አባ ይፍቱኝ
(በእወቀቱ ስዩም)
ሲኦል አለ ሲሉኝ፥ የለም ብየ ክጀ
የባልቴት ተረት ነው፥ በማለት ቀልጀ
አውቄ በድፍረት፥ በድያለሁና
ያንጹኝ በንስሐ፥ ያንሱኝ በቀኖና
ሲኦል ከነጭፍራው፥ በጉም ተሸፍኖ
እንዴት ሳላየው ኖርኩ፥ ካጠገቤ ሆኖ?
አባ ይፍቱኝ
ሰይጣን ብሎ ነገር፥ የተጭበረበረ
ዋዛ ነው ቧልት ነው፥ ብየ አስብ ነበረ
ይሄው እውነት ሆኖ፥ ዋዛና ተረቱ
ባይኔ በብረቱ
ዲያብሎስን አየሁት፥ በሸሚዝ ዘንጦ
እልፍ ግዳይ ጥሎ፥ ቸብቸቦ ጨብጦ
አባ
ልክ እንደ ብርሌ፥ አጥንት ሲከሰከስ
አባይን አዋሽን፥ የሚያስንቅ ደም ሲፈስ
ለምለም ፍጥረት ሁላ፥ ወደ አመድ ሲመለስ
ልክ እንደ ጧፍ ሐውልት፥ ምስኪኖች ሲጋዩ
ምድጃው ዳር ሆነው፥ ይሄንን እያዩ
ገሃነም ከላይ ነው፥ ብለው መሳትዎ
እርስዎ እንደፈቱኝ፥ እግዚሃር ይፍታዎ፡፡
@zephilosophy
(በእወቀቱ ስዩም)
ሲኦል አለ ሲሉኝ፥ የለም ብየ ክጀ
የባልቴት ተረት ነው፥ በማለት ቀልጀ
አውቄ በድፍረት፥ በድያለሁና
ያንጹኝ በንስሐ፥ ያንሱኝ በቀኖና
ሲኦል ከነጭፍራው፥ በጉም ተሸፍኖ
እንዴት ሳላየው ኖርኩ፥ ካጠገቤ ሆኖ?
አባ ይፍቱኝ
ሰይጣን ብሎ ነገር፥ የተጭበረበረ
ዋዛ ነው ቧልት ነው፥ ብየ አስብ ነበረ
ይሄው እውነት ሆኖ፥ ዋዛና ተረቱ
ባይኔ በብረቱ
ዲያብሎስን አየሁት፥ በሸሚዝ ዘንጦ
እልፍ ግዳይ ጥሎ፥ ቸብቸቦ ጨብጦ
አባ
ልክ እንደ ብርሌ፥ አጥንት ሲከሰከስ
አባይን አዋሽን፥ የሚያስንቅ ደም ሲፈስ
ለምለም ፍጥረት ሁላ፥ ወደ አመድ ሲመለስ
ልክ እንደ ጧፍ ሐውልት፥ ምስኪኖች ሲጋዩ
ምድጃው ዳር ሆነው፥ ይሄንን እያዩ
ገሃነም ከላይ ነው፥ ብለው መሳትዎ
እርስዎ እንደፈቱኝ፥ እግዚሃር ይፍታዎ፡፡
@zephilosophy