ግንቦት የእምዬ ማርያም ወር
ደራሲ- ስብሀት ገ/እግዚሀብሔር
መፅሀፍ-ሽፍቶችና መሪዎች
በአፈ-ታሪክ ላይ የተመረኮዘ ጥናታዊ ፅሁፍ
ያገራችን ሴት በስጋ የሄዋን ልጅ፡ በመንፈስ የማርያም ልጅ ናት ብለን እናምናለን። ይህን ፅሁፍ ለሴት ልጅ ሁሏ በከበሬታ እንደ ገፀ-በረከት እናቀርባለን - ወላዲታችን ናትና። እንኳን ማርያም ማረችሽ፡ ማርያም በሽልም ታውጣሽ፣ እንላታለን የማርያምን አራስ።
የአባ ኪዳነ ማርያምን፣ ቅኝት እንከተላለን።
የአለም መድኃኒት እመሀላቸው ተወልዶ ቢሰቀልላቸው፣ ካዱት። እኛ ግን አመንን!!
“ኢትዮጵያ ታበፅህ እደዊሀ ሀበ እግዚአብሄር” ብሏል ነብዩ ዳዊት። “ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች”
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተነስቶ፣ ከደቀ መዛሙርቱና ከሌሎቹ አማኞቹና ተከታዮቹ ጋር ሰነባብቶ ወደ አባቱ ሊያርግ ሆነ።
ድንግል እናቱን ሲሰናበት፣ እንዲህ አላት
“የኢትዮጵያን ምድር ለርስት ጉልትሽ ሰጥቼሻለሁ”
እንግዲህ እቺ ሀገር ድንግል በክልኤ ማርያምን አጥብቃ የምትወዳት ያለምክንያት አይደለም። የአስራት ሀገሯ ስለሆነች!!
ቤተ ክህነት የቅዱሳንን በአላት በሙሉ ከነደባሎቹ ታቦት! ታውቅ እና ታክብር እንጂ፣ ምድረ ሀበሻ ግን በወሩ በአንድ ልደታ፣ በሦስት በአታ፣ በአስራ ስድስት ኪዳነምህረት ፣ በሀያ አንድ ማርያም እያለ ነው ሄዶ የሚያስቀድሰው።
ምእመናን ከቤተ ክርስቲያን ሲወጡ ብናስተውል፣ አብዛኛዎቹ ነጭ ያገር ልብስ የለበሱ ሴቶች ናቸው። ወንዶቹ በቁጥር ቢበዛ አንድ አስረኛ ሲሆኑ፣ ለዚያውም አብዛኛዎቹ የፈረንጅ ኮትና ሱሪ የለበሱ ናቸው።
አራስ ልጅ ሆነንም ቋንቋችንን እና ባህላችንን የምታስተምረን እናታችን ናት።ልጅ ሆነንም አንጥልጥላን ቤተ ክርስትያን የምትወሰደን እናታችን ናት ።ህዝብ ሆነንም ዝማሬም ሽብሸባም ለእምነትም ለእንጀራም እንቀጥላለን እንጂ፣ ቤተ ክርስትያኑን የምትሞላው ግን ሴት ልጅ ናት።
ግንቦት የእምዬ ማርያም ወር ነች
በግንቦት አንድ ፣ ሶስት ፣አስራ ስድስት ፣ሀያ አንድ በቅደመ ተከል -ልደታ፣ ባእታ ፣ኪዳነ ምህረት ፣ማርያም እያለን በብዙ ድምቀት እናከብራታለን።
(በጥቂቱ አጥሮና ታርሞ የቀረበ)
@zephilosophy
ደራሲ- ስብሀት ገ/እግዚሀብሔር
መፅሀፍ-ሽፍቶችና መሪዎች
በአፈ-ታሪክ ላይ የተመረኮዘ ጥናታዊ ፅሁፍ
ያገራችን ሴት በስጋ የሄዋን ልጅ፡ በመንፈስ የማርያም ልጅ ናት ብለን እናምናለን። ይህን ፅሁፍ ለሴት ልጅ ሁሏ በከበሬታ እንደ ገፀ-በረከት እናቀርባለን - ወላዲታችን ናትና። እንኳን ማርያም ማረችሽ፡ ማርያም በሽልም ታውጣሽ፣ እንላታለን የማርያምን አራስ።
የአባ ኪዳነ ማርያምን፣ ቅኝት እንከተላለን።
የአለም መድኃኒት እመሀላቸው ተወልዶ ቢሰቀልላቸው፣ ካዱት። እኛ ግን አመንን!!
“ኢትዮጵያ ታበፅህ እደዊሀ ሀበ እግዚአብሄር” ብሏል ነብዩ ዳዊት። “ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች”
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተነስቶ፣ ከደቀ መዛሙርቱና ከሌሎቹ አማኞቹና ተከታዮቹ ጋር ሰነባብቶ ወደ አባቱ ሊያርግ ሆነ።
ድንግል እናቱን ሲሰናበት፣ እንዲህ አላት
“የኢትዮጵያን ምድር ለርስት ጉልትሽ ሰጥቼሻለሁ”
እንግዲህ እቺ ሀገር ድንግል በክልኤ ማርያምን አጥብቃ የምትወዳት ያለምክንያት አይደለም። የአስራት ሀገሯ ስለሆነች!!
ቤተ ክህነት የቅዱሳንን በአላት በሙሉ ከነደባሎቹ ታቦት! ታውቅ እና ታክብር እንጂ፣ ምድረ ሀበሻ ግን በወሩ በአንድ ልደታ፣ በሦስት በአታ፣ በአስራ ስድስት ኪዳነምህረት ፣ በሀያ አንድ ማርያም እያለ ነው ሄዶ የሚያስቀድሰው።
ምእመናን ከቤተ ክርስቲያን ሲወጡ ብናስተውል፣ አብዛኛዎቹ ነጭ ያገር ልብስ የለበሱ ሴቶች ናቸው። ወንዶቹ በቁጥር ቢበዛ አንድ አስረኛ ሲሆኑ፣ ለዚያውም አብዛኛዎቹ የፈረንጅ ኮትና ሱሪ የለበሱ ናቸው።
አራስ ልጅ ሆነንም ቋንቋችንን እና ባህላችንን የምታስተምረን እናታችን ናት።ልጅ ሆነንም አንጥልጥላን ቤተ ክርስትያን የምትወሰደን እናታችን ናት ።ህዝብ ሆነንም ዝማሬም ሽብሸባም ለእምነትም ለእንጀራም እንቀጥላለን እንጂ፣ ቤተ ክርስትያኑን የምትሞላው ግን ሴት ልጅ ናት።
ግንቦት የእምዬ ማርያም ወር ነች
በግንቦት አንድ ፣ ሶስት ፣አስራ ስድስት ፣ሀያ አንድ በቅደመ ተከል -ልደታ፣ ባእታ ፣ኪዳነ ምህረት ፣ማርያም እያለን በብዙ ድምቀት እናከብራታለን።
(በጥቂቱ አጥሮና ታርሞ የቀረበ)
@zephilosophy