Posts filter


የ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ቀጥለው ይካሄዳሉ
*********************************

የ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ቀጥለው ሲካሄዱ አርሰናል ከ ኒውካስትል ምሽት 12:30 ላይ በኢምሬትስ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።

በደረጃ ሰንጠረዡ ላይ አርሰናል በ2ኛ ኒውካስትል በ3ኛ ደረጃ ላይ ተከታትለው ተቀምጠዋል።

በመካከላቸው ያለው ልዩነት 2 ነጥብ ብቻ ሲሆን ኒውካስትል የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፈ 2ኛ ደረጃን መያዝ ይችላል። አርሰናል ደረጃውን ላለመልቀቅ የሚፋለም ይሆናል።

ከኢምሬቱ ጨዋታ ቀድም ብሎ በሚካሄዱ መርሐ ግብሮች ኤቨርተን ከሳውዛምፕተን ቀን 8 ሰዓት ላይ በ ጉዲሰን ፓርክ ይጫወታሉ።

የዛሬው ጨዋታ ለኤቨርተን በጉዲሰን ፓርክ የሚያደርጉት የመጨረሻው ጨዋታቸው ሲሆን፤ ቡድኑ በቀጣይ ዓመት ወደ አዲሱ ስታዲየም የሚያቀና ይሆናል።

በሌላ መርሐ ግብር ቀን 10:15 ዌስትሃም ከኖቲንግሃም ፎረስት በለንደን ስታዲየም ይጫወታሉ።

አንዲሁም ቀን 11 ሰዓት ብሬንት ፎርድ ከ ፉልሃም፤ ሌስተር ሲቲ ከ ኢፕ ስዊች የሚጫወቱ ይሆናል።

በሴራን ታደሰ

ኢቢሲ የስፖርት ገፅ

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ




ክለቦች የምዕተ ዓመት የዋንጫ ረሀባቸውን ያስታገሱበት (2024/25)

1. ክሪስታል ፓላስ - በ120 ዓመት የክለቡ ታሪክ ማንችስተር ሲቲን በማሸነፍ ለመጀመርያ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ያነሳበት።

ንስሮቹ ከአሁን በፊት ሁለት ጊዜ በኤፍ ኤ ዋንጫ ለፍጻሜ ቢደርሱም በማንችስተር ዩናይትድ ተሸንፈው ክብሩን ማጣታቸው ይታወሳል።

2. ጎ ኤሄድ ኤግልስ - በኤርዲቪዜው የሚሳተፈው ክለብ የደች ዋንጫን በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ ሲያነሳ ዘንድሮ ከ 93 ዓመት በኋላ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ሆኗል።

3. ኒውካስል ዩናይትድ - ከተመሰረተ 133 ዓመት የሆነው ኒውካስትል የእንግሊዝ ሊግ ካፕን ለመጀመርያ ጊዜ ያነሳበት ዓመት ሆኗል።ክለቡ ከዋንጫ ጋር ሲገናኝ ደግሞ ከ70 ዓመት በኋላ ነው።

4. ቦሎኛ - በጣልያን ዋንጫ ፍጻሜ ኤሲ ሚላንን በማሸነፍ ከ51 ዓመት በኋላ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ነው።

በቀጣይ ሁለት ሳምንት ውስጥ መልስ ሊያገኙ የሚችሉ የረጅም ዓመታት የዋንጫ ጥያቄዎች

• ፒ ኤስ ጂ - በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ የደረሰው የፈረንሳዩ ሀብታም ክለብ ኢንተር ሚላን ማሸነፍ ከቻለ ለመጀመርያ ጊዜ የአህጉሩን ትልቁን ክብር የሚያሳካበት ይሆናል።

• ሪያል ቤቲስ - በአውሮፓ ኮንፍረንስ ሊግ ለፍጻሜ የደረሰው የስፔኑ ክለብ ቼልሲን ካሸነፍ ለመጀመርያ ጊዜ የአውሮፓ መድረክ ውድድር ላይ የነገሰበት ይሆናል።

• ቶተንሀም ሆትስፐርስ - በዩሮፓ ሊግ ፍጻሜ ከማንችስተር ዩናይትድ የሚገናኝበትን ፈተና በድል የሚወጣ ከሆነ የ40 ዓመታት የዩሮፓ ሊግ የዋንጫ ድርቁን ያስታግሳል።

• ሀሪ ኬን - በግል ደግሞ የ31 ዓመቱ እንግሊዛዊው ሃሪ ኬን ለመጀመርያ ጊዜ ከዋንጫ ጋር የተገናኝበት ዓመት ሆኖለታል።

በአንተነህ ሲሳይ

ኢቢሲ የስፖርት ገፅ

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ


የፕሬዝዳንቶቹ የስልክ ውይይት
************************

ፕሬዝዳንት ትራምፕ እና ፕሬዝዳንት ፑቲን በስልክ ለመመከር ቀጠሮ መያዛቸውን ከክሬምሊን የወጡ መረጃዎች አመላክተዋል::

የኢስታንቡል የሰላም ውይይትን ተከትሎ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር ለመምከር ቀጥሮ መያዛቸውን በትሩዝ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል::

የሁለቱ መሪዎች የስልክ ውይይት ለነገ ሰኞ ቀጠሮ የተያዘለት ስለመሆኑ ክሬምሊን አረጋግጧል::

የመሪዎቹ ውይይት የሩስያ ዩክሬን ጦርነት እንዲያበቃ በሚያስችል ጉዳይ ላይ እንደሚሆን ይጠበቃል::

የሁለቱ ሀገራት የንግድ ጉዳይ በፕሬዝዳንቶቹ የስልክ ውይይት ላይ የሚነሳ ሌላው አጀንዳ እንደሚሆንም ይጠበቃል::

ፕሬዝዳንት ትራምፕ "የሩስያ ዩክሬንን ሰላም ማምጣት የምችለው እኔ ነኝ" ማለታቸው የሚታወስ ነው ሲል ቲአርቲ ዘግቧል::

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ




ኢትዮጵያ እየፈጠረች ያለው የቴክኖሎጂ አቅም የታየበት መድረከ
**************

በምሥራቅ አፍሪካ ትልቁ የሆነው እና በዓይነቱ ልዩ የሆነው ETEX2025 ኢትዮጵያ እየፈጠረችው ያለው አቅም ምን ያክል እንደሆነ ያሳየ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ETEX2025 ላይ ሥራዎቻቸውን ያቀረቡት ስታርታፖች ከሌላው ዓለም ከመጡት አቻዎቻቸው እና ከኢንቨስተሮች ጋር ትስስር ሊፈጥሩ መቻላቸውን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

በ2010 ዓ.ም ላይ እንደሀገር የነበሩ ስታርታፖች በጣም ጥቂቶች እንደነበሩ ያስታወሱት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በአሁኑ ጊዜ ከሁለት ሺህ በላይ ስታርታፖች እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

ከነዚህ መካከል ምርቶችን እና አገለግሎቶችን ማቅረብ የጀመሩ እና ከፍተኛ ተስፋ የሚጣልባቸው መኖራቸውን አውስተው፣ በዚህ ኤክስፖ ላይ አገልግሎቶቻቸውን እና ምርቶቻቸውን ያቀረቡት በልዩ ሁኔታ የተመረጡ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ ካላት ከፍተኛ የሰው ቁጥር ውስጥ 70 በመቶ እና ከዚያ በላይ ወጣት እንደሆነ የጠቀሱት ዶክተር ባይሳ፣ ስታርታፕ ይህን የወጣት ኃይል አምራች እንዲሆን እና ለሀገር ጠቃሚ ሥራ እንዲሠራ ያስችለዋል ብለዋል፡፡

መንግሥት የሀገርን ብልፅግና ለማረጋገጥ ባለው ቁርጠኝነት ስታርታአፕ ላይ አተኩሮ እየሠራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ወጣቶች ብቁ የኢንዱስትሪ ፈጣሪ እንዲሆኑ አቅማቸውን የማጎልበት እና የሥራ ካባቢን የማመቻቸት ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ዘርፍ እንደ ሀገር ያሉብንን ችግሮች መፍቻ፣ ልማትን ማፍጠኛ እና ተወዳዳሪነትን ማረጋገጫ እንዲሆን መንግሥት በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል ያሉት ሚኒስትር ዴታው፣ በፈጠራ የሚመራ ኢኮኖሚን ማጎልበት ደግሞ ዓላማው እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ሽግግሮችን በማፋጠን ውጤታማ የሆኑ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለማምረት ስታርታፖች ከፍተኛ ሚና እንዳላቸውም ነው ዶክተር ባይሳ የተናገሩት፡፡

ስታርታፕ ለበርካታ ሀገራት የፈጠራ መስክ እና የዕድገት መነሻቸው እንደሆነ የጠቀሱት ዶክተር ባይሳ፣ ኢትዮጵያም የምትፈልገውን በፈጠራ የታገዘ ኢኮኖሚን ለመገንባት ለስታርታፖች ከሀሳብ ጀምሮ በየደረጃው አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገች እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

በምሥራቅ አፍሪካ ትልቁ የሆነው እና በዓይነቱ ልዩ የሆነው ETEX2025 ኢትዮጵያ እየፈጠረችው ያለው አቅም ምን ያክል እንደሆነ ያሳየ መሆኑን ጠቅሰው፣ ቀጣይ ተስፋችንንም ያመላከተ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በለሚ ታደሰ


ሀሪ ኬን ለ2ኛ ተከታታይ ዓመት የኮከብ ግብ አግቢ ሽልማት አሸነፈ
*****************

እንግሊዛዊው የባየር ሙኒኩ ተጫዋች ሃሪ ኬን የ2024/25 የውድድር ዘመን በ26 ግቦች በማጠናቀቀ ለሁለተኛ ጊዜ የቶርጃገርካኖኔን ሽልማት አሸናፊ ሆኗል።

ሀሪ ኬን በቡንደስሊጋ ታሪክ ቡድኑን በተቀላቀለ በመጀመርያዎቹ ሁለት ተከታታይ የውድድር ዘመናት ከፍተኛ ግብ በማስቆጠር የቶርጃገርካኖኔን ሽልማት ያሸነፈ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል።

ሻምፒዮኑ ባየርን ሙኒክ በዛሬው እለት ሆፈንሃይምን 4 ለ 0 በማሸነፍ የውድድር ዘመኑን ጨዋታዎች አጠናቋል።

በጨዋታው ሃሪ ኬን በ86ኛው ደቂቃ ግብ በማግባት በውድድር ዘመኑ ያስቆጠራቸውን ግቦች 26 ማድረስ ችሏል።

በሴራን ታደሰ


በአሜሪካ ሁለት ግዛቶች በተከሰተ ከባድ አውሎ ንፋስ 21 ሰዎች ሞቱ
**********************

በአሜሪካ ኬንታኪ እና ሚዙሪ ግዛቶች ሌሊቱን በተከሰተ ከባድ አውሎ ንፋስ 21 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ተገለፀ፡፡

በኬንታኪ ግዛት ቢያንስ 14 ሰዎች መሞታቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡

በደቡብ ምስራቅ የግዛቱ ክፍል በተከሰተው ከባድ አውሎ ንፋስ የተጎጂዎች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊጨመር እንደሚችልም ባለስልጣናቱ ገልፀዋል።

በአጎራባች ሚዙሪ ግዛት ቢያንስ ሰባት ሰዎች መሞታቸው የተገለፀ ሲሆን በሌሎች ግዛቶችም የሰው ህይወት ባያልፍም በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል፡፡

በአውሎ ንፋሱ ምክንያት በተለያዩ የሃገሪቱ ግዛቶች ውስጥ የሚገኙ ከ600,000 በላይ ቤቶች እና የንግዶች ድርጅቶች የኤሌክትሪክ ኃይል እንደተቋረጠባቸው ተጠቅሷል፡፡

ከሁለት ወራት በፊት በኬንታኪ ግዛት በከባድ የአየር ሁኔታ 24 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የቢቢሲ ዘገባ አስታውሷል፡፡


ሊቨርፑል ጀርሚ ፍሪምፖንግን ከባየር ሊቨርኩሰን ለማስፈረም ተስማማ
******************

ሊቨርፑል የባየር ሊቨርኩሰኑን የቀኝ መስመር ተከላካይ ጀርሚ ፍሪምፖንግን ለማስፈረም ተስማምተዋል።

ኔዘርላንዳዊው ተጫዋች የህክምና ምርመራውን ካደረገ በኋላ በሊቨርፑል ቤት የሚያቆየውን የ 5 አመት ኮንትራት ይፈርማል።

በመሆኑም ሊቨርፑል ለባየር ሙኒክ 35 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ክፍያን ለተጫዋቹ የውል ማፍረሻ ይከፍላል።

ኔዘርላንዳዊው የቀኝ መስመር ተከላካዩ ጄሪሚ ፍሪፖንግ የትሬት አሌክሳንደር አርኖልድ ተተኪ በመሆን አንደሚጫወት ይጠበቃል።

በሴራን ታደሰ


ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ሥራዎችን በመገንባት ረገድ አርአያ እየሆነች ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
************************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን ለአፍሪካ ብልጽግና እና ትብብር” በሚል ጭብጥ እየተካሄደ ባለው “አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካ” መርኃ ግብር ላይ ንግግር አድርገዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸውም፤ ኢትዮጵያ አካታች የሆኑ የቴክኖሎጂ ሥራዎችን በመገንባት ረገድ አርአያ እየሆነች መምጣቷን ተናግረዋል፡፡

የዲጂታል ቴክኖሎጂን በሁሉም አገልግሎቶች ላይ ለመተግበር መንግስት ትኩረት አድርጎ በመስራት ላይ መሆኑንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

በጥቂት አመታት ውስጥ ከ50 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን የዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ይሆናሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህም ዜጎች የተለያዩ አገልግሎቶችን ማግኘት እንዲችሉ እና አዳዲስ እድሎችንም እንዲያገኙ ያስችላል ብለዋል፡፡

ከዚህ ባሻገር የዲጂታል መገበያያ መንገዶችን በስፋት በመተግበር ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

መንግስት አብዛኛውን የማህበረሰብ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ በማድረግ በአንድ ቦታ ብዙ አገልግሎት የሚገኝበትን መንገድ ለመፍጠር እንቅስቃሴ ማድረጉንም አንስተዋል፡፡

በዚህም መሶብን በመገንባት 12 የሆኑ የፌደራል ተቋማት በአንድ ስፍራ ሆነው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አውስተዋል፡፡

ይህ የዲጂታል ትግበራ ህብረተሰቡን ከመንግስት ጋር ይበልጥ ለማቀራረብና ያለምንም እንግልት በቀላሉ አገልግሎት ማግኘት እንዲችል የሚያደርግ ነው ብለዋል፡፡

በንፍታሌም እንግዳወርቅ

10 last posts shown.