"የላባቸው ዋጋ ይከፈላቸው!!"
የፍልስፍና ቻናላችን የጤና ባለሙያዎች ብሔርና ሀይማኖት ሳይለያያቸው ለመብታቸው መከበር በአንድነት ሆነው ያነሱትን የመብት ጥያቄ እና ትግል ይደግፋል።
የጤና ባለሙያዎች የመንግስት ውክቢያ እና እስር ሳይስፈራቸው ለመብታቸው በድፍረት ና በፅናት መቆማቸው መብቱ ቢጣስም በፍርሀት ለደነዘዘው የህብረተሰብ ክፍል ምሳሌ በመሆን መነሳሳትን ፈጥረዋል።
ሆኖም ግን ህዝቡ ተገቢውን እውቅናና ድጋፍ ባለመስጠቱ ምክንያት የመብት ጥያቄው በሀይል የመዳፈን ጥላ አጥልቶበታል። መንግስት በሚያደርገው የጭካኔ ድርጊት ምክንያት ከዶክተሩ የባሰ ችግር ያለበት የህብረተሰብ ክፍል የመብት ትግሉን እንዳይቀላቀል "ስራዬን አጣለሁ" የሚል ስጋት አድሮበታል።
ይህ ጥያቄ የጤና ባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን የአብዛኛው የመንግስት እና የግል ዘርፍ ሰራተኞች ጥያቄ ነው።መምህራኖች፣ የፍትህ ባለሙያዎች፣ ኢንጂነሮች ተገቢውን ደሞዝ እያገኙ አይደለም።
በ6 አመት ውስጥ ነዳጅን ጨምሮ አብዛኛው ምግብ እና መሰረታዊ ፍጆታ በሶስት እጥፍ(300%) ጨምሯል ለሰራተኛው የደሞዝ ጭማሪ የተደረገው ግን ከ30% በታች ነው።በዚህም ቤተሰቡን ለማስተዳደር ይቅርና የራሱን የእለት-ጉርስ እንኳን ለመሸፈን በቂ አይደለም።
ለልጆቹ የተሻለ ትምህርት የሚፈልግ ህዝብ መምህራኖች የተሻለ ደምወዝ እንዲያገኙ ማድረግ አለበት። ይህ ካልሆነ ፈፅሞ የትምህርት ጥራትን ሊጠብቅ አይገባውም መምህሩም ስራውን እንደተከበረ ስራ (profession) ሳይሆን እንደመጠባበቂያ (ጊዜ ማሳለፊያ) ስራ ሊቆጥረው ይገደዳል።
ከሙስና የፀዳ እውነተኛ ፍትህ ለማግኘት የሚፈልግ ህዝብ መጀመሪያ የዳኛ፣ የአቃቢ-ህግ ፣የፖሊስ ደሞዝ በቂ አይደለም ብሎ ሊታገል ይገባል።
ስርዓተ -አልበኝነት እንዲኖር የማይፈልግ ህዝብ ሰራተኛው ተገቢውን የላቡን ዋጋ እንዲከፈለው ማገዝ ይኖርበታል።አለበለዚያ ነጥቆ እና አጭበርብሮ የሚበላን ሰው እያበረታታ ነው ማለት ነው።
የዜጎች የመብት ጥያቄ የሚመለሰው ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል አንድ ሆኖ በመተባበር ድምፁን ሲያሰማ ነው።በተናጠል የሚደረግ ትግል ነጥሎ ለመምታት ያመቻልና ...
የህዝብን ሀብት ጠንካራ ገቢ በሚያሰገኙ ፕሮጀክቶች ላይ ከማዋል ይልቅ የሀገሩ ህዝብ እንኳን በነፃነት የማይንቀሳቅስበት አገር ላይ ለቱሪዝም ገቢ ብሎ ቢሊዮን ብሮችን በማውጣት የቅንጦት ሪዞርቶችና መናፈሻዎች መስራት ትክክል አይደለም።
በጦርነት የተጎዳውን ኢኮኖሚ መልሶ እንዲያገግም ከማድረግ ይልቅ ቢሊዮን ዶላሮችን አውጥቶ በአንድ አገር ሁለት ቤተ-መንግስት የሚሰራ መንግስት ህዝባዊ ተቃውሞ ካልገጠመው በስተቀር ይህን ስራውን ይቀጥላል።
በማጭበርበር እና በሙስና በአንድ ጀንበር ሚሊዮን ብሮችን በማጋበስ ሀገርቱ ላይ በነፃነት የሚርመሰመሱ ሰዎችን ከማሰር ይልቅ መብቱን በሰላማዊ መንገድ የጠየቀውን ዜጋ ማሰር እና ከስራ ማፈናቀል ፍትሀዊ አይደለም።
@zephilosophy
የፍልስፍና ቻናላችን የጤና ባለሙያዎች ብሔርና ሀይማኖት ሳይለያያቸው ለመብታቸው መከበር በአንድነት ሆነው ያነሱትን የመብት ጥያቄ እና ትግል ይደግፋል።
የጤና ባለሙያዎች የመንግስት ውክቢያ እና እስር ሳይስፈራቸው ለመብታቸው በድፍረት ና በፅናት መቆማቸው መብቱ ቢጣስም በፍርሀት ለደነዘዘው የህብረተሰብ ክፍል ምሳሌ በመሆን መነሳሳትን ፈጥረዋል።
ሆኖም ግን ህዝቡ ተገቢውን እውቅናና ድጋፍ ባለመስጠቱ ምክንያት የመብት ጥያቄው በሀይል የመዳፈን ጥላ አጥልቶበታል። መንግስት በሚያደርገው የጭካኔ ድርጊት ምክንያት ከዶክተሩ የባሰ ችግር ያለበት የህብረተሰብ ክፍል የመብት ትግሉን እንዳይቀላቀል "ስራዬን አጣለሁ" የሚል ስጋት አድሮበታል።
ይህ ጥያቄ የጤና ባለሙያዎች ብቻ ሳይሆን የአብዛኛው የመንግስት እና የግል ዘርፍ ሰራተኞች ጥያቄ ነው።መምህራኖች፣ የፍትህ ባለሙያዎች፣ ኢንጂነሮች ተገቢውን ደሞዝ እያገኙ አይደለም።
በ6 አመት ውስጥ ነዳጅን ጨምሮ አብዛኛው ምግብ እና መሰረታዊ ፍጆታ በሶስት እጥፍ(300%) ጨምሯል ለሰራተኛው የደሞዝ ጭማሪ የተደረገው ግን ከ30% በታች ነው።በዚህም ቤተሰቡን ለማስተዳደር ይቅርና የራሱን የእለት-ጉርስ እንኳን ለመሸፈን በቂ አይደለም።
ለልጆቹ የተሻለ ትምህርት የሚፈልግ ህዝብ መምህራኖች የተሻለ ደምወዝ እንዲያገኙ ማድረግ አለበት። ይህ ካልሆነ ፈፅሞ የትምህርት ጥራትን ሊጠብቅ አይገባውም መምህሩም ስራውን እንደተከበረ ስራ (profession) ሳይሆን እንደመጠባበቂያ (ጊዜ ማሳለፊያ) ስራ ሊቆጥረው ይገደዳል።
ከሙስና የፀዳ እውነተኛ ፍትህ ለማግኘት የሚፈልግ ህዝብ መጀመሪያ የዳኛ፣ የአቃቢ-ህግ ፣የፖሊስ ደሞዝ በቂ አይደለም ብሎ ሊታገል ይገባል።
ስርዓተ -አልበኝነት እንዲኖር የማይፈልግ ህዝብ ሰራተኛው ተገቢውን የላቡን ዋጋ እንዲከፈለው ማገዝ ይኖርበታል።አለበለዚያ ነጥቆ እና አጭበርብሮ የሚበላን ሰው እያበረታታ ነው ማለት ነው።
የዜጎች የመብት ጥያቄ የሚመለሰው ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል አንድ ሆኖ በመተባበር ድምፁን ሲያሰማ ነው።በተናጠል የሚደረግ ትግል ነጥሎ ለመምታት ያመቻልና ...
የህዝብን ሀብት ጠንካራ ገቢ በሚያሰገኙ ፕሮጀክቶች ላይ ከማዋል ይልቅ የሀገሩ ህዝብ እንኳን በነፃነት የማይንቀሳቅስበት አገር ላይ ለቱሪዝም ገቢ ብሎ ቢሊዮን ብሮችን በማውጣት የቅንጦት ሪዞርቶችና መናፈሻዎች መስራት ትክክል አይደለም።
በጦርነት የተጎዳውን ኢኮኖሚ መልሶ እንዲያገግም ከማድረግ ይልቅ ቢሊዮን ዶላሮችን አውጥቶ በአንድ አገር ሁለት ቤተ-መንግስት የሚሰራ መንግስት ህዝባዊ ተቃውሞ ካልገጠመው በስተቀር ይህን ስራውን ይቀጥላል።
በማጭበርበር እና በሙስና በአንድ ጀንበር ሚሊዮን ብሮችን በማጋበስ ሀገርቱ ላይ በነፃነት የሚርመሰመሱ ሰዎችን ከማሰር ይልቅ መብቱን በሰላማዊ መንገድ የጠየቀውን ዜጋ ማሰር እና ከስራ ማፈናቀል ፍትሀዊ አይደለም።
@zephilosophy