"እውነት ምንድን ነው?"
ጲላጦስ
አንዳንዶች ፍልስፍና በዘመናችን እምብዛም የሚወደድ ሆኖ አለመገኘት ብቻ ሳይሆን እየተጠላም ነው ይላሉ፡፡
ሶቅራጥስ ራሱን አሳልፎ የሰጠላት፣ ፕሌቶም ፍልስፍናን ከማጣት ይልቅ ሞት ይሻላል በማለት ሁለት ጊዜ መስዋዕት ሆኖ የቀረበላት፧ ጳጳሳት ተከታዮችዋን ያሰሩባት፣ ያሰቃዩባት... ይህች «ፍልስፍና» «ለመሆኑ ምን ብታነሳ ነው ይህ ሁሉ የመጣባት?» ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው፡፡
ተከታዮቿ የፍልስፍና ትልቁና የመጀመሪያ ጥያቄዋ «እውነት» ስለሆነ ነው፤ ይላሉ፡፡ «እውነት ምንድነው?» የሚለው ጥያቄ ፍልስፍና የተጣለችበት መሠረት ነው:: "በእርግጥ የምናየውን ነገር የምናየው፤ የምንሰማውን ነገር የምንስማው ፤ የምናሸተውን ነገር የምናሸተው ፤ የምንነካውን ነገር የምንነካው ወዘተ እውነት ስለሆነ ነው? ወይስ እውነት ነው ብለን ስለምናስብ?" በማለት ፈላስፎቹ ይጠይቃሉ፡፡
ይኸ ዓለም፡- «ለእያንዳንዱ ሰው እምነቱ የእሱ እውነት ነው» ይለናል፡፡ «እምነትህ እውነት ነው›› በሚለው በዚህ ዓለም ውስጥ ፈላስፎቹ ደግሞ «ማስረጃ ማቅረብ የማትችልበት እምነት እውነት ሊሆን አይችልም» ይላሉ።
ታላቁ ፈላስፋ ፍሬዴሪክ ኒቼ ፦«የምታምነው ለመኖሩ ማስረጃ ማቅረብ ካልቻልክ እምነትህ ውሸት ነው፤ አባቴ ለእኔ ያስተላለፈው እምነት አያቴ የነገረውን ነው ፤ አያቴም የቅድም አያቴን ይዞ ለአባቴ አስተላለፈው፤ እንግዲህ እኔ የምኖርበት እምነት አስቀድሞ ሌሎች የኖሩበትን እንጂ እኔ በማስረጃ አረጋግጬ ያገኘሁት አይደለም ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ለእምነትህ ማስረጃ የለህምና ውሸት ነው›› ይላል፡፡ ሌሎችም ፈላስፎች በዚህ ይስማማሉ፡፡
እንግዲህ ወደ «እውነት» ጥያቄ ስንመጣ ኒቼ ሊነሳ የሚገባው ፈላስፋ ይሆናል፡፡ እንደኒቼ እምነት
«እውነት በተገቢ ሁኔታ የተነሳችበት የተጠየቀችበት በአንድ ሰውና በእንድ ቦታ ብቻ ነው፤ ይኸውም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እሱም በጲላጦስ ነው» ይላል፡፡ አናቶሊ ፍራንስም በዚህ አባባል «እስማማለሁ ብቻ ሳይሆን አምንበታለሁም» ይላል።
«ጲላጦስም፡- እንግዲህ ንጉሥ ነህን? አለው::
ኢየሱስም መልሶ፡-" እኔ ንጉሥ እንደሆንሁ አንተ ትላለህ እኔ ለእውነት ልመሰክር ተወልጃለሁ፤ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ድምፄን ይሰማል አለው፡፡"
ጲላጦስም፦ "እውነት ምንድር ነው? አለው"
ዮሐ 17:38
እነሆ እኛም እንደ ጲላጦስ እውነት ምንድን ነው? ብለን እንጠይቃችኋለን
@zephilosophy
ጲላጦስ
አንዳንዶች ፍልስፍና በዘመናችን እምብዛም የሚወደድ ሆኖ አለመገኘት ብቻ ሳይሆን እየተጠላም ነው ይላሉ፡፡
ሶቅራጥስ ራሱን አሳልፎ የሰጠላት፣ ፕሌቶም ፍልስፍናን ከማጣት ይልቅ ሞት ይሻላል በማለት ሁለት ጊዜ መስዋዕት ሆኖ የቀረበላት፧ ጳጳሳት ተከታዮችዋን ያሰሩባት፣ ያሰቃዩባት... ይህች «ፍልስፍና» «ለመሆኑ ምን ብታነሳ ነው ይህ ሁሉ የመጣባት?» ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው፡፡
ተከታዮቿ የፍልስፍና ትልቁና የመጀመሪያ ጥያቄዋ «እውነት» ስለሆነ ነው፤ ይላሉ፡፡ «እውነት ምንድነው?» የሚለው ጥያቄ ፍልስፍና የተጣለችበት መሠረት ነው:: "በእርግጥ የምናየውን ነገር የምናየው፤ የምንሰማውን ነገር የምንስማው ፤ የምናሸተውን ነገር የምናሸተው ፤ የምንነካውን ነገር የምንነካው ወዘተ እውነት ስለሆነ ነው? ወይስ እውነት ነው ብለን ስለምናስብ?" በማለት ፈላስፎቹ ይጠይቃሉ፡፡
ይኸ ዓለም፡- «ለእያንዳንዱ ሰው እምነቱ የእሱ እውነት ነው» ይለናል፡፡ «እምነትህ እውነት ነው›› በሚለው በዚህ ዓለም ውስጥ ፈላስፎቹ ደግሞ «ማስረጃ ማቅረብ የማትችልበት እምነት እውነት ሊሆን አይችልም» ይላሉ።
ታላቁ ፈላስፋ ፍሬዴሪክ ኒቼ ፦«የምታምነው ለመኖሩ ማስረጃ ማቅረብ ካልቻልክ እምነትህ ውሸት ነው፤ አባቴ ለእኔ ያስተላለፈው እምነት አያቴ የነገረውን ነው ፤ አያቴም የቅድም አያቴን ይዞ ለአባቴ አስተላለፈው፤ እንግዲህ እኔ የምኖርበት እምነት አስቀድሞ ሌሎች የኖሩበትን እንጂ እኔ በማስረጃ አረጋግጬ ያገኘሁት አይደለም ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ለእምነትህ ማስረጃ የለህምና ውሸት ነው›› ይላል፡፡ ሌሎችም ፈላስፎች በዚህ ይስማማሉ፡፡
እንግዲህ ወደ «እውነት» ጥያቄ ስንመጣ ኒቼ ሊነሳ የሚገባው ፈላስፋ ይሆናል፡፡ እንደኒቼ እምነት
«እውነት በተገቢ ሁኔታ የተነሳችበት የተጠየቀችበት በአንድ ሰውና በእንድ ቦታ ብቻ ነው፤ ይኸውም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እሱም በጲላጦስ ነው» ይላል፡፡ አናቶሊ ፍራንስም በዚህ አባባል «እስማማለሁ ብቻ ሳይሆን አምንበታለሁም» ይላል።
«ጲላጦስም፡- እንግዲህ ንጉሥ ነህን? አለው::
ኢየሱስም መልሶ፡-" እኔ ንጉሥ እንደሆንሁ አንተ ትላለህ እኔ ለእውነት ልመሰክር ተወልጃለሁ፤ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ድምፄን ይሰማል አለው፡፡"
ጲላጦስም፦ "እውነት ምንድር ነው? አለው"
ዮሐ 17:38
እነሆ እኛም እንደ ጲላጦስ እውነት ምንድን ነው? ብለን እንጠይቃችኋለን
@zephilosophy