የመጀመሪያዋ ሴት "ሊልዝ"
የሔዋንን የሴት ቀዳሚነትነትን የማይቀበሉ ግለሰቦች ሊልዝ የሚልን ስም ሲያነሱ ይሰማል፡፡ ሊልዝ ከሔዋን በፊት የተፈጠረች ሴት ስትሆን፤ የአዳም የመጀመሪያዋ ሚስት ናትም ይሏታል፡፡ ሊልዝ ከሔዋን መቅደሟን በተመለከተ ከሚቀርቡት መከራከርያዎች መካከል ከመጽሐፍ ቅዱስ አንፃር የሚነሳውን ለማንሳት ያህል፡ አንደኛው በዘፍጥረት መጽሐፍ 1፡27 ላይ የተቀመጠውን ትረካ የሚመለከት ነው፤ ይህ ክፍል ፈጣሪ ወንድ እና ሴትን በአንድ ጊዜ እንደፈጠረ የሚናገር ሲሆን በዚህ ክፍል ላይ ከአዳም ጋር በተመሳሳይ ጊዜ የተፈጠረቸዋ ሴት ሔዋን ሳትሆን ሊልዝ ናት የሚል ድምዳሜ ይነሳል፡፡ ሌላኛው የኢሳያስ መጽሐፍ 34፡14” ነው፤ በዚህ ላይም የተገለጸቹ ሊልዝ መሆኗ አከራካሪ ኢይደለም ይሉናል የሔዋን ቀዳሚት ሴትነትን የማይቀበሉት፡፡ ከመጽሐፍ ቅዱስ ባሻገር “Talmud”፣ “Kabbalah” እና “Alphabet of Ben Sira" ተብለው በሚጠሩ የሂብሪው መጽሐፍት ላይ ሊልዝ ስሟ በግልጽ ሰፍሮ ይገኛል፡፡እነዚህ መፅሀፎች የአዳም የመጀመሪያ ሚስት ሊሊዝ እንደሆነች፣ ኾኖም ከአዳም ጋር እኩል ነን አይደለንም በሚል ጭቅጭቅ ምክንያት እንደተለየችው ይተረካሉ፡፡
ሊልዝ ከገነት ከወጣች በኃላ የክፉ መናፍስት እናት በመሆን በሌሊት ህጻናት ገዳይ እና የሴሰኝነት ምንጭ ተደርጋ በአይሁዶች ዘንድ ዛሬም ድረስ ትወሰዳለች፡፡ በሌላ በኩል ስለ ሴቶች መብት እና እኩልነት አጥበቀው የሚከራከሩን ፌሚኒስቶች ሊልዝን የነጻነት እና የእኩልነት ምልክት አድርገው ይወስዷታል፡፡ ለዚህ ማሳያ በእስራኤል በሴቶች መብት እና እኩልነት ላይ ያተኮረ “Lilith” የሚል መጽሔት እንደሚገኝ መጥቀስ ይችላል፡፡ እንዲሁም ፌሚኒስት የሆኑ ጸሓፍት በዘፍጥረት መጽሐፍ ላይ ያለው የሰው አፈጣጠር ትረካ ዳግም መከለስ አለበት በማለት የተለያዩ ድርሳናትን ጽፈዋል፡፡ አብዛኞቹ መጽሐፍት የመጀመሪያዎቹ ሰዎች አፈጣጠር ትረካ መምስል ያለበት የሚሉት፦
"በመጀመሪያ እግዚአብሔር አዳም እና ሊልዝን ከአፈር አበጃቸው፡፡ የሕይወት እስትንፋስንም በአፍንጫቸው ተነፈሰባቸው፡፡ ሁለቱም ከተመሳሳይ ነገር ተፈጥረዋልና እኩል እና አቻ ነበሩ፡፡ እኩልነታቸውን ያልወደደው አዳም ታዲያ ወደ ፈጣሪ ቀርቦ ቅሬታውን አቀረበ፡፡ ፈጣሪም አዳምን ሰምቶ ሊልዝ አዳም እንደፈለገው የበታቹ እንድትሆን፣ ካለዚያ ከገነት እንደምትወጣ ነገራት፡፡ ሊልዝም ከአዳም በታች ከምትሆን ይልቅ ከገነት መውጣትን መረጠች:: ፈጣሪም ይህን ባየ ጊዜ ለአዳም ሌላ ሴት መፍጠርን ወሰነ፡፡ ከአዳም ግራ ጎንም ሔዋንን ፈጠረ "
የሚል መልክ ያለው ነው::
@Zephilosophy
የሔዋንን የሴት ቀዳሚነትነትን የማይቀበሉ ግለሰቦች ሊልዝ የሚልን ስም ሲያነሱ ይሰማል፡፡ ሊልዝ ከሔዋን በፊት የተፈጠረች ሴት ስትሆን፤ የአዳም የመጀመሪያዋ ሚስት ናትም ይሏታል፡፡ ሊልዝ ከሔዋን መቅደሟን በተመለከተ ከሚቀርቡት መከራከርያዎች መካከል ከመጽሐፍ ቅዱስ አንፃር የሚነሳውን ለማንሳት ያህል፡ አንደኛው በዘፍጥረት መጽሐፍ 1፡27 ላይ የተቀመጠውን ትረካ የሚመለከት ነው፤ ይህ ክፍል ፈጣሪ ወንድ እና ሴትን በአንድ ጊዜ እንደፈጠረ የሚናገር ሲሆን በዚህ ክፍል ላይ ከአዳም ጋር በተመሳሳይ ጊዜ የተፈጠረቸዋ ሴት ሔዋን ሳትሆን ሊልዝ ናት የሚል ድምዳሜ ይነሳል፡፡ ሌላኛው የኢሳያስ መጽሐፍ 34፡14” ነው፤ በዚህ ላይም የተገለጸቹ ሊልዝ መሆኗ አከራካሪ ኢይደለም ይሉናል የሔዋን ቀዳሚት ሴትነትን የማይቀበሉት፡፡ ከመጽሐፍ ቅዱስ ባሻገር “Talmud”፣ “Kabbalah” እና “Alphabet of Ben Sira" ተብለው በሚጠሩ የሂብሪው መጽሐፍት ላይ ሊልዝ ስሟ በግልጽ ሰፍሮ ይገኛል፡፡እነዚህ መፅሀፎች የአዳም የመጀመሪያ ሚስት ሊሊዝ እንደሆነች፣ ኾኖም ከአዳም ጋር እኩል ነን አይደለንም በሚል ጭቅጭቅ ምክንያት እንደተለየችው ይተረካሉ፡፡
ሊልዝ ከገነት ከወጣች በኃላ የክፉ መናፍስት እናት በመሆን በሌሊት ህጻናት ገዳይ እና የሴሰኝነት ምንጭ ተደርጋ በአይሁዶች ዘንድ ዛሬም ድረስ ትወሰዳለች፡፡ በሌላ በኩል ስለ ሴቶች መብት እና እኩልነት አጥበቀው የሚከራከሩን ፌሚኒስቶች ሊልዝን የነጻነት እና የእኩልነት ምልክት አድርገው ይወስዷታል፡፡ ለዚህ ማሳያ በእስራኤል በሴቶች መብት እና እኩልነት ላይ ያተኮረ “Lilith” የሚል መጽሔት እንደሚገኝ መጥቀስ ይችላል፡፡ እንዲሁም ፌሚኒስት የሆኑ ጸሓፍት በዘፍጥረት መጽሐፍ ላይ ያለው የሰው አፈጣጠር ትረካ ዳግም መከለስ አለበት በማለት የተለያዩ ድርሳናትን ጽፈዋል፡፡ አብዛኞቹ መጽሐፍት የመጀመሪያዎቹ ሰዎች አፈጣጠር ትረካ መምስል ያለበት የሚሉት፦
"በመጀመሪያ እግዚአብሔር አዳም እና ሊልዝን ከአፈር አበጃቸው፡፡ የሕይወት እስትንፋስንም በአፍንጫቸው ተነፈሰባቸው፡፡ ሁለቱም ከተመሳሳይ ነገር ተፈጥረዋልና እኩል እና አቻ ነበሩ፡፡ እኩልነታቸውን ያልወደደው አዳም ታዲያ ወደ ፈጣሪ ቀርቦ ቅሬታውን አቀረበ፡፡ ፈጣሪም አዳምን ሰምቶ ሊልዝ አዳም እንደፈለገው የበታቹ እንድትሆን፣ ካለዚያ ከገነት እንደምትወጣ ነገራት፡፡ ሊልዝም ከአዳም በታች ከምትሆን ይልቅ ከገነት መውጣትን መረጠች:: ፈጣሪም ይህን ባየ ጊዜ ለአዳም ሌላ ሴት መፍጠርን ወሰነ፡፡ ከአዳም ግራ ጎንም ሔዋንን ፈጠረ "
የሚል መልክ ያለው ነው::
@Zephilosophy