የግብዓት ዋጋ እስከ 400 በመቶ በመጨመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች እንዲጓተቱ ምክንያት ሆኗል ተባለ
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እንደገለፀው የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ እስከ 400 በመቶ መጨመሩ የመንገድ ግንባታው የሚፈለገውን ደረጃ ላይ እንዳይደርስ ምክንያት ሆኗል።
ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ እንደተናገሩት ይህንን ችግር ለመቅረፍ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በማቆም ነባሮችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ቃል የተገቡ ሁሉም የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይጠናቀቁ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።
የምክር ቤት አባላትም ከ1980 ጀምሮ በጥናት የተለዩ መንገዶች እንዳልተገነቡ፣ የተጀመሩት በጊዜያቸው አለመጠናቀቃቸውንና የተሰሩትም ሳይገለገሉ መበላሸታቸውን አንስተዋል። በተጨማሪም ለመንገድ ልማት የተነሱ ዜጎች ለዓመታት ካሳ ሳይከፈላቸው መቆየታቸውንም ካፒታል ሰምቷል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በበኩላቸው የመንገድ ግንባታ መጓተት የካሳ ክፍያና የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግር መሆኑን አምነዋል። ችግሩን ለመፍታትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እንደገለፀው የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ እስከ 400 በመቶ መጨመሩ የመንገድ ግንባታው የሚፈለገውን ደረጃ ላይ እንዳይደርስ ምክንያት ሆኗል።
ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ እንደተናገሩት ይህንን ችግር ለመቅረፍ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በማቆም ነባሮችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ቃል የተገቡ ሁሉም የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይጠናቀቁ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።
የምክር ቤት አባላትም ከ1980 ጀምሮ በጥናት የተለዩ መንገዶች እንዳልተገነቡ፣ የተጀመሩት በጊዜያቸው አለመጠናቀቃቸውንና የተሰሩትም ሳይገለገሉ መበላሸታቸውን አንስተዋል። በተጨማሪም ለመንገድ ልማት የተነሱ ዜጎች ለዓመታት ካሳ ሳይከፈላቸው መቆየታቸውንም ካፒታል ሰምቷል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በበኩላቸው የመንገድ ግንባታ መጓተት የካሳ ክፍያና የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግር መሆኑን አምነዋል። ችግሩን ለመፍታትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
Source: capitalethiopia
@Ethiopianbusinessdaily