አዎ ነጃሺ ሰልሟል! ካልሆነ አንዱን ምረጡ
~
* ኢትዮጵያ በፍትሃዊ መሪዋ በነጃሺ አማካኝነት የነብዩ ሙሐመድን ﷺ ባልደረቦች ተቀብላ አስተናግዳለች። (አንድ ሐቅ)
* እነዚያን ተሳዳጅ ሙስሊሞች የተቀበላቸው ንጉስ ነጃሺ ሰልሟል። (ሌላ ሐቅ)
እነዚህን ሁለቱንም መረጃዎች ያስተላለፉት የነብዩ ሙሐመድ ﷺ ባልደረቦች ናቸው። እንጂ ይህንን ጉዳይ የሚገልፅ አንድም የኢትዮጵያ የታሪክ ምንጭ የለም። እደግመዋለሁ አንድም ምንጭ የለም። ቤተ ክርስቲያንም የላትም። የንጉሳኑ ዜና መዋእልም የሉም። ስለዚህ ጉዳይ ቀርቶ ስለዚያ ዘመን (7ኛው ክፍለ ዘመን) የኢትዮጵያ ታሪክ የሚያትት ተጨባጭና የተሰነደ የታሪክ መረጃ ራሱ ከናካቴው የለም።
ስለዚህ "ነጃሺ ሰልሟል" የሚለውን ሲናገሩ ካላመናችሁ "ኢትዮጵያ የነብዩ ሙሐመድን ﷺ ባልደረቦች ተቀብላ አስተናግዳለች" የሚለውን ከየት አምጥታችሁ ነው ያመናችሁት? "እንግዳ ተቀባይ ነን" ለማለት የመጀመሪያውን ሐቅ ትቀበላላችሁ። "በኢትዮጵያ ታሪክ ሙስሊም ነግሶ አያውቅም" ለማለት ሁለተኛውን ሐቅ ትጥላላችሁ። ከአንድ አካል ከተላለፉ ሁለት ዘገባዎች ውስጥ የጎረበጠንን መጣል፣ የጣፈጠንን መውሰድ አያስኬድም። ወይ ሁለቱንም እመኑ፤ ወይ ሁለቱንም ጣሉ። አንዱን ይዞ ሌላውን መጣል በራስ ህሊና ላይ መሸፈት ነው። ምናልባት ህሊና ካለ!
=
ኢብኑ ሙነወር
https://t.me/IbnuMunewor