ከምነቴ ጋር ቀረሁ
አውቃለሁ!
አታምኝም በማምነው
ያንደኛው ሰው መንገድ፣ ለሌላው ገደል ነው።
ቢቀና ጎዳናው፣ ቢወለወል አስፋልት
አብሮ ከማያልም፣ አብሮ መሄድ ልፋት
ያንደኛው ሰው እግር፣ ለሌላው እንቅፋት።
ባልጮህ ባደባባይ
ምኩራብ ባልገነባ፣ መዝሙር ባላሰማ
ከጥላየ በቀር፣ ባይኖረኝ ተከታይ
በቃል ወይ በዜማ
ተገልጦ ባይታይ
በልብ ተጠንስሶ፣ ባይን የሚገነፍል
እኔም እምነት አለኝ፣ ዋጋ የሚያስከፍል።
እምነት - ተስፋ - ፍቅር
መች ባንድ ላይ ሁኖ
ለሰው ልጅ ይሰጣል
በምነቱ የፀና፣ ድንገት ፍቅሩን ያጣል
ፍቅርሽን ሸኝቼው፣ ተስፋየን አባረርሁ
ከምነቴ ጋር ቀረሁ፡፡
በእውቀቱ ስዩም
📚አዳምኤል
@zephilosophy
አውቃለሁ!
አታምኝም በማምነው
ያንደኛው ሰው መንገድ፣ ለሌላው ገደል ነው።
ቢቀና ጎዳናው፣ ቢወለወል አስፋልት
አብሮ ከማያልም፣ አብሮ መሄድ ልፋት
ያንደኛው ሰው እግር፣ ለሌላው እንቅፋት።
ባልጮህ ባደባባይ
ምኩራብ ባልገነባ፣ መዝሙር ባላሰማ
ከጥላየ በቀር፣ ባይኖረኝ ተከታይ
በቃል ወይ በዜማ
ተገልጦ ባይታይ
በልብ ተጠንስሶ፣ ባይን የሚገነፍል
እኔም እምነት አለኝ፣ ዋጋ የሚያስከፍል።
እምነት - ተስፋ - ፍቅር
መች ባንድ ላይ ሁኖ
ለሰው ልጅ ይሰጣል
በምነቱ የፀና፣ ድንገት ፍቅሩን ያጣል
ፍቅርሽን ሸኝቼው፣ ተስፋየን አባረርሁ
ከምነቴ ጋር ቀረሁ፡፡
በእውቀቱ ስዩም
📚አዳምኤል
@zephilosophy