ሰዎች ፈረዱብኝ | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ሰዎች ፈረዱብኝ
አንተ ግን አዳንከኝ /2/
አምላኬ ሆይ ተመስገንልኝ
ጌታዬ ሆይ ተመስገንልኝ
ሌላ ምን ቃል አለኝ
ሊያልፉኝ አልወደዱም ነውሬን ሊሰውሩ
ሰዎች ፈጠኑብኝ በደሌን ሊያወሩ
አንተ ግን ሰብስበህ በፍቅር ሸፈንከኝ
በመተላለፌ አዝነህ ሳትለየኝ
ይህ ፍቅርህ ሰበረኝ አጣበቀኝ ካንተ
ደጅህ ያመጣኛል ሁሌ እየጎተተ /2/
መርከሴን አውጀው ሲያነሱብኝ ድንጋይ
ሰወረኝ ተዓምርህ ልጅ ሳልሰቃይ
ወደህ ስለማርከኝ ክፉዎች ተከዙ
ይህ አይደለም ብለው የኃጢአት ደሞዙ
ካነተ በላይ ጌታ ማን ሊያውቀኝ ይችላል
የፍቅርህን ሚዛን ማንስ ያዛባዋል /2/
ማዳንህ ይደንቃል ለወደኩት ልጅህ
ምህረትህ ይደፋል ሁሌ በሚዛንህ
እንደሰው አይታይ ፍርድህም ይለያል
ለባርያህ አርነት በምህረት ፈርደሃል
ፍቅር እየዘረዘርክ መንገዴን የጠረክ
ስለልጅህ ጽድቅን ለድህነት የፈረድክ /2/
እኔ አልፈርድብህም በሰላም ሂድ አልከኝ
ዳግም እንዳልበድል በፍቅር እያየኸኝ
ወደፅድቅህ ህጎች ነፍሴን አፈሳለሁ
እንዲህ ከወደድከኝ ወዴት እሄዳለሁ
አልለይም ካንተ ከፍቅር መድረኬ
አመልካለሁ አንተን ፊትህ ተንበርክኬ /2/
@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All
ሰዎች ፈረዱብኝ
አንተ ግን አዳንከኝ /2/
አምላኬ ሆይ ተመስገንልኝ
ጌታዬ ሆይ ተመስገንልኝ
ሌላ ምን ቃል አለኝ
አዝ
ሊያልፉኝ አልወደዱም ነውሬን ሊሰውሩ
ሰዎች ፈጠኑብኝ በደሌን ሊያወሩ
አንተ ግን ሰብስበህ በፍቅር ሸፈንከኝ
በመተላለፌ አዝነህ ሳትለየኝ
ይህ ፍቅርህ ሰበረኝ አጣበቀኝ ካንተ
ደጅህ ያመጣኛል ሁሌ እየጎተተ /2/
አዝ
መርከሴን አውጀው ሲያነሱብኝ ድንጋይ
ሰወረኝ ተዓምርህ ልጅ ሳልሰቃይ
ወደህ ስለማርከኝ ክፉዎች ተከዙ
ይህ አይደለም ብለው የኃጢአት ደሞዙ
ካነተ በላይ ጌታ ማን ሊያውቀኝ ይችላል
የፍቅርህን ሚዛን ማንስ ያዛባዋል /2/
አዝ
ማዳንህ ይደንቃል ለወደኩት ልጅህ
ምህረትህ ይደፋል ሁሌ በሚዛንህ
እንደሰው አይታይ ፍርድህም ይለያል
ለባርያህ አርነት በምህረት ፈርደሃል
ፍቅር እየዘረዘርክ መንገዴን የጠረክ
ስለልጅህ ጽድቅን ለድህነት የፈረድክ /2/
አዝ
እኔ አልፈርድብህም በሰላም ሂድ አልከኝ
ዳግም እንዳልበድል በፍቅር እያየኸኝ
ወደፅድቅህ ህጎች ነፍሴን አፈሳለሁ
እንዲህ ከወደድከኝ ወዴት እሄዳለሁ
አልለይም ካንተ ከፍቅር መድረኬ
አመልካለሁ አንተን ፊትህ ተንበርክኬ /2/
@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All