"ሥልጣን ያባልጋል፤ እውነት ነው፤ ፍጹማዊ ሥልጣን ደግሞ የባለጌ ባለጌ እንደሚያደርግ የሮማ ካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ጎርጎሪያ ሶስተኛ የተናገሩት ሀሳብ ግሩም ምስክር ይሆናል᎓᎓ ነገር ግን፣ ይህም ታውቆ እንኳን ዛሬም እንደ ትላንቱ ሥልጣን የአያሌዎችን ልብ እያጓጓች፤ ልክፍት በሚመስል አስፈሪ ፍቅሯ እንደማግኔት ትስባቸዋለች:: ድሮም ሆነ ዘንድሮ የመንበር ጥማት ያው የመንበር ጥማት ነው፤ ከብዙዎች ልብ ተፍቆ አልወጣም:: ሥልጣን፣ ቢሰሩባትም ባይሰሩባትም እርካቧን የረገጠ፣ ኮርቻውን የተቆናጠጠ፣ መንበሯ ላይ የተደላደለ ሁሉ (ቢያንስ አብዛኛው) በሞቱ እንጂ በፈቃዱ ሊለያት የማይሻ ጦሰኛ ፍቅሯ ተቀፍድዶ ይኖራል፡፡ አፍቃሪዋም ዘመኑን ሁሉ ሲጨነቅና ሲጠበብ ዕድሜውን የሚገብርላት፣ የክብሩ ዘውድ፣ ወይም የመራራ ውርደቱ ፅዋ ትሆናለች።"
(ዲራአዝ፤ እርካብና መንበር)
@zephilosophy
(ዲራአዝ፤ እርካብና መንበር)
@zephilosophy