ጥፋት እኮ
ሰም ቢፈልግ ኮርቶ በኔ በተጠራ
ነውር እኮ ቤት ቢኖረው ሰውነቴ የሱ ሥፍራ
ኃጢያት እኮ
አባት ቢሻ ደም አምጬ በወለድኩት
ክፋት እኮ መልክ ቢሆን ቁርጥ እሱን በመሰልኩት
በደል እኮ
ትግል ቢሻ እኔ እኮ ነኝ ጦር ጉልበቱ
ዝሙት እኮ ውበት ቢሆን መልኬ ነበር ምልክቱ
መራቆቴ
ምህረት አቅፎት በቸር ክንድህ ባመለጠ
እንኳን ልትፈርድ በሸሸከው በመረሳት ዋጋ ቀለህ
ደግ እኮ ነህ
ሁሉን ሸፋኝ ምን በገጼ ተገለጠ
እንደገና ለመከዳት ዛሬም በሬን ታንኳኳለህ🙏
@Ethiopian_Ortodoks