ሙአዚኖች ሱብሕ ሶላት ላይ አትቸኩሉ። ወቅቱ መግባቱን ሳታረጋግጡ አዛን አታድርጉ። { وَكُلُوا۟ وَٱشۡرَبُوا۟ حَتَّىٰ یَتَبَیَّنَ لَكُمُ ٱلۡخَیۡطُ ٱلۡأَبۡیَضُ مِنَ ٱلۡخَیۡطِ ٱلۡأَسۡوَدِ مِنَ ٱلۡفَجۡرِۖ } ነው የሚለው። ቀደም ብሎ አዛን የሚደረግ ከሆነ ቤታቸው ውስጥ የሚሰግዱ ሰዎች፣ በተለይም ቶሎ ሰግደው መተኛት የሚፈልጉ አካላት ወቅት ሳይገባ ሊሰግዱ ይችላሉና ጥንቃቄ ያስፈልጋል። በተጨማሪም ወቅቱ ካልተጠበቀ ሰዎች ሰሑር በትክክል እንዳይመገቡ እንቅፋት ይሆናል። ሙአዚንነት አማና ነው። አማናችሁን በትክክል ተወጡ።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor