጣው በ2007 ዓ.ም ነበር።

ይህ ደንብ “በርካታ ጉዳዮችን ያካተተ ቢሆንም ግልጽነት የጎደላቸው ጉዳዮችን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ” በአዲስ መልክ እንዲዘጋጅ መደረጉን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በትላንትናው ዕለት ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። አዲሱ ደንብ እንዲዘጋጅ ከተደረገባቸው ምክንያቶች አንዱ፤ በቀድሞው ደንብ ያልነበረ “የዳኞች ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን” ማካተት በማስፈለጉ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ ገልጿል።

🔴 ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15924/

@EthiopiaInsiderNews

4k 0 13 17
Catalog
Channels and groups catalog Channels compilations Search for channels Add a channel/group
Ratings
Rating of Telegram channels Rating of Telegram groups Posts rating Ratings of brands and people
API
API statistics Search API of posts API Callback
Our channels
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse @TGStatAPI
Read
Blog Telegram Research 2019 Telegram Research 2021 Telegram Research 2023
Contacts
Справочный центр Support Email Jobs
Miscellaneous
Terms and conditions Privacy policy Public offer
Our bots
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot @tg_analytics_bot @TGStatChatBot