Posts filter


Betty እባላለሁ እድሜ  23 ነው በጣም ቆንጆ  እና ለ kiss የሚገፋፋ ከንፈር አለኝ ስራዬ የ ሆቴል  አስተናጋጅ ነኝ
በምሰራበት ሆቴል በጣም ብዙ ደምበኞች ነበሩኝ  ቀኑን ባላስታውስም ወደ 2:30 አካባቢ ይሆናል ከደንበኞቼ አንዱ መኝታ ቤቱ ድረስ ቢራ እንዳመጣለት ይጠይቀኛል እኔም ቢራዉን ወሰድኩለት ክፍሉ ስገባ ግን ያልጠበኩት
see more....


ጎልልልልልልልልል ክርስትያኖኖኖኖኖ

ሮናልዶ በሳውዲ ሊግ ላይ ተገልብጦ ያስቆጠራትን ድንቅ ጎል ይመልከቱ 👇👇

https://t.me/addlist/fDJhM0jRWXAwOGVk


ከ17 ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ


የመንግሥትና የግል ሠራተኞች ከደመወዛቸው ለአደጋ ሥጋት ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ቀረበ‼️
👉ባንክና ኢንሹራንስን ጨምሮ በበርካታ 👉አገልግሎቶች ላይ ክፍያ ይፈጸማል።
የሚጠበቅባቸውን ክፍያ በወቅቱ ገቢየማያደርጉ ወለድና ቅጣት ይከፍላሉ።
የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ራሱን የቻለ የፌዴራል መንግሥት አስፈጻሚ አካል ሆኖ እንዲቋቋም በቀረበው ረቂቅ አዋጅ፣ የመንግሥትና የግል ድርጅት ተቀጣሪ ሠራተኞች ከሚከፈላቸው የተጣራ የወር ደመወዝ ላይ ክፍያ እንዲፈጽሙ የሚያስገድድ ድንጋጌ ተካተተ፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትናንት መጋቢት 9 ቀን 2017 ዓ.ም.  ባደረገው መደበኛ ስብሰባ የምክር ቤት አባላት በረቂቁ ላይ ለስምንት ደቂቃ ያህል ከተወያዩበት በኋላ፣ ለምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ ተመርቷል፡፡
በረቂቅ አዋጁ ማብራሪያ ላይ በቅድመ አደጋ፣ በአደጋና በድኅረ አደጋ ወቅቶች ለሚወሰዱ የአደጋ ሥጋት ቅነሳ፣ ምላሽና መልሶ ማቋቋም የሚሆን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ መቋቋሙ ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ፈጣን፣ አስተማማኝ፣ ተገማችና የአደጋ ሥጋት ምላሽ የፈንድ ሥርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ በአገር በቀል አቅም ዜጎች፣ ማኅበረሰብና ተቋማት እርስ በርስ በመደጋገፍ የአደጋ ሥጋትን የመከላከል፣ የማቅለል፣  የዝግጁነት፣ የምላሽ፣ የማገገምና በተሻለ ሁኔታ መልሶ ማቋቋም ላይ ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲያበረክቱ ለማስቻል ትልም የያዘ ስለመሆኑ ተብራርቷል፡፡
ፈንዱ ከሠራተኞች ደመወዝ ላይ ከሚቆረጥለት ገቢ በተጨማሪ ባንኮች፣ አነስተኛና ጥቃቅን የፋይናንስ ድርጅቶች ከሚሰጡት የብድር መጠን ላይ፣  የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ከሚከፍሉት የአገልግሎት ክፍያ፣ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ለሚሰጡት አገልግሎት ከሚሰበስቡት የፕሪሚየም (ዓረቦን) ክፍያና  ከማንኛውም የአክሲዮን ዲቪደንድ ድርሻ እንደሚሰበሰብ ተመላክቷል፡፡
በተጨማሪም ከበረራ ትኬት ሽያጭ፣ የቴሌኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ለድምፅና ለዳታ አገልግሎት ከሚያስከፍሉት የአየር ሰዓት ዋጋ፣   ከፓስፖርትና ከቪዛ አገልግሎት ክፍያ፣ የነዳጅ ሽያጭ አቅራቢ ድርጅት ከሚያገኘው ገቢ፣ ማንኛውም የንግድ ፈቃድ በሚወጣበትና በሚታደስበት ጊዜ በቁርጥ የሚታሰብ እንደሆነም በረቂቁ ተካቷል፡፡
#ሪፖርተር
====================
ትኩስ ያልተሰሙ ዜናዎችን ማግኘት ከፈለጉ ቻናላችንን join አድርጉ+ለሌሎች ጋብዙ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2


❗️ህ.ወ.ሓ.ት ከሻዓብያ ጋር እየሰራ ነው የሚለው ክስ ማስረጃ የማይቀርብበትና ሆን ተብሎ የቀረበ በመሆኑ አንቀበለውም ፤በእዚህ መንገድ የሚገኝ የጥቅም ማዕቀፍም የለንም ሲል ለአሻም ገለጸ፡፡

‹‹በክልሉ መፈንቅለ መንግስት ፈጽመዋል የሚለው የስም ማጥፋት ነው››ህ.ወ.ሓ.ት

በዛሬው ዕለት ረፋዱን ከአሻም ዜናናወቅታዊ ጉዳዮች ዝግጅት ክፍል ጋር በደብረጺዮን ገ/ሚካዔል (ዶ/ር) የሚመራው  የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ(ህ.ወ.ሓ.ት) ም/ሊቀመንበርና ቃል አቀባይ ኣማኑዔል አሰፋ ቃለ- ምልልስ አድርገዋል፡፡

ቃል-አቀባዩ ከአሻም በኩል ከተነሱላቸው 7ጥያቄዎች መካከል ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከሻዓብያ( እነሱ ጠላት) እያሉ ከሚጠሩት አካል ጋር እውን እየሰራችሁ ነው የሚለው ይገኝበታል፡፡ ለዚሁ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት አማኑዔል ‹‹ ከሻዓብያ ጋር ለመስራት ምንም አይነት ፍላጎትም ሆነ  በዚሁ መንገድ ሄዶ ጥቅሞቻችንን ለማስጠበቅ የሚያስችል ማዕቀፍ የለንም፣ ይህ ከንቱ ፍረጃ ነው ሲሉ ክሱን ውድቅ አድርገዋል፡፡

ከእዚህ ይልቅ የፕሪቶሪው ስምምነት አካል ከሆነው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነቱ ተፈጻሚ እንዲሆንና የትግራይ ህዝብ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ‹‹ሰላማዊ›› ባሉት መንገድ ከፌደራሉ መንግስት ጋር እየሰሩ መሆኑን አማኑዔል ተናግረዋል፡፡

አማኑዔል አስከትለውም ህ.ወ.ሓ.ት ከሻዓብያ ጋረ እየሰራ ነው የሚለው ክስ ሆነ ተብሎ የቀረበ ነው፤ ከእዚህ ውጭ ከማንም ጋር ግንኙነት የለንም ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ከተማ ላደረጉ መገናኛ ብዙሃን መግለጫ በሰጡበት ‹‹  እኔን እነሱ ጠላት እያሉ ከሚጠሩት ፌደራል መንግስቱ ጋር እየሰራህ ነው ሲሉ ይከሱኛል ፤ እነሱ ግን በጀርባ ‹‹ይኸው ጠላት የሚሉት‹‹ ፌደራል መንግስት›› ስልጣናቸውን እንዲመልስላቸው ሲማጸኑትና ሲለማመጡት ይውላሉ›› ሲሉ መክሰሳቸው የሚታወስ ነው፡፡

ሌላው አሻም በክልሉ መፈንቅለ መንግስት ፈጽማችኋል የሚል  በጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት የቀረበባችሁን ክስ  ትቀበላላችሁ ስትል የሰነዘረችላቸው ጥያቄ  ነው፡፡ ለዚሁ ምላሽ የሰጡት አማኑዔል በአጭሩ‹‹ ይህ የስም ማጥፋት ነው›› በማለት እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል፡፡


ዩኤስ አይ ዲ USAID

አንድ የአሜሪካ ፌደራል ፍርድ ቤት፣ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳድር የአሜሪካ ዓለማቀፍ ተራድዖ ድርጅትን (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲን) ወደነበረበት እንዲመልስ ትዕዛዝ መስጠቱን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል

ፍርድ ቤቱ፣ ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ በጥድፊያ እንዲፈርስ የተደረገበት መንገድ የአሜሪካ ሕገመንግሥቱን በብዙ መንገድ ጥሷል ሊባል የሚችል ነው ማለቱን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

ዩ ኤስ ኤ አይ ዲን የማፈረስ ወይም መልሶ የማዋቀር ሥልጣን የሕግ አውጭው ምክር ቤት ብቻ ሥልጣን እንደኾነ ፍርድ ቤቱ ጠቅሷል ተብሏል።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ ከድርጅቱ 83 በመቶ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ እንደታጠፉና ቀሪዎቹ በውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ሥር መጠቃለላቸውን ከሳምንት በፊት መግለጣቸው አይዘነጋም።


መጣል የጀመረው ዝናብ ለበልግ አብቃይ አካባቢዎች ጠቃሚ ነው ተባለ

በአሁኑ ወቅት እየጣለ ያለው ዝናብ ለበልግ አብቃይ አካባቢዎች ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ፈጠነ ተሾመ ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር በነበራቸው ቆይታ÷ኢትዮጵያ ከክረምት ቀጥሎ ከፍተኛ ዝናብ የምታገኘው በበልግ ወቅት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሀገሪቱ ደቡባዊ አጋማሽ፣ ሰሜን እና ምዕራብ አካባቢዎች የበልግ ወቅት ዝናብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ነው ያስረዱት፡፡

የአሁኑ ዝናብ ለበልግ አብቃይ አካባቢዎች ከፍተኛ ጥቅም እንደሚሰጥ ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ÷ በተለይም በእንሰሳት እርባታ ለሚተዳደሩ አካባቢዎች ለመኖ አቅርቦት መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል ብለዋል።

ቅጽበታዊ ጎርፍ በሚያጋጥማቸው አካባቢዎች ኢንስቲትዩቱ ለአርሶ አደሩ መረጃ በመስጠት ሰፊ ሥራ ሲያከናውን መቆየቱን አንስተዋል።

በከተማም የጎርፍ ማፋሰሻ ቦዮችን የማጽዳት እና ሌሎች ለጎርፍ ተጋላጭ የሚያደርጉ ሁኔታዎችን የመከላከል ሥራ መሰራቱን ነው የገለጹት፡፡

ኤፍኤምሲ

@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH


ቱርክ የፕሬዝደንት ኢርዶጋንን ዋና ተቀናቃኝ አሰረች።

የቱርክ ባለስልጣናት የፕሬዝደንት ኢርዶጋን ዋና ተቀናቃኝ የሆኑትን በሙስናና እና የሽብር ቡድንን በመርዳት በመክሰስ ዋና ተቃዋሚው አስራለች።

የሪፐብሊካን ፕፕልስ ፓርቲ(ሲኤችፒ) አባል የሆኑት የኢስታንቡል ከንቲባ ኢክረም ኢማሞግሉ የሽብር ድርጅትን በመምራት፣ በጉቦና ጨረታ በማጭበርበር ክሶች ሁለት የተለያዩ ምርመራዎች ተከፍተውባቸዋል።

የኢማሞግሉ ፓርቲ ቱርክን ከሁለት አስርት አመታት በላይ የመሩት ፕሬዝደንት ኢርዶጋን ተፎካካሪ አድርጎ ሊሰይማቸው ጥቂት ቀናት ነበር የቀሩት።

ለሁለት የስልጣን ዘመን የኢስታንቡል ከንታባ የሆኑት ኢማሞግሉ ወደፊት በሚደረግ ምርጫ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ኢማሞግሉ በኤክስ ገጻቸው ላይ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልእክት ተስፋ እንደማይቆርጡና ለሚደረግባቸው ጫና ሸብረክ እንደማይሉ ተጽፈዋል።

የኢስታንቡል የአቃቤ ህግ ቢሮ የመጀመሪያ ምርመራውን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ፤ ጋዜጠኞችና ነጋዴዎችን ጨምሮ 100 ሰዎች ማዘጋጃ ቤት ከሰጠው ጨረታ ጋር በተያያዘ የወንጀል ተግባር ተሳትፈዋል የሚል ጥርጣሬ እንዳለው ጠቅሷል።

ቢሮው በሁለተኛ ምርመራው ኢማሞግሉ በቱርክና በምዕራባውያን አጋሮቿ በሽብር የተፈረጀውን የኩርድ ሰራተኞች ፓርቲን (ፒኬኬ) ይረዳሉ የሚል ክስ አቅርቦባቸዋል።


የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል ያዘጋጀው ፎረሙ÷“የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና እድሎች” በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

በፎረሙ ላይ የህብረቱ አባል ሀገራት፣ የማዕድን ዘርፍ ተዋንያን፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።

ፎረሙ እስከ መጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን÷ በአፍሪካ ማዕድን ዘርፍ ያሉ እድሎች፣ ፈተናዎች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ምክክር እንደሚደረግ ተጠቁሟል፡፡


ኢትዮጵያ ከዱር እንስሳት ሀብት የምታገኘው አመታዊ ገቢ ከ150 ሚሊዮን ብር አይበልጥም

ኢትዮጵያ ከዱር እንስሳት ሀብት እያገኘች ያለችው ዓመታዊ ገቢ ከ150 ሚሊዮን ብር የዘለለ እንዳልሆነ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል።

ኢትዮጵያ ከአላት የዱር እንስሳት ሀብት የመታገኘው ገቢ እጅግ ዝቅተኛ ነው፤ በዓመት እየተገኘ ያለው ገቢ ከ150 ሚሊዮን ብር የዘለለ ዓይደለም ሲሉ የባለስልጣኑ ዳይሬክተር ኩማራ ዋቅጅራ ገልጸዋል።

“ሌሎች ሀገራት ከዱር እንስሳት የሚያገኙት ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ኢኮኖሚያቸውን ይደግፋል” ያሉት ኃላፊው፤ በአንፃሩ ኢትዮጵያ ከዱር እንስሳት የምታገኘው ገቢ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋፅዖ አነስተኛ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ፖርኮች በሚፈለገው መጠን እየለሙ አለመሆናቸው እና ሀብቱን ለመጠበቅ የሚበጀተው በጀት አነስተኛ መሆኑ ሀገሪቱ ከዱር እንስሳት የምታገኘው ገቢ ዝቅተኛ እንዲሆን አድርጎታል ሲሉም ተናግረዋል፡፡

መንግስት ዘርፉ ትልቅ የኢኮኖሚ ምንጭ እንደሚሆን አምኖበት እና ከዱር እንስሳት ሀብት የሚገኘውን ዝቅተኛ ገቢ ለማሳደግ በፓርኮች አካባቢ የቱሪዝም መዳረሻዎች የማልማት ስራ እየሰራ ነው ሲሉ መግለጻቸውነ ከፕሬስ ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።


በምሽት የንግድ እና የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ የወጣውን ደንብ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል

የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ በምሽት የንግድ እና የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ የወጣውን ደንብ ቁጥር185/2017 ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል።

ቢሮው የአዲስ አበባ ከተማ አሁን ከደረሰችበት ኢኮኖሚያዊና ማህበረሰባዊ ለውጥ አንፃር የአብዛኛው ማህበረሰብ የሥራ ባህል እና ፍላጎት በመለወጡ የንግድ ሥራዎችንና አገልግሎቶችን በምሽት መከወን እየተለመደ የመጣውን ተግባር ወጥነትና ቀጣይነቱን ማረጋገጥ ማስፈለጉን አስታውቃል

ለዚህም ደንቡ በመውጣቱን ይህ ደንብ ቀደም ብሎ የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ያስተላለፈውን ውሳኔ ለማስፈጸም በመሆኑ ከዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ሐቢባ ሲራጅ አብራርተዋል፡፡

በመሆኑም በከተማዋ በስፋት እየተከናወነ የሚገኘው መሠረተ-ልማት በኢኮኖሚው ላይ የፈጠረውን መነቃቃት አጠናክሮ ለማስቀጠል፣ የስራ ባህልን ይበልጥ ለማዳበር ፣ የኢኮኖሚ እድገትን ለማፋጠን፣ የከተማዋን ተወዳዳሪነት እውን ለማድረግ ቀን ከሚሰጠው አገልግሎት በተጨማሪ በምሽት የንግድ እና አገልግሎት መስጫ ተቋማት አገልግሎት የሚሰጡበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል፡፡

በደንቡ የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ማብራሪያ በሁሉም የሚዲያ አውታሮች አማካኝነት ማህበረሰቡ እንዲያውቃቸው እንደሚደረግ እና ደንቡን የማስተዋወቅ ስራ እንደሚሰራም መግለፃቸውን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።


ኢትዮጵያ ጊዜው ያለፈበት የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ ኤርትራን እያስገረመ ነው - ኦስማን ሳለህ

ኢትዮጵያ የተሳሳተና ጊዜው ያለፈበት በኃይል ወይም በዲፕሎማሲዊ መንገድ የባሕር ኃይል የማቋቋም ወይም የባሕር በር የማግኘት ጉዳይ ኤርትራን እያስገረማት እንደሆነ የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ኦስማን ሳለህ ገለፁ፡፡

ሚንስትሩ ባልተለመደ መልኩ በሃገሪቱ ለሚገኙ ዲፕሎማቶች እና አማባሳደሮች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ኦስማን ሳልህ፤ ኢትዮጵያ የጎረቤቶቿን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት እንድታከብር ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ ግፊት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

“የኤርትራ ጦር ኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛል የሚሉ አካላት ለኢትዮጵያ ውስጣዊ ችግር ኤርትራን ተጠያቂ ማድረግ የሚፈልጉ ናቸው” በማለትም ኦስማን ከሰዋል።

ኦስማን በሕወሓትና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል ባለው ሽኩቻ ውስጥ ኤርትራ ሚና አላት የሚለውን ውንጀላም አስተባብለዋል።


እስራኤል ወደ ሙሉ ውጊያ ገብታለች - ቤንያሚን ኔታንያሁ

ከ400 በላይ ፍልስጤማውያን መገደላቸው ሪፖርት የተደረገበትን የጋዛ ጥቃት ገና የመጀመሪያው እንደሆነ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ተናግረዋል።

እስራኤል በጋዛ ሰርጥ በሐማስ ላይ "ውጊያዋን በሙሉ ኃይል ጀምራለች" ሲሉ ኔታንያሁ አስጠንቅቀዋል፡፡

ጥር ወር ላይ ከተደረሰው የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት በኋላ እስራኤል የፈጸመችው ከባዱ የአየር ጥቃት ነው ተብሏል።

ጥቃቱ በተፈጸመበት ወቅት በርካቶች ለረመዳን ጾም የቀኑን የመጨረሻ ምግባቸውን እየበሉ እንደነበር የዓይን እማኞች ተናግረዋል።

በቦታው አስከሬኖች ወዳድቀው፣ የቆሰሉ ሰዎች ህክምና ለማግኘት እየተማጸኑ እንዲሁም እሳት ተቀጣጥሎ የነበረ ሲሆን፤ ሁኔታውንም አሰቃቂ ብለውታል።

ኔታንያሁ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት "ድርድሩ የሚቀጥለው በእሳት ውስጥ ብቻ ነው፤ ይህም ገና ጅምር ነው" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተያየት የተሰማው የእስራኤል ጦር በጋዛ የሃማስ ይዞታዎች ናቸው በሚል ከፍተኛ የአየር ጥቃት ከከፈተ በኋላ ነው።

የተኩስ አቁሙ አሸማጋይ የሆነችው ግብጽ ይህንን የእስራኤል ጥቃት በጽኑ አውግዛለች።

@Addisinsider_ETH
@Addisinsider_ETH


እስራኤል በጋዛ ሰርጥ በሐማስ ላይ "ውጊያዋን በሙሉ ኃይል ጀምራለች" አሉ  ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ

ከ400 በላይ ፍልስጤማውያን መገደላቸው ሪፖርት የተደረገበትን የጋዛ ጥቃት ገና የመጀመሪያው እንደሆነ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ተናገሩ።

እስራኤል በጋዛ ሰርጥ በሐማስ ላይ "ውጊያዋን በሙሉ ኃይል ጀምራለች" ሲሉ ኔታንያሁ አስጠንቅቀዋል፡፡

ጥር ወር ላይ ከተደረሰው የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት በኋላ እስራኤል የፈጸመችው ከባዱ የአየር ጥቃት ነው ተብሏል።

ጥቃቱ በተፈጸመበት ወቅት በርካቶች ለረመዳን ጾም የቀኑን የመጨረሻ ምግባቸውን እየበሉ እንደነበር የዓይን እማኞች ተናግረዋል።

በቦታው አስከሬኖች ወዳድቀው፣ የቆሰሉ ሰዎች ህክምና ለማግኘት እየተማጸኑ እንዲሁም እሳት ተቀጣጥሎ የነበረ ሲሆን፤ ሁኔታውንም አሰቃቂ ብለውታል።

ኔታንያሁ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት "ድርድሩ የሚቀጥለው በእሳት ውስጥ ብቻ ነው፤ ይህም ገና ጅምር ነው" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተያየት የተሰማው የእስራኤል ጦር በጋዛ የሃማስ ይዞታዎች ናቸው በሚል ከፍተኛ የአየር ጥቃት ከከፈተ በኋላ ነው።

የጋዛ የጤና ሚኒስቴር በዚህ ጥቃት ከ400 በላይ ሰዎች መገደላቸውን እንዲሁም በመቶዎች የሚቆጠሩ መቁሰላቸውን አስታውቋል።

የተኩስ አቁሙ አሸማጋይ የሆነችው ግብጽ ይህንን የእስራኤል ጥቃት በጽኑ አውግዛለች።


❗️"የትጥቅ መጠን አለመግባባት ነው..." ታደሰ ወረደ

በትግራይ ትጥቅ መፍታት እና የወቅቱ የደህንነት ስጋት
በትግራይ ተቋርጦ የነበረው የቀድሞ ተዋጊዎች ወደ ሰላማዊ ሕይወት የመመለስ ስራ ዳግም ለማስቀጠል መግባባት መደረሱ ተገለፀ።

የትግራይ ሐይሎች አዛዥ ጀነራል ታደሰ ወረደ ሂደቱ ተቋርጦ የነበረው በነበረ ሊፈታ የሚጠበቅ የትጥቅ መጠን አለመግባባት ነው ብለዋል።


በሻሸመኔ ከተማ በድብቅ ሊጓጓዝ የተዘጋጀ 22 ኩንታል ካናቢስ በቁጥጥር ስር ዋለ

በሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር አላቼ ክፍለከተማ ዉስ በድብቅ ሊጓጓዝ የተዘጋጀ 22 ኩንታል አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታዉቋል።

መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የሰሌዳ ቁጥጥር ኮድ 3A38486 አ.አ የሆነ አይሱዚ ተሽከርካሪ ከሻሸመኔ ከተማ 22 ኩንታል ካናቢስ የተሰኘ አደንዛዥ እፅ በድብቅ ጭኖ ወደ ቦረና ሞያሌ ከተማ ሲጓዝ ከህብረተሰቡ በተገኘ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉን የሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አላቼ ክፍለከተማ መግለጫ ያሳያል።

ተሽከርካሪዉ በቁጥጥር ስር የዋለዉ በሻሸመኔ ከተማ አስተዳደር አላቼ ክፍለከተማ ዲዳ ቦኬ የተባለ አከባቢ መሆኑ ተገልጿል ።

እፁን ሲያጓጉዝ የነበረዉ አሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ዉሎ ምርመራ እየተደረገበት ሲሆን የምርመራ መዝገቡም እንደተጠናቀቀ ለሚመለከተዉ የፍትህ አካል እንደሚላክ ብስራት ሬዲዮ ከአላቼ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል ።


አቃቢ ህግ በእነ ዮሀንስ ቧያለው መዝገብ ስር በተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ላይ ምስክሮችን ማሰማት ጀመረ::

አቃቢ ህግ ተከሳሾቹ ባስተላለፉት ትዕዛዝ ምክንያት የደረሱ ጉዳቶችን ያስረዱልኛል ያላቸውን ምስክሮች አቅርቧል
አቃቢ ህግ በእነ ዮሀንስ ቧያለው መዝገብ ስር በተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ላይ ምስክሮችን ማሰማት ጀመረ።
የፍትህ ሚኒስቴር በእነ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ ባሉ 52 ተጠርጣሪዎች ላይ የፖለቲካ ርዕዮትን በሀይል ለማስፈጸም ተንቀሳቅሰዋል፣ በ1996 ዓም የወጣውን የወንጀል ህግ እንዲሁም የሽብር ወንጀሎችን ለመከላከል የወጣውን ህግ ጥሰዋል በሚል ከአንድ ዓመት በፊት ክስ መመስረቱ ይታወሳል፡፡
በዚህ ክስ መዝገብ ስርም የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን ወክለው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ እንዲሁም የአማራ ብልጽግና ፓርቲን ወክለው የክልሉ ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ዮሀንስ ቧያለው እንዲሁም የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባሉ ካሳ ተሸገር (ዶ/ር) ጫኔ ከበደ፣ እስክንድር ነጋ፣ ዘመነ ካሴ፣ አበበ ፈንታው፣ አሰግድ መኮንን፣ መከታው ማሞ፣ ፈንታሁን ሙሃባ እና ሌሎችም ተካተዋል፡፡
ከ52ቱ ተከሳሾች መካከል 16ቱ ተከሳሾች አዲስ አበባ ልደታ በሚገኘው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስት እና ሽብር ወንጀሎች ችሎት የቀረቡ ሲሆን የአቃቢ ህግ ምስክሮች በተከሳሾች ላይ የምስክርነት ቃላቸውን እንደሰጡ የተከሳሾች ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአል ዐይን ተናግረዋል፡፡
ጠበቃ ሰለሞን እንዳሉት በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛና 2ተኛ ህገ-መንግስታዊ እና ፀረ -ሽብር ችሎት አቃቤ ህግ በእነ ዮሐንስ ቧያለው የክስ መዝገብ በሚገኙ ተጠርጣሪዎች ላይ ያቀረባቸውን ምስክሮች ፍርድ ቤቱ መስማት ጀምሯል፡፡

Via -አል ዓይን

@Addis_Reporter


በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተከሰተ የእንስሳት ወረርሽኝ በአንድ ወረዳ ብቻ ከ230 በላይ እንስሳት መሞታቸው ተገለጸ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ኡባ ደብረጸሐይ እና ዛላሕ ወረዳዎች እንዲሁም በሻውላ ከተማ አስተዳደር ከመጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ በተከሰተ የእንስሳት ወረርሽኝ በርካታ ቁጥር ያላቸው እንስሳት መመታቸው ተገጿል።

የበኡባ ደብረጸሐይ ወረዳ ብቻ ባለፉት አራት ቀናት ከ238 የሚሆኑ እንስሳት መሞታቸውን አርብቶ አደሮች እና የእንስሳት ጤና ባለሙያዎች ለአዲስ ስታንዳርድ አስታውቀዋል።

የኡባ ደብረጸሐይ ወረዳ የግብርና ጽሕፈት ቤት ሐላፊ የሆኑት አቶ አይሬ ሞርጫ ስለመንሰኤው እስከአሁን የተረጋገጠ ነገር ባይኖርም "አየሩ ጸሐያማ ሆኖ ነው የከረመው ከዛ ግን ከሰሞኑ የተወሰነ ዝናብ መጣል ጀምሮ ነበረ" ሲሉ የወረርሽኙም መነሻ ከዚሁ የአየር መቀየር ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ጠቁመዋል።


በአዲስ አበባ የቡና ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨመረ።

ለቡና ዋጋ መጨመር የግብይት ሰንሰለቶች ጤናማ አለመሆን በምክንያትነት ተቀምጧል፡፡

ባለፈው አንድ ወር ውስጥ በምርት ገበያ የቡና ዋጋ በዕጥፍ መጨመሩን ኢትዮ ኤፍ ኤም ዘግቧል፡፡

ጣቢያችን በተለያዩ የገበያ ቦታዎች ተዘዋውሮ ባደረገው ምልከታ ከወራት በፊት አንድ ኪሎ ቡና ከ600 ብር ጀምሮ ይሸጥ የነበረ ሲሆን ከሰሞኑ አንድ ኪሎ ቡና ከ800 እስከ 900 ብር እና ከዛ በላይ እየተሸጠ እንደሚገኝ ጣቢያው በቅኝት ማረጋገጡ ገልጿል፡፡

ወደ ገበያ የሚቀርበው የቡና መሸጫ ዋጋው እንደየ ጥራቱ ቢለያይም ከዝቅተኛው ጀምሮ እስከ ከፍተኛው የጥራት መጠን ያለው ቡና በአማካይ እስከ 200 ብር የዋጋ ጭማሪ መኖሩምን ከሸማቾች እና ነጋዴዎች ሰምተናል ብሏል የዜና ምንጩ፡፡

በጉዳዩ ላይ ሀሳብ እንዲሰጡበት የጠየቅናቸው በኦሮሚያ ቡና ገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ዳዲ ለኢትዮጵያ ምርት ገበያ የተቆላ ቡናን እስከ 800 ብር እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል።

ዋና ስራ አሰኪያጁ በገበያው ላይ ምርት እንዲጠፋ የሚያደርጉ የተለያዩ የግብይት ሰንሰለቶች ጤናማ አለመሆን ለመጨመሩ አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት መሆኑንም ያነሳሉ፡፡

ኢትዮጵያ በቡና ምርት ከአፍረካ በአንደኛነት፣ ከዓለም ደግሞ ብራዚል፣ ቬትናም፣ ኮሎምብያ እና ኢንዶኔዢያን ተከትላ 5ኛ ደረጃ እንደተቀመጠች መረጃዎች ያሳያሉ፡፡


የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር 413 ደረሰ

እስራኤል በጋዛ በፈጸመችው የአየር ድብደባ የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር ከ400 መሻገሩ ተገለጸ።

የፍልስጤም ጤና ሚኒስቴር በዋትስአፕ ገጹ ባጋራው መረጃ የሟቾቹ ቁጥር 413 መድረሱን ጠቁሟል።

ከሁለት ወራቱ የተኩስ አቁም ስምምነት በኋላ የተፈጸመው መጠነሰፊ የአየር ጥቃት ከ560 በላይ ሰዎችን ማቁሰሉንና በርካታ ሰዎችም አሁንም ድረስ በፍርስራሽ ውስጥ እንደሚገኙም ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ሃማስ ባወጣው መግለጫ "ኔታንያሁ እና ጽንፈኛ መንግስቱ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለመጣስ መወሰኑ በጋዛ የሚገኙ ታጋቾችን እጣፈንታ ጥያቄ ውስጥ ከቷል" ብሏል።

የቡድኑ የፖለቲካ ቢሮ አባል ኢዛት አል ሪሽቅም የእስራኤል የቦምብ ድብደባ በታጋቾች ላይ "የሞት ፍርድ" እንደማሳለፍ ይቆጠራል ማለታቸውን ሬውተርስ ዘግቧል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጽህፈት ቤት ግን ሃማስ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለማራዘምና ታጋቾችን ለመልቀቅ ፈቃደኛ ባለመሆኑ የእስራኤል ጦር የተጠናከረ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ መታዘዙን ነው ያመላከተው።

20 last posts shown.