EOTC ቤተ መጻሕፍት


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


ይህ Channel የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍት፤ ስብከትች እንዲሁም የተለያዩ ለአብነት ትምህርት የሚሆኑ በድምፅ ፤ይሁን በጹሁፍ እንዲሁም በ Video ሚለቀቅበት Channl new
ተጨማሪ ወይም ሚፈልጉትን መፃህፍት
ብለው ይጠይቁን
ማስታወቂያም እንሰራለን በውስጥ መስመር ይጠይቁን
የሰማነዉን እንናገራለን!
ያየነዉን እንመሰክራለን!

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ይህ ቻናል በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ስር በሚገኙ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ የሚከበሩ ዓመታዊ የንግሥ በዓላትን የሚገልፅ ነው። 
 
የንግሥ በዓላት የት ደብር እንደሚከቡሩ የሚገልፅ ቻናል ይቀላቀሉን!
👇👇
📎 https://t.me/beale_nigs
📎 https://t.me/beale_nigs




«ዝክረ ኒቅያ» ሀገር አቀፍ የሊቃውንት ጉባኤ ሊዘጋጅ ነው!

የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ /አዲስ አበባ)



በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ ታሪካዊና በዓይነቱ ልዩ የሆነ የተሰኘ ሀገር አቀፍ የሊቃውንት የምክክር ጉባኤ ከሚያዚያ 20 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለማካሔድ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ የጉባኤውን ዓላማ እና ለቤተ ክርስቲያን ያለውን ፋይዳ አስመልክቶ ዛሬ ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሕዝብ ግኑኝነት ጽ/ቤት መግለጫ በሊቃውንት ጉባኤ ተሰጥቷል፡፡

በቀደምት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥያቄዎችና የኑፋቄ ትምህርቶች ሲነሱ መልስ ለመስጠት ሊቃውንቱ ተሰባስበው ምላሽ የሚሰጡ መሆኑንና አሁንም በቤተ ክርስቲያን ላይ በነገረ ሃይማኖት እንዲሁም በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ላይ የተለያዩ ኑፋቄና ቀኖናዊ ጥያቄዎች እየተነሱ በመሆኑ የሊቃውንት መሰባሰብ አስፈላጊ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ 

ጉባኤው ከጥር 26-29 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለማካሄድ ታቅዶ እንቅስቃሴ ሲደረግ የቆየ ቢሆንም፡-

1ኛ) ጉባኤው በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የጉባኤ ቤት መምህራንና ሊቃውንት የሚታደሙበት እንደመሆኑ፥ በተለይ በጠረፉ የሀገራችን ክፍል የሚገኙ መምህራንን በበቂ ቊጥር ለማካተት እንዲቻል ፥ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ ፤

2ኛ) በጥር ወር በርካታ ሀገራዊ ክንውኖችና ሃይማኖታዊ ክብረ በዓላት በየአካባቢው የሚካሄዱ በመሆናቸው የጉባኤው መካሄጃ ጊዜ እንዲስተካከል ከአንዳንድ አህጉረ ስብከት በተደጋጋሚ አስተያየት በመሰጠቱ ፤

3ኛ) ጉባኤው ከዘመናት ቆይታ በኋላ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄድና በቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዮች ዙሪያ ጠቃሚ ውይይቶችን በማካሄድ ፥ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የሚጠቅም የውሳኔ ሐሳብና አስተያየት የሚያቀርብ ፥ አልፎም የአቋም መግለጫ የሚያወጣ መሆኑን  ከግምት ውስጥ በማስገባት የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ከመካሄዱ ጥቂት ቀደም ብሎ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፥ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፥ የጉባኤ ቤት መምህራንና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፥ የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች በሚገኙበት ከሚያዝያ 20-25 ቀን 2017 ዓ.ም. በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሚካሄድ ይሆናል።

በጉባኤው፡- ያለውን ማጽናት፣ የጠመመውን ማቅናት፣ የጠፋውን መፈለግ፣ ሊቃውንቱን እርስ በእርስ ማስተዋወቅና ቤተክርስቲያን ያለችበትን ችግር ቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ እና ብፁዓን አበው በተገኙበት ለምልአተ ጉባኤው ጥያቄ የሚቀርብ እና ምላሽ እንዲሰጥበት እንደሚደረግ ግቡን ማድረጉ ተገልጧል፡፡

ከመላው የሀገሪቱ ክፍል ከተቻለም ከውጭው ዓለም ያሉ የቤተክርስቲያን ሊቃውንት የሚሰባሰቡ ሲሆን በጊዜው በኒቂያ እንደተደረገው በዚህ ጉባኤም 318 ሊቃውንት የሚታደሙ እንደሆነ በመግለጫው ተገልጧል፡፡

በብፁዕ  አቡነ እንድርያስ ሰብሳስቢነት የሚመራው የሊቃውንት ጉባኤ ከ 15 በላይ አባላት ያለው መሆኑ በመግለጫው ላይ ለማስታወስ ተሞክሯል፡፡

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot


ሳይሆን ለመመስገን፣ ለምደነቅ ወይም ለመከበር ተብሎ ስለሚሆን እና እነዚህም ጠባያት ደግሞ የሥጋ ጠባዮች ስለሆኑ እነዚህ መግቢያ አድርጎ ሰይጣን እንዳያስተውም ስለሚፈራ ነው።

ሁልጊዜም ቢሆን በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ችግሮች የሚፈጠሩት ቲኦሎጂን ወይም ነገረ እምነትን ለአማኞች ድኅነት ቅድሚያ ሰጥቶ ማስተማር ቀርቶ የራስን ፍላጎት ለማርካት በሚደረግ አላስፈልጊ ዕውቀት መሰል ክርክር ውስጥ ነው። ይህ ጉዳይ ከዚህም አልፎ ክርክር በማያስነሡ ጉዳዮች እንኳን የሚነሣው የተለየ ነገር ተናግሮ ማስደነቅና መከበርንም ሆነ ሌላ ነገር ሲፈለግ የሚያጋጥም ስለሆነ ነው።

እንዲያውም ከዚህም አልፎ አሁንም ብዙ ገዳማዊያን ሊቃውንት አንድ መሠረታዊ ሥጋታቸውን ደጋግመው ሲያነሡ አይቻለሁ። ይህም አሁን አሁን ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ወደ ዕውቀትነት እያወረዱት ነው የሚል ሥጋት ነው። ይህ ሥጋታቸው ደግሞ ተራ ሥጋት አይደለም። በአሁኑ ጊዜ በርከት ያሉ ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ያጠኑታል፣ ለማወቅ ይጥሩለታል፣ ይወድዱታል፤ በዚያም ደስተኞች ይሆናሉ። ከዚህም የተነሣ ወደ እውነተኛው የመዳን ዕውቅት ሳይሸጋገሩ ልክ እንደ አካዳሚክ ዕውቀት በጥናት ላይ ብቻ ተመሥርተው ይቀራሉ። ይህ ባሕል እየሆነና እየተለመደ ስለሔደ ክርስቲያናዊው እውነተኛው ሕይወታዊውን ዕውቀት አካዳሚያዊ ዕውቀት እየተካው ስለሆነ ክርስትና አደጋ ላይ ነው ያለው ይላሉ። ይህን የሚሉበት ምክንያት ክርስቲያናዊ ዕውቀት ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት በማድረግ ከመነገር በላይ ወደ ሆነው ወደ ሚኖረው ዕውቀት ካልተሸጋገረ አካዳሚያዊ ዕውቀት ይሆናል። ከዚህም የተነሣ እንደማንኛውም አካዳሚያዊ ነገር በሰው አእምሮ መረዳት (reasoning) ላይ ይወሰንና ስፉሕ አእምሮ ያላቸው ሰዎች ሲመጡ ያንን የሚያሻሽሉት የሚያስፋፉት፣ ጠባብ አእምሮ ያላቸው ሲይዙት ደግሞ እንደዚያው የሚያጠብቡት ይሆንና በመጨረሻም በሒደት የመበረዝ ፣ የመለወጥ ፣ የመጥፋት አደጋ ይገጥመዋል የሚል ተጨባጭ ሥጋት አላቸው።

የእኛ ዘመን ተሟጋች ትውልድ ደግሞ አብዛኛው መጀመሪያ የተማረው ዘመናዊውን ወይም ምዕራባዊውን ትምህርት ነው። ይህን አስቀድሞ መማር በራሱ ችግር አይደለም፤ ( ሊሆንም አይችልም። እነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ ባስልዮስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮ ዘእንዚናዙ እና ሊሎችም ጭምር መጀመሪያ የተማሩት የዓለሙን ፍልስፍና ነውና። የእኛ ትውልድ ግን ከመጠን በላይ ሲስተማቲክ በሆነው አካዳሚክስ ውስጥ ከማለፉ የተነሣ ነገሮችን ሳያውቀው በዚያ መጠን የመበየን፣ ጨርሶ የማወቅ እና አቋም መያዝ ድረስ መድረሱ ችግሩ ብቅ እያለ መሆኑን ያመለክታል ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም ክርስትናን ከትምህርት ከሚገኝ መጠነኛ ዕውቀት በሕይወት ወደሚደረስበት የመረዳት ዕውቀት ካልተሸጋገረ ችግር መግጠሙ አይቀሬ ነው። በሰሚዕ የሚገኝ ዕውቀት እና እምነት መግቢያ በር እንጂ መድረሻ አዳራሽ ወይም ቤት አይደለምና።

ይህ ጉዳይ ራሱን የቻለ ብዙ እንድንማማር የሚያደርግ ስለሆነ ጊዜውና ችሎታው ያላችሁ ሁሉ በዚህ ጉዳይ ሰፋ ያለ ዕውቀት ብታካፍሉን ብዙዎቻቸን መንገዳችንን ለማቃናት ብዙ ይጠቅመናል፤ ጉዳዮችን በአካዳሚ መንገድ እና ዓይን ከማየት፣ አለፍ ሲልም እንደ ፖለቲካ አቋምን ከመለካካት ሊያተርፉን ይችላሉ፤ ሲሆን ሲሆን ደግሞ ወደ መንፈሳዊው ዓለም እንድንገባ እና መንገዳችንን ወደዚያ እንድናደርግ ሊረዱን ይችላሉ ብዬ አስባለሁ።

ከሰሞኑ ውይይቶች በተለይ አስተያየት መስጫ ላይ የማያቸው ጥያቄዎች እና መልሶች ብዙዎቹ ትውልዱ ወደዚህ አካዳሚያዊ የነገረ መለኮት ዕውቀት ሳያውቀውም ቢሆን እያደላ መሆኑን የሚጠቁሙ ይመስለኛል። በእኔ መረዳት ኦርቶዶክሳዊ የነገረ ዕውቀት አቀራረብ ቀርቶ ምዕራባዊ የምነለውንና የራሱ ሥነ ሥርዓት ያለውንም ያንን እንኳ የማያሟሉ፣ የነገሮቹን መቅድማቸውን እንኳ በውል ሳናገኘው አንኳር ጉዳዩ ላይ ገብተን እንደዚያ ያለ አስተያየቶች መወራወራችን በእጂጉ ያስፈራል። ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው በእጂጉ ያስፈራል። እኔን እስከገባኝ ደርሰ ከፍተኛ ድፍረት የተሞላው የአላዋቂ ክርክር ወስጥ መሆናችንን በታላቅ ትሕትና (ነገሩ እንኳ ሳስበው ድፍረትም ጭምር ነው) መጠቆም እፈልጋለሁ።

በማኅበራዊ ሚዲያ ልናደርጋቸው የሚገቡንን ውይይቶች እና ትምህርቶች በተመለከተ እኔ ከጠቆምኳቸው እና ከሌሎቹም መሠረታዊ ትውፊቶቻችን አንጻር በማየት በውስጥ መወያየት እና አቀራረቦችን ማስተካከል ይቻላል፤ ይገባለም ብዬ አምናለሁ። አበቃሁ። መልካም ጾም ይሁንልን።

©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot


ኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀትን በተመለከተ

አንድ ወንድም ከቲክታክ ውይይት ሰማሁት ብሎ የጠየቅኝ ጆሮጅዬን ጭው ነው ያደረገኝ። አንዳንድ ተወያዮች እድገት ያመጡ እና ከፍ ያለ ዕውቀት ላይ የደረሱ እየመሰላቸው ነው መሰል በአብና በወልድ መካከል ገብተው ሁሉ አስተያየት እየሰጡ መሆኑን (የጠየቀኝ ሰው ያለኝን ቃለ በቃል መድገም አልፈለግሁም) ከጥያቄው ተረድቻለሁ። ኪሩቤል ቀና ብለው ወደማያዩት ዙፋን፣ ሱራፌል በሁለት ክንፎቻቸው እግራቸውን በሁለት ክንፎቻቸው ፊታቸውን ሸፍነው ሁለት ክንፎቻቸውን ደግሞ ዘርግተው ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ብለው ከማመስገን ውጭ ወደ ማይደፍሯት ዙፋን ወይም ገናንነት መግባት የሚፈልግ ሕሊና በፍጥነት በንስሐ መመለስ አለበት ብዬ አምናለሁ።

አንድ ወንድም አንድ ጊዜ እንዲህ ያለ ነገር ገጥሞት ነበር። ከጓደኛው ጋር ወደ ጎንደር በሔዱበት ወቅት ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራን ሰላም ለማለት በገቡበት ጥያቄ አነሣ። ምሥራቅ ኦርቶዶክሶች በአንድ አካል ሁለት ባሕርይ የሚሉት ባሕርየ ትስብእት ከባሕርየ መለኮት ጋር ከተዋሐደ ፣ ወልድ ደጎሞ በባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ ስለሆነ እንዴት ሊይድርገው ነው ይላሉ ብሎ ይጠይቃል፤ እንደማስታውሰው ነው። ሊቀ ሊቃውንትም እርሱ ከበደኝ አላለ እናንተን ምን አስጨነቃችሁ ብለው መለሱለት ብሎ የነገረኝን ባስታወስኩ ቁጥር እደነቃለሁ። (በአጻጻፍ የሳትኩት ካለ ሓላፊነቱ የእኔ ነው)። መልሱ ሁልጊዜ ያስደስተኛል። ምክንያቱም በሥላሴ አንድነት ውስጥ ገብታ ቦታ ለማካፈል የምትደፍር ኅሊና እንዴት ያለች ደፋር እና አላዋቂ ናት በእውነት ። ሙሴ እንኳ ወደ ዕፀ ጳጦስ ለመጠጋት ጫማውን እንዲያውልቅ ታዝዞ ነበር። የቀረበውም በረዓድ እና በመንቀጥቀጥ ነበር። ምሳሌው ለተመረጠው ለሙሴ እንኳ እንዲያ የሚያስፈራ ከሆነ አማናዊው የተዋሕዶ ምሥጢርም ይልቁን ምን ያህል ትሕትና እና ጥንቃቄ ይፈልግ ይሆን?

የተገለጠና እና በትክክል የምናውቀው እንኳ ቢሆን እንዲህ ያለው ይዘት በፍጹም ለማኅበራዊ ሚዲያ የሚሆን አይደለም። እውነቱን ለመናገር “የተቀደሰውን ለውሾች አት ስጡን” ለምን አንጠብቀውም የሚለውን እጠይቅና የተቀደሰውን ስለማናውቀው ይሆናል በሚል መልስ እንደገና እቆማለሁ። በርግጥም የምናውቀው አይመስለኝም። ይህ ሁሉ እንግዲህ ኦርቶዶክሳዊውን ነገረ ዕውቀት በመጠቆም ለማሳሰብ እንደ መግቢያ ያነሣሁት ነው።

ሴባስቲያን ብሮክ የሚባለው የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የኦሬንታል በተለይም የሶርያ ኦርቶዶክስ አባቶችን ጽሑፎች በተመለከተ ብዙ ካጠና በኋላ ሀሳቦቹን ካጋራባቸው መጻሕፍት አንዱ ሰሞኑን በሕሊና በለጠ ብርህት ዓይን ተብሎ የተተረጎመውን The luminous Eye የተባለ መጸሐፍ ጽፏል። ብሮክ በዚህ መጽሐፉ ካነሳቸው መሠረታዊ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የምሥራቃውያን (ኦሬንታል) አባቶች ትምህርታቸውን እንደ ምዕራቡ በነገረ ጉዳይ የተደራጀ (Systematic) ለምን አላዳረጉትም የሚለው ይገኝበታል። (ይህን ስጽፍ መጽሐፉን እያየሁ ስላልሆነ በትክክል ባልገልጸውም አሁን) እርሱ የሚለው የኦሬንታል ሊቃውንት የምዕራብ ሊቃውንት ያደረጉትን ማድረግ ስለማይችሉ ወይም አቅም ስለሌላቸው ሳይሆን ስለኦርቶዶክስ ነገረ ዕውቀት ባላቸው መረዳት ምክንያት ነው። ለምሳሌ የምዕራብ ሊቃውንት አንድን ጉዳይ ብያኔ (definition) ሰጥተው ይጽፋሉ። ለምሥራቃውያን ደግሞ ብያኔ ችግር ያመጣል።

ምክንያቱም መበየን ማለት ለነገሮች ድንበር መሥራት፣ መከለል፣ መለየት፣ መወሰን ማለት ነው። ነገረ ሃይማኖት ደግሞ ለሰው ልጅ አእምሮ በሚመጥን ከእግዚአብሔር የተገለጠ መለኮታዊ ሀሳብ ነው። ያን መልኮታዊ ሀሳብ ደግሞ ጥልቀቱን መወሰን እና ለዚያም ድንበር ማበጀት አይቻልም። የሰው ቋንቋም ለሰው ማስረዳት ቢችልም ነገረ አምላክን ወስኖ መያዝ ግን አይችልም። ስለዚህ እግዚአብሔር በገለጠልን መጠን እናብራራዋለን (እንተረጉመዋለን) እንጂ ልንወስነው ወይም በብያኔ ልንዘጋው አንችልም የሚል እምነት ወይም አረዳድ ስላላቸው ብያኔ እና ብያኔያዊ አካሔድ አይጠቀሙም የሚል ማብራሪያ ይሰጣል። ይህን ሀሳብ በየንታ እሸቱ ርጢን መጽሐፍ መቅድም ላይ ለመጠቆም ሙከራ አድርጊያለሁና ያንንም ማየት ይቻላል።ይህን እውነታ ከእኛም ሆነ ከሌሎች የኦሬንታል አብያተ ክርስቲያን ትውፊት መረዳት ይቻላል።

ኦሬንታሎቹን ብቻ ሳይሆን እኔ እስካየሁት ድረስ ምሥራቅ ኦርቶዶክሶችን ከምዕራቡ (ከካቶሊክም ከሮቴስታንትም) ከሚለዩን መሠረታዊ ነገሮች አንዱ ይህን የሚመለከት ነው።
ሌላውና መሠረታዊው የኦርቶቶዶክስ ነገረ ዕውቀት የሚያጠነጥነው ደግሞ መገለጥ ላይ ነው። መገለጥ በሁሉም ክርስቲያኖች ዘንድ ተቀባይነት ያለው ቢሆንም በሮማ ካቶሊክ በተለይም ደግሞ ከቶማስ አኲናስ መምጣት በኋላ (በእምነት መግለጫዋ ላይም እንዳለው) የሰው አእምሮ ወይም የመረዳት ችሎታ (reason) ብቻውን እግዚአብሔርን በርግጠኝነት ለማወቅ በአጠቃላይ ሃይማኖትን ለማወቅ በቂ ነው ብለው ያምናሉ። (ይህን ሀሳብ Thinking Orthodox እና የመሳሰሉትን መጻሕፍት አንብቦ የበለጠ መረዳት ይቻላል።)

በሁለቱም ኦርቶዶክሶች ግን ይህ ሀሳብ ተቀባይነት የለውም። እንደዚህ ከሆነ ሃይማኖት ከሳይንስ የሚለይበት መሠረታዊ ነገር ይጠፋል ወይም ያንሣል። ይህን ጉዳይ አሁንም በስፋት መግባት ባልፈልግም ኦርቶዶክሳዊው ነገረ ዕውቀት ከዚህ በጅጉ የራቀ እና የተለየ መንገድ ያለው ነው። ምንም እንኳ ሲስተማቲክ ቲዖሎጂ በእኛም ተቋማት እየተሰጠ እና በዚሁ መንገድ መጻሕፍት እየተጻፉና እየተዘጋጁ ቢሆንም መሠርታዊ ጥንቃቄ እና ኦርቶዶክሳዊውን ድነበር መጠበቅ ግን በብዙ የምሥራቅ ሊቃውንት ዘንድ የታወቀ ብቻ ሳይሆን የተለመደም ጭምር ነው።

በኦርቶዶክሳዊያን ዘንድ ደግሞ በሰው አእምሮ አድሮ የሚናገረው ራሱ እግዚአብሔር ነው። ይህም በጥልቅ መግቦቱ ለሰው ልጆች በመግለጥ የሚያሳየው ነው። ሰዎች በቅጥነተ ኅሊና ማለትም አእምሮአቸውን በማራቀቅ ብቻ ሊደርሱበት የሚቻላቸውም አይደለም። ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ምእመናን “እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ የሥጋ እንደ መሆናችሁ፥ በክርስቶስም ሕፃናት እንደ መሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደ መሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልሁም። ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበርና ወተት ጋትኋችሁ፤” /1ኛ ቆሮ 3 ፤ 1 – 2/ የሚላቸው በክርስትና ለመንፈሳዊ ሕይወት ሕጻናት ስለሆኑ እንጂ ለእውቀት ለፍልስፍና እና ለአመክንዮ ሕጻናት ሆነው አልነበረም ባዮች ናቸው። ስለዚህ በመንፈሳዊ ሕይወት በተጋድሎ ውስጥ በምትገኝ የማትቋረጥ መገለጥ የሚሰጥ እንጂ የሰው አእምሮ የማሰብ ችሎታ ብቻውን ይደርስበት ዘንድ አይቻልም ብለው ያምናሉ። በተለይም ደግሞ መጀመሪያ ቅዱስ ወግሪስ እንደተናገረው የሚታመነው “እውነተኛ የነገረ ሃይማኖት ዐዋቂ የሚጸልይ ሰው ነው” የሚለው አባባል የሰው የሃይማኖት ዕውቀት የመረዳት ችሎታ ላይ እንዳያርፍ መጠበቂያ አጥራቸው ነው።

የኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀት ሦስተኛው መሠረታዊ መለያ ደግሞ ሃይማኖታዊ ዕውቀት በመሠርቱ ለሰዎች ድኅነት ቅድሚያ የሰጠ (Pastoral) መሆኑ ነው። ይህም ማለት ጉዳዮች የሚብራሩት የሚተረጎሙት የሚሰበኩት የሰውን ድኅነት ቅድሚያ ሰጥተው እንጂ ለዕውቀት እና ለርቃቄ ተብለው አይደለም። ከዚህ የተነሣ ለድኅነት ከሚጠቅመው ውጭ እንኳን እንዳሁኑ ማንም ሊያየው በሚችል ሚዲያ ይቅርና ለኦርቶዶክሳዊያን ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን የጉባኤ ቀለም ለመናገር እና ለማራቀቅ የሚደክም የለም፣ ሲያጋጥምም አይመሰገንም። ምክንያቱም ለድኅነታቸው


እነዚህ አጋጣሚዎች ለእኔ እጅግ አስተማሪዎች ነበሩ። እውነት ለመናገር ስለሌሎች ከመናገር በፊት እነዚያ አካላት የሚሉትን በትክክል ማወቅ በእጂጉ አስፈላጊ መሆኑንና ስለተለያዩ ብቻ እያነሡ መለጠፍ፣ እንደ ልብ መናገር በጣም አደገኛ መሆኑን የተማርሁት ይህን ከመሰሉ ስለእኛ ከተነገሩ እጂግ የተሳሳቱ ትምህርቶች ፣ ጽሑፎች እና አመለካከቶች ነው። ከዚያም ወዲህ ትላልቅ የሚባሉት የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት ጽሑፎች ውስጥ ሳይቀር ይህን የመሰለውን ስለእኛ ያላቸውን የተሳሳተ እምነታቸውን ሳይ በእጂጉ አዝናለሁ፤ በዚያ ምክንያትም የሥራዎቻቸውን ደኅና ነገር ሁሉ በዚያው ዓይን እያየሁ እንድጠራጠራቸው እሆናለሁ።

ይህን ሁኔታ በሌሎችም አይቻለሁ። በተለይ በእስልምናው ሐዲዝ ላይ እኛን መነኮሳቶቻቸውንና ሊቃውንቶቻቸውን ያመልካሉ ብለው የጻፉት ሁልጊዜ ሲያስቀኝ እና ሲያስገርመኝ ይኖራል። እንዲህ ያለው ችግር በርግጥ በእኛም ዘንድ አለ። በተለይ ካቶሊኮች እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚለው አሳፋሪ ነገር እስካሁንም የሚናገሩት ሞኞች አሉ። በነገራችን ላይ ለእመቤታችን ወላጆች በተለይም ለቅድስት ሀና ብዙ ቤተ ክርስቲያን በመሰየም የካቶሊኮችን ያህል የሚኖር አይመስለኝም። ተመልከቱ እንግዲህ ይህ ሁሉ ባለበት ነው እመቤታችንን ኃይል አርያማዊት ናት ይላሉ የሚል የስሚ ስሚ ወሬን በአደባባይ ሳይቀር በድፍረት እንናገር የነበረው።

ዋናው የፈለግሁት ነገር ሌሎች እኛ ያልሆንነውን ብለዋል ሲሉ እኛን የሚሰማንን ያህል ወይም ከዚያም በላይ የናም የግምት ንግግር ሌሎቹንም ልክ እንደእኛ እንዲሰማቸው ያደርጋል። በግሌ ስለሌሎች በድፍረት መናገር ምን ያህል ስሐተት እንደሆነ እና እኔን የእነርሱ ደጋግሞ እንደሚያሳዝነኝ እነርሱንም የእኛ እንዲህ ሊያደርጋቸው እንደሚችል እና ስለማንኛውም አካል ስለምንናገረው ነገር በእጂጉ መጠንቀቅ እንዳለብኝ የተማርኩት ከእነዚህ አጋጣሚዎች ነበር።
የሚያሳዝነው ግን አሁንም እየሆነ ያለው እንደዚያው መሆኑ ነው። አሁንም ሰዎች ራሳቸው ስለሚያምኑት ነገር ከሰዎቹ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የሚያምኑት እያሉ መናግር እጂግ በጣም አደገኛ ስሕተት ነው። የተጠራጠረ ሰው ማድረግ ያለበት መጠየቅ ነው። ከዚያ ራሳቸው የተጠየቁት አካላት እምነታቸውን አስተሳሰባቸውን አረዳዳቸውን በግልጽ ያስረዱ። እዚይ ላይ ምን ለማለት እንደፈለጉ ደጋግሞ እየጠየቁ ማጣራት እና በትክክል መረዳት መቅደም አለበት ። ካለበለዚያ ዲዮስቆሮስ አውጣኪያዊ ነው ብለው እስካሁን በስሕተት እንደሚያምኑት እና ስለማናምነው ነገር ከእኛ በላይ ሆነው እንዲህ ነው የምታምኑት እንደሚሉን አንዳንድ ምሥራቃውያን ከመሆን የዘለለ ጠቀሜታ የለውም።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot


ስለሌሎች ስንናገር

ስለኦርቶዶክሳዊ ነገረ ዕውቀት የገባሁትን ቃል አልረሳሁትም። ነገር ግን ይህች ብትቀደም ወደድኩ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ወደ ግሪክ በሔዱበት ወቅት የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የእኛ ፓትርያርክ ቀድሰው አማኞቻቸውን ያቆርቡበት ዘንድ አንድ ቤተ ክርስቲያን በውሰት ይሰጣሉ። የታሰበው አገልግሎት የተፈጸመበትን ይህን ቤተ መቅደስ ግን ግሪኮች ከዚያ በኋላ አልተጠቀሙበትም። እንደተዘጋ ትተውት ቀሩ እንጂ። ይህን ያደረጉበት ምክንያት ደግሞ ኦሪንታል ኦርቶዶክሶች አውጣኪያውያን ናቸው፤ ስለዚህ እነርሱ አርክሰውታል ብለው በማመን ነው። ይህን የሰማሁት የዛሬ 16 ዓመት ወደ ግሪክ ለአገልግሎት ብቅ ባልኩበት ወቅት እዚያው ግሪክ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ነበር።

ግሪኮች ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ምሥራቅ ኦርቶዶክሶች ስለኦሬንታል ኦርቶዶክሶች የነበራቸው አመለካከት ወይም እምነት ይህ ነበር። ይህ የሆነበት ምክንያትም በ448 ዓ.ም. በአውሳብዮስ ከሳሽነት በፍላብያኖስ ዘቁስጥንጠንያ መሪነት ወደ 40 የሚጠጉ ሊቃነ ጳጳሳት ተሰብስበው ነበር። ክስሱ አውጣኬን ባሕርየ መለኮት ባሕርየ ሥጋን ዋጠው መጠጠው ስለዚህ አንድ ንጥል ባሕርይ (Monophysite) ነው ብሎ አስተምሯል የሚል ነበር። በርግጥ ቀጥታ የተጠየቃቸው ጥያቄዎች ሌሎች ነበሩ። በጉባኤው ላይም አውጣኬ በአካል አልተገኘም ነበር። ላቲኖች እንደሚሉት ከሆነ ያልተገኘው የገዳም አበምኔት እንደመሆኑ መጠን በዓቴን ለቅቄ አልወጣም በማለቱ ነበር። በዚህም ምክንያት ይህን ታምናለህ አታምንም እየተባለ የተጠየቀው በመልእክተኞች ሲሆን መልእክተኞቹም ዮሐንስ የሚባል ቄስ እንድርያስ እና አትናቴዎስ የሚባሉ ዲያቆናት እንደነበሩ መዝግበዋል። እነርሱን ወደዚህ ድምዳሜ የወሰዳቸው ግን ጌታ ሰው ከሆነ በኋላ ሁለት ባሕርይ መሆኑን ታምናለህ? ተብሎ ሲጠይቅ እኔ እንዲህ አልልም ቅድመ ተዋሕዶ እንጂ ደኅረ ተዋሕዶ እንደ ቄርሎስ አንድ ባሕርይ እላለሁ እንጂ ሁለት አልልም በማለቱ እነርሱ ሁለት አልልም አንድ እንጂ ካለ አንደኛው ባሕርይ ጠፍቷል ማለቱ ነው የሚል ትርጉም ራሳቸው ሰልሰጡ ነበር። በዚህም ላይ የጌታ ሰውነት እንደ እኛ አይደለም ብሏል ብለው ዲያቆናቱ የሰጡትን ምስክርነት ይዘው ነበር ያወገዙት፤ እንዳነበብኩት።

አውጣኬ ደግሞ እኔ እንደዚህ ብዬ አላስተማርኩም፤ ያወገዙኝ ያለአግባብ ነው ብሎ ለንጉሡ ቴዎዶስዮስ ካልዓይ ክስ አቀረበ። ንጉሡም የእስክንድርያው ፓትርያርክ ዲዮስቆሮስ ባለበት እንዲታይለት እርሱን በማወገዝ ግንባር ቀደም የነበሩት እና ልዮን፣ ፍላብያኖስ እና ሊሎች አራት ያልህ ደግሞ በዳኝነት በዚህኛው ጉባኤ እንዳይሰየሙ አዘዘለት ። ቅዱስ ዲዮስቆሮስም ሊቃነ ጳጳስት እና ሊቃውንት ተሰብስበው የአውጣኬ ክስሱ እንዲሰማ እና የርሱም መልስ እንዲደመጥ በ449 ዓ.ም. ጉባኤ ጠራ። በጉባኤውም ወደ 127 ጳጳሳትና ሊቃውንት ተገኙ። አውጣኬን እንዲወገዝ ያስተባበሩት እነ አውሳብዮስ ፣ ፍላብያኖስ ግን ቢጠሩም ሳይገኙ ቀሩ። ጉባኤው ግን ተካሔደ። አውጣኬም ተጠየቀ። እርሱም እነርሱ ያወገዙኝ እኔን ብሏል የሚሉትን አላልኩም፤ እኔ አንድ ባሕርይ ነው ብዬ አምናለሁ። እምነቴ ቄርሎስ እንዳስተማረው እንጂ እነርሱ እንደሚሉት አይደለም ብሎ ቃሉን ሰጠ። በዚህ ምክንያት ይህ በቅዱስ ዲዮስቆሮስ የሚመራው ጉባኤ አውጣኬን ከግዝቱ ፈታው።

በዚህ ጊዜ ቀድመው ያወገዙት ሰዎች ዲዮስቆሮስ አውጣኬን ከግዝቱ የፈታው ራሱ ዲዮስቆሮስ እንደ እርሱ ቢያምን ነው ብለው ማስወራት ጀመሩ። እንዲያውም ልዮን ይህን ጉባኤ የሚጠራው ጉባኤ ፈያት እያለ እንደነበር ጽሑፍ ማንበቤን አስታውሳለሁ። አስወርተውም አልቀሩ የ451ዱ ጉባኤ ኬልቄዶን እንዲጠራ እና ሀሳቡ እንኳ በአግባቡ ሳይደመጥ ዲዮስቆሮስ እንዲወገዝ ተደረገ። በዚህ ምክንያት እስከቅርብ ጊዜያት አንዳንዶቹም እስካሁን ድረስ ኦሬንታሎቹን አውጣኬያውያን እንደሆንን ያምናሉ። የሚያስገርምም የሚያሳዝንም ነገር ነው።

አንዳንዶች ሀሳባቸውን በታወቀ መንገድ መቀየር እና ማስተካከል የጀመሩት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ (አሁን ዩኒቨርሲቲ) የመጀመሪያው ዲን የነበሩት ሕንዳዊው V.C. Samuel የተባሉት ሊቅ ለሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጥናታቸው መጽሐፍ ሆኖ ከታተመ በኋላ ነበር። የኒህ አባት መጽሐፍ “the Council of Chalcedon Re-Examined” – ‘ጉባኤ ኬልቄዶን እንደገና ሲመረመር’ በሚል ርእስ በሠሩት ጥናት ላይ ይህን ንጥል አንድ ብቻ ባሕርይ /monophysite/ የሚለውን እንኳን ዲዮስቆሮስ ሊቀበለው ይቅርና አውጣኬም ስለማለቱ ማረጋገጫ አላቀረባቸሁም። እርሱ ያላለውን ብሏል ብላችሁ አወገዛችሁት እንጂ እርሱ እንዲህ ነው የማምነው ብሎ ልክ አርዮስ፣ ንስጥሮስ፣ መቅዶንዮስ እንዳደረጉት አልተከራከረም ፤ ሀሳቡንም አላስረዳም። እርሱ እናንተ የምትከስሱበትን ለማለቱ ማስረጃ የላችሁም። አላልኩም ፤ እኔ የማምነው እንደ ቄርሎስ ነው ስለማለቱ ግን ማስረጃ አለ። ኦሪነታሎች አንድ ባሕርይ የሚለውን የምንጠቀመውም በተዋሕዶ እንጂ እናንተ እንደምትሉን ሞኖፊሳይት አይደለንም፤ አይመለከተንም፤ ይህን ለማረጋገጥ ከፈለጋችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስሟን ብቻ ብትመለከቱ ይበቃችኋል። ተዋሕዶ የሚለውን የስሟ መጠሪያ አድርጋዋለችና የሚለውን ሀሳብ በሰፊ ጥናት ካሳዩ በኋላ ብዙ ሊቃውንቶቻቸው ስለኦሬንታሎች ያላቸውን የተሳሳተ አመለካከት አስተካክለዋል።

በቅርብ ጊዜ ደግሞ የእኛው ቀሲስ ዶክተር መብራቱ ኪሮስ የማስተርስ ጥናቱን በዚህ ዙሪያ በመሥራት የኦሬንታሎቹ እምነት ምሥራቆቹ እንደሚሉን እንዳልሆነ ጥሩ አድርጎ አስረድቷል። የቀሲስ ዶክተር መብራቱ ትኩረቱ ታሪኩ ላይ ሳይሆን ቀጥታ ነገረ እምነታችን ወይም ዶክትሪኑ ላይ ነው። የቀሲስን ጥናት የፈለገ “Miaphysite Chrystology: An Ethiopian Perspective” በሚል ረእስ አፈላልጎ ማግኘት እና ማንበብ ይቻላል። እነዚህን ሁለቱን እንደምሳሌ አነሣሁ እንጂ ሌሎችም ይኖራሉ።

ይህም ሆኖ ብዙዎች ገዳማውያኑ እና ዓለም አቀፍ ጥናቶችን ለማወቅ ወይም እኛን ኦሬንታሎችን ቀርበው እምነታችንን በትክክል ያልተርዱት ግን እስካሁን ድረስ እኛን የሚያዩን አውጣኬያውያን አድርገው ነው። እንዲያውም አንድ ወንድም እንደ ነገረኝ በአቶስ ተራራ (Mount Athos) የኖሩት እና አሁንም ያሉት በኃይለኛ ምናኔ እና ብቃት የሚመሰገኑት የግሪክ ኦርቶዶክስ አባቶች እስካሁን ድረስ ኦሬንታሎችን አጥፋ የሚል ጸሎት ሁሉ አላቸው ብሎ ነግሮኛል። እኔም ራሴ ባለፈው ዐሥር ዓመት ውስጥ አሜሪካን ሀገር ያለ አንድ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መካነ ድር ላይ የአውጣኬን እምነት የያዙ ቤተ ክርስቲያኖች አሁንም አሉ፤ ለምሳሌ የኮፕቲክ እና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ብሎ ጽፎ አንብቤ እንዴት በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች በቀላሉ መረጃ በሚያገኙበት እንዲህ ትጽፋለህ ብዬ ጽፌለት ጽሑፉን የጻፈው ቄስ ይቅርታ ጠይቆ አስተካክሏል።


ከዚህም ብዙ ቁምነሮችን የምናገኝ ይመስለኛል። ይኸኛው እንደ ቅዱስ ቄርሎስ ሳይጠነቀቅ እዚያው ፊት ለፊት ካህኑን ገጥሞታል። መልአኩ ደግሞ ምን ያህል ጊዜ እንደታገሰው እና እንደጠበቀ እናስተውል። መልአኩ እንዳለው ሰዎች ከስሐተታቸው በሌሎች ሰዎች ሲታረሙ ማየት እግዚአብሔርንም መላእክትንም የሚያስደስት መሆኑ አስገራሚ ነው። ያም በመሆኑ ደግሞ እግዚአብሔር ለመጀመሪያው አባት ቅዱስ ቄርሎስን ለዚህ ካህን ደግሞ አዋቂ ዲያቆን አዘጋጀ። ስሕተት ደግሞ የማትገባበት ጊዜ እና ቦታም እንደሌለ የምትምረውም የሰው ዓይነት እንደሌለ ከታሪኮቹ መረዳት ይቻላል። ከዚህ ታሪክ ሌሎች ብዙ ነጥቦችንም መውሰድ እንችላለን።  እንደላይኛው ሁሉ መልአክ ተገልጾለት የሚነጋገር አባት ሳይቀር ሊስት የኑፋ/ቄ ቃላትንም ሊጠቀም መቻሉ እንደተጠበቀ ሆኖ ነገረ ግን ሰውየው ውስጡ እምነቱና ሀሳቡ ኑፋቄና ተንኮል ከሌለው እግዚአብሔርም ይታገሰዋል። ቀኑንም ጠብቆ የሚያርመውንና የሚያስተምረውን ሰው ይልክለታል። ከሁሉም በላይ ደግሞ እግዚአብሔር ደስ የሚሰኘው በሌላ ሰው ስንስተካከል ነው። ለዚህ አባት የተላከለትም ከእርሱ በላይ የበቃ አባት ሳይሆን ከእርሱ በሥልጣነ ክህነትም የሚያንስ ዲያቆን ነው። ዲያቆኑን ተጠራጥሮ አልቀበለም ሲል ደግሞ መልአኩ ተገልጾ ማረጋገጫ የሰጠው ከእኛ ያንሳሉ ብለን ከምናስባቸው ሰዎችም ቢሆን ሰምተን እንድንታረምና እንድንሰተካከል ጭምር ነው።

በሰው መታረምን በተመለከተ ደግሞ ሌላ ታሪክ ልጨምር። ቃለ እግዚአብሔርን ከምጠያየቃቸው እና ከምጫወታቸው አንዱ የሆነው  መምህር በረከት አዝመራው ካነበበው የትርጓሜ መጽሐፍ የነገረኝ ነው።  ሙሴ ደብረ ሲና ወጥቶ ሲመለስ እሥራኤል ጣዖት አቁመው ሲሰግዱ አግኝቷቸው እነዚያን ጣዖት የሚያመልኩትን እንዲገደሉ አዝዞ በወገኖቻቸው ተገድለዋል። እርሱ እንደነገረኝ መተርጉማኑ አንድ ጥያቄ አንሥተው ይመልሳሉ። እግዚአብሔር እነዚያን ጣዖት አምላኪዎች እንደ ፈርዖን ለምን ራሱ አላጥፋቸውም ወይም ለምን ራሱ አልቀሰፋቸውም? በሙሴ ትዕዛዝ በራሳቸው ወገኖች እንዲገደሉ ለምን አደረገ የሚል ጥያቄ ያነሡና ይመልሳሉ።

እግዚአብሔር ራሱ ሳያጠፋቸው በራሳቸው ወገኖች እንዲገደሉ ያደረገው ስለሁለት ምክንያት ነው። የመጀመሪያው እሥራኤል ታሪካቸው እግዚአብሔርን ክዶ ጣዖት ማምለክ ብቻ ሳይሆን ጣዖት አምላኪዎችንም የማጥፍት ታሪክ እንዳላቸው እንድናውቅ ነው። ሁለተኛም ከላይ እንዳልነው የሰው ስሐተት በሰው ሲታረም እግዚአብሔር ደስ ስለሚለው ነው የሚል ነው። ከላይ ባየነው ታሪክ መልአኩም ያለው ይህንኑ ነው።

ከዚህም ጋር በሁለቱም አባቶች ታሪክ ላይ አንድ ሌላ መሠራታዊ ትምህርት እናገኛለን። ይኸውም ሰዎች በሚሳሳቱ ጊዜ በሁለንተናቸው ኦርቶዶክሳዊ ሆነው የሆነ ኑፋቄያዊ ቃላት እና ሀሳብ ባገኘንባቸው ጊዜ መማማሩ እንዳለ ሆኖ ልናደርገው የሚገባን ጥንቃቄ ፣ ከበሬታ ፣ ልናሳያቸው የሚገባው ፍቅር ተገልጾልናል። ያን አባት ያረመው ያ ዲያቆን በእኛ ዘመን ቢሆን ኖሮ እንኳን በዚያ አባት በመልአኩም ሊናደድ የሚችል ይመስለኛል። ለምን ሳይቀስፈው ብሎም መልአኩንም የሀሳቡ ተባባሪ አድርጎ ሊቆጥረው ይችላል። (ይህን የምለው ስለእኛ ሕሊና መሆኑ ሳይረሳ) ምክንያቱም የእኛ ዘመን አንዱ ትልቁ ድክመታችን የመጨረሻ ፍርድ ሁሉ ሰጭዎች መሆናችን ነውና።

ማጠቃለያ

እንዲህ ያሉ ነገሮች ለምን ተነሡ? ምን ሲል እንዲህ ተባለ? ለምን እነእገሌ እንዲህ ይላሉ? ... ለምን ዝም ይባላል? የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ማቆም ይኖርብናል። በየትኛውም ዘመን በየትኛውም መዓርግ ባለ መንፈሳዊ ሰውም ላይ ብዙ የምናውቃቸውም የማናውቃቸውም ስሐተቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ መረዳት ተገቢ ነው። እባብ ያዬ በልጥ በረዬ የሚባልላቸው መሆንም የለብንም። እንዲያውም እንዲህ ዓይነት ታሪኮች ሁልጊዜም ማስተማሪዎች በመሆን አንዱ የእግዚአብሔር የመግቦት መገለጫዎች፣ የየዘመኑን ሰው ማንቂያዎች፣ ወዳጆቹንም መጠበቂያዎች (በተለይ ከትዕቢትና ኩነኔ ከሚያመጣ ጥፋት) ናቸው። ዋናው የሚያስፈልገን ነገር ከሁሉም ነገር እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው፣ እኛ ውስጥ ሊያርመው የፈለገው ነገር ምንድን ነው የሚለው ጥያቄ መሆን አለበት ። ካስተዋልን ሁላችንም የየራሳችንን ስሐተቶች የማየት እና የመታረም ዕድል እናገኝበታለን።

ማር ይስሐቅ መላእክትን ለማየት ከበቃ ሰው ይልቅ የራሱን ስሕተት ለማየት የበቃ ሰው የበለጠ ብቃት ደረጃ ላይ ደርሷል ይላል። ቅዱሱ አባት መላእክትን የሚያይ የውጭ ዐይኑ የተከፈተለት ነው፣ የራሱን ስሕተት የሚያይ ግን የውስጥ ዓይኑ የተከፈተለት ነውና እርሱ የበለጠ በቅቷል እንዳለ ወደ ሰው ስሕተት ከማየት ይልቅ ወደራሳችን ስሐተት ማየት ኦርቶዶክሳዊም መንፈሳዊም መንገድ መሆኑን እናስተውል። በዚህ ጽሑፍ ላነሣቸው ያልፈልኳቸው ብዙ ድክመቶች እንዳሉብን ይሰማኛል። ለሁላችንም የሚጠቅመን ግን የራሳችን ስሐተት ማየት እንጂ የሌሎቹ ላይ ማፍጠጥ እና ከፍ ዝቅ አድርጎ መናገርም ሆነ መጻፍ አይደለምና አጥብቀን እንታረም። ይልቁንም ያለነው በዐቢይ ጾም ዋዜማ ላይ ስለሆነ በቀሩን ቀናት ይቅርታ ተጠያይቀን ከቡድነኝነት፣ ከተሳሳቱ ግምቶች እና ግምታዊ ንግግሮች፣ ከፍረጃ እና ከአጸፋዊ ፍረጃ፣ በማናውቀው እና በማይገባን ነገር ከመነጋገር ወጥተን ወደ መንፈሳዊ ድንኳናችን እንሰብሰብ። ያን ጊዜ ስሕተቶቻቸን ይታዩናል። ለሰዎችም ፍቅር ሐዘኔታ የተመላ የማስተካከያ መንገድ ይገለጽልናል።  እግዚአብሔር ቢፈቅድ ስለኦርቶዶክሳዊ ነገር ዕውቀት ትንሽዬ ማስታወሻ ለጾም ቅበላችን እጨምራለሁ፤ መልካም ጾም ያድርግልን። ልዑል እግዚአብሔር ከሚታወቅም ከማይታወቅም ስሐተት ሁላችንንም በቸርነቱ ይጠብቀን፤ አሜን።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


#እመቤታችን_ጥንተ_አብሶ_ከሌለባት_ለምን_ሞተች?

"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአፅብ ለኩሉ"

"ሞት ለሟች ይገባል
የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ይደንቃል!!!" ፤ ደራሲ፡፡

ሞት በአዳም በደል ምክንያት የመጣ ዕዳ ነው፤ባህርያዊ ሳይሆን ባህርያዊ መስሎ ከባህርያችን ጋር ተስማምቶ የሚኖር ፍዳ ነበር፡፡ ሞት ጌታችን ሳይገድለው/ሳይሽረው በፊት ወደ ሲኦል መውረጃ መንገድ ነበር፤
ለአጋንንት እግር እርግጫ፤ ለመንጸፈ ደይን ተመቻቻተን የምንሰጥበት ሂደት፤ሥጋ በመቃብር የሚፈርስበት፤ነፍስ በሲኦል የምትሰቃይበት ክስተት ነበር፡፡

👉ክርስቶስ ሲመጣ ግን ይህ ሞት የሚለው ንባብ ሳይቀየር ትርጉሙና ምሥጢሩ ተቀየረ፤መጠጫው ጽዋው ሳይቀየር መጠጡን እንደመቀየር ነው፤መሞት በሐዲስ ኪዳን መሻገር ነው፤ወደ ዘለዓለም ሕይወት መጠራት፤መቃብርም ለትንሣኤ ዘጉባኤ መቆያ ስፍራ ነው፡፡

👉እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለምን ሞተች? ሞት የጥንተ አብሶ ውጤት ከሆነ እመቤታችንም የሞተችው ጥንተ አብሶ ስላለባት ነው ብለው የሚከራከሩ ወገኖች አሉ፤

አነዚህ ሰዎች በሐዲስ ኪዳን ሞት ምን እንደሆነ ያለመረዳታቸውና እንዲሁም የእመቤታችን ሞት ምክንያቱ ምንድነው የሚለውን ባለማወቃቸው ምክንያት የሚናገሩት ነው፡፡

ሞት ጥንተ አብሶ ያለበት ብቻ ነው የሚሞተው ከተባለ ጌታችን ራሱ መሞቱ ጥንተ አብሶ ስላለበት ነው ያሰኛል፤ ይህ ደግሞ እርሱ ንጹሕ ሆኖ ሳለ ስለእኛ ሞተ የምንለውን የድኅነት ፅንሰ ሀሳብ ከንቱ ያደርግብናል፤ስለዚህ ሞት ከክርስቶስ በኋላ የመብቀል ሂደታችን መሆኑን እንመርምር፡፡

ይህን ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይነግረናል:—
"አንተ ሞኝ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም"፤ይላል 1ኛ ቆሮ 15፡36፡፡
ሰለዚህ ሞት በሐዲስ ኪዳን ሕያው ለመሆን የምናልፍበት ሂደት (process) ነው፡፡

ራሱ ጌታችንም ሲያስተምረን:—

"እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘለዓለም ሕይወት አለው፤ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም"፤ዮሐ 5፡24፡፡

ዳግመኛም ፦ "እውነት እውነት እላችኋለሁ ቃሌን የሚጠብቅ ቢኖር ለዘለዓለም ሞትን አያይም" ብሏል፤ዮሐ 8፡51፡፡

ይህም ማለት ነፍስ ከሥጋ አትለይም ማለት አይደለም፤እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ ነፍስ በገነት እንደምትኖር፤ ከዚያም በትንሣኤ ዘጉባኤ ጊዜ ነፍሳችን ከሥጋችን ጋር ተዋሕዳ ተነሥተን ከመላእክት ጋር እያመሰገንን የምንኖረውን ዘላለማዊ ሕይወት ለመግለጽ እንጂ፡፡

👉እመቤታችን ቃሉን በመስማትና በማመን በመጠበቅ የመጀመሪያዋና ተወዳዳሪም የሌላት ናት፤ ማንም ሊሰማው የማይችለውን "ቃል ሥጋ ኮነ" ን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማች መስማት ብቻ ሳይሆን ያመነች ናት፤ቅድስት ኤልሳቤጥ "ወብፅዕት አንቲ እንተ ተአምኒ ከመ ይከውን ቃል ዘነገሩኪ እምኀበ እግዚአብሔር ፤
(ከእግዚአብሔር የተነገረሽ ቃል እንደሚፈጸም ያመንሽ አንቺ ብፅዕት ነሽ) ብላ እንዳመሰገነቻት (ሉቃ 1፡45) "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም" ብላ ስታምን ነበር ሞትን ያለፈችው፤ትንሣኤ ልቡናን ቀድማ የተነሣችው፤ ይህ ምሥጢር የተከናወነባት ናት፤እያንዳንዱን የጌታን ቃል በልብዋ ትጠብቀውና ታስበው እንደነበር ተጽፏል፤ሉቃ 2፡51፡፡

እንዲህ ከሆነ ሕይወት የሆነውን ጌታ ፀንሳ፤ወልዳ የድንግልና ጡት ያጠባች ሆና እንዴት ትሞታለች?
ሕይወትን የዳሰሱ እጆች፤ሕይወትን የተመለከቱ ዓይኖች፤ሕይወትን ያቀፉ ጉልበቶች እንዴት ለሞት ይሰጣሉ? ብለን ስንጠይቅ የሚከተሉት ምላሾች ይኖሩናል፡፡

➊ ከተገፋችበት ፤ከተንከራተተችበትና የኀዘንና የመከራ ሰይፍን ካስታናገደችበት ዓለም ወደማያልፈው ዓለም ወደመንግሥተ ሰማያት መጠራቷን፤የማያልፈውን ዋጋ እንደተቀበለች ለማሳየት እንጂ የሞት ሞት የሚባለውን መፍረስና መበስበስን፤ወደ ሲኦል መውረድን የሚያሳይ እንዳልሆነ መገንዘብ ያስፈልጋል።

ይህንንም ቅዱስ ያሬድ "ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ ፈለሰት እምዘ ይበሊ ኀበ ኢይበሊ፤ዳዊት አቡሃ በመሰንቆሁ እንዘ የኀሊ፤የሰው እጅ ያልሰራት ድንኳን ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ የተናገረላት እመቤታችን አባቷ ዳዊት በመሰንቆው እያመሰገናት ከሚያረጀው ዓለም ወደማያረጀው/ወደማያልፈው ሄደች"
በማለት እነደነገረን ነው፡፡

➋ ከሰማይ የወረደች (ኃይል አርያማዊት) ናት የሚሉ አሉና ሰው እንደሆነች እና ከምድር እንደተገኘች፤ሙሉ የሰውነት ማንነት ያላት መሆኑን ለማጠየቅ ነው፤ እመቤታችንን ሞት ባያገኛት ካልዕ ፍጥረት (ልዩ ፍጥረት) ስለሆነች ነው ብለው ብዙዎች በተከራከሩ ነበር፤ይህም ደግሞ ክርስቶስ የነሣውን ሥጋና ነፍስ (ምሥጢረ ተዋሕዶን) ጥያቄ ምልክት ውስጥ ይከተው ነበርና በዚህ ምክንያት በሕገ ሰብእ በሩካቤ ብእሲ ወብእሲት ስለተገኘች በሕገ ሰብእ ሞት ተጠርታለች፤ ይህ ሞቷ እሷን ሌላ ፍጥረት የጌታን ተዋሕዶ ምትሐት ከማለት የሚታደግ መድኃኒትም ጭምር ነው፡፡

➌ ፍትሑ ርቱዕ (ፍርዱ ቅን የሆነ) እግዚአብሔር ለማንም እንደማያዳላ ያጠይቃል፤ እመቤታችን እንደማንኛውም ሰው ሞትን ባታይና ባትቀምስ ፍርዱ ትክክል አይደለም፤ አንዱን በሞት ይወስዳል ሌላውን ይተዋል፤ወዲህም ልጅዋ አምላክ ነውና ሞትን ያልቀመሰችው በልጅዋ ምክንያት እንጂ እርሷ የተለየ ቅድስና ስላላት አይደለም በተባለ ነበርና ሞትን እንድትቀምስ ፈቅዷል፤ሞትን መቅመሷ በክብር ላይ ክብር ቢጨምርላት እንጂ ቅንጣት ታህል ክብር አይቀንስባትምና፡፡

ይህንንም ደራሲው፦

"ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ፤ክርስቶስ ሥጋውን ለነሳበት አካል በሞት አላዳላም" በማለት ተናግሯል፡፡

ቅዱስ ያሬድም ፦

"እንበይነዝ አእምሩ በውስተ ፍትሕ ከመ ኢያደሉ ትጥዓም ሞተ እሙ ወእመ ኩሉ
አዘዘ ወልድ በርቱዕ ቃሉ"

(በፍርድ እንደማያዳላ ስለዚህ ነገር ዕወቁ፤የእርሱ እናት፤የሁሉ እናት እመቤታችን ሞትን ትቀምስ ዘንድ ወልድ በማይሻር ቃሉ አዘዘ) በማለት አስረግጦ ተናግሯል። (ቅዱስ.ያሬድ)፡፡

👉መልኩ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ
ቅድስት ኤልሳቤጥ ከምድር በተባበረ ቃል እንዲህ ብለዋል👇
"ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ"
ሉቃ 1፥28 ፤ ሉቃ 1፥42

👉የተባረክሽ ማለት መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለብሽ ማለት ነው!

በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን እያማለደች የምታሰጥ ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ምድራችንን በበረከት ትጎብኝልን!!!!!

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


ብቻችንን አንችልም
             
Size:-59.4MB
Length:-1:04:12

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery














የ የካቲት 16 የኪዳነ ምረት ስርዓተ ማህለት እነሆ


እግዚአብሔር ለምን ዝም ይላል?
             
Size:-82.9MB
Length:-1:38:35

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@kendilebirihan
@kendilebirihan
@kendilebirihan


እንደ ሁኔታው ለብቻው ልመለስበት እችላለሁ) በጣም የተለያዩ ሀሳቦች ናቸው። እንዲህ ያለው ችግር ቀደም ብሎም የነበረ ችግር ነው። ስለዚህ አሁንም ለመርታት በሚፈልግ ልቡና ውስጥ ሆኖ ጥቅሶችን ከዐውዳቸው ነጥሎ አውጥቶ መጠቀም ችግርን ያባብስ እንደሆን እንጂ መፍትሔ ሊሆን አይችልምና ከዚህም መጠበቅ ተገቢ ነው።

4) ከመጠራጠር አለመጀመር

መና/ፍቃን ሀሳብ እና ጥያቄ ሲያነሱ የእነርሱን አመክንዮ እና ፍረጃ ሰምቶ ነባር ትምህርቶችን ወይም ምንጮቻችን ከመጠራጠር መጀመር በጣም አደገኛ ነገር ነው። ለምሳሌ ሳጥናኤል እኔ ፈጠርኳችሁ ባለ ጊዜ በጥርጥር የጀመሩት እውነት በተገለጠ ጊዜ ከእርሱ ጋር አብረው ወድቀው የሚያስቱ መናፍስት ሆኑ እንጂ ሲመለሱ አላየናቸውም። እውነቱን ባያውቁም በያለንበት እንቁም ባለው በቅዱስ ገብር ኤል ቃል ጥርጥሩን ሳያስገቡ የጸኑት ግ ን በኋላ እግዚአብሔር እውነቱን ገልጾላቸዋል። ይህ የመጀመሪያው የፍጥረት ፈተና የሚያስረዳን ከመጠራጠር መጀመር ምን ያህል አደገኛ መሆኑን ብቻ ሳይሆን መንገዱ ዲያብሎሳዊ መሆኑን ነው። በሳይንስ ከመጠራጠር መጀመር ወደ ዕውቀት ይወስዳል ከሚባለው በተቃራኒ በሃይማኖት በመጠራጠር አለመጀመር መሠረታዊ ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን ማለት ነው።

በዚሁ መንገድ ካየን አንዳንድ የግእዝ ምንጮቻችን ከሌላ ሀገር ምንጮች ስናነጻጽር በቀጥታ ላይገጥሙልን ይችላሉ። ለምሳሌ ያህል ገድለ ጊዮርጊስን ስንመለከት ሰማዕቱን ያሰቃየውን ንጉሥ ዱድያኖስ ይለዋል። በሌላው ሀገር ግን ያሉት ምንጮች በሙሉ ደግሞ ንጉሡን ዲዮቅልጥያኖስ ይሉታል። ይህ በመሆኑ የእኛ ምንጭ ስሐተት ነው ልንል አንችልም። እኔ እንኳ በአቅሜ በአደረግሁት ፍለጋ አንድ ጥናት ላይ የጥንት ምንጮች ዱድያኖስ ይሉ እንደነበር አግኝቻለሁ። ስለዚህ ይህ ስም ምንጫችን ስሐተት መሆኑን ሳይሆን ምንጫችንን ወይም አቀባይ ቋንቋችንን እንድንመረምር እና የእኛ ቅጂ ከቀዳማውያን ምንጮች መሆኑን ይጠቁማል እንጂ ልዩ መሆኑ ስሕተት መሆኑን ሊያሳይ አይችልም ማለት ነው።

በገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ ያለው የሞቱበትን በሽታ እንደመስቀሌ እቆጥርልሃለሁ የሚለውን ሀሳብ ስሑታኑ ባነሡበት መንገድ ተመልክቶ ከመጠራጠር ከመጀመር ወደ ገድሉ ጠልቆ ገብቶ ምክንያቱን ከማጥናት መጀመር ከብዙ በሽታ ይፈውሳል። በዚሁ ጉዳይ ላይ ገድሉን ስንመለከት አቡነ ተክለ ሃይማኖት ትልቁ ፍላጎታቸው የደም ሰማዕትነትን ማግኘት ነበር። ዘመኑ ደግሞ ያንን አልፈቀደላቸውም። ስለዚህ ጌታ በበሽታ የገጠማቸውን ተጋድሎ እንደ ሰማዕትነት ወይም መስቀል እንደሚቆጥርላቸው ቃልኪዳን ገባላቸው ይላል እንጂ መና/ፍቃኑ የሚሉትን ወይም ሊሉ የሚፈልጉትን ገድሉ በፍጹም አይልም።

በገድለ ቅዱሳንና በገድለ ቅዱሳን መጽሐፍ መካከል ልዩነት እንኳ ቢኖር ወደ ቀዳማይ ምንጭ በሚደረግ ጥናት ይስተካከላል እንጂ ገድለ ቅዱሳንን ወደ መጠራጠር ሊወስድ አይችልም። በርግጥ የሰው አእምሮ ውሱን ስለሆነ ለእንዲህ ያለ ፈተና ተደጋግሞ ሊወድቅ ይችላል። እንዲህ ያሉትን ነገሮች ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስም ያስረዳል። ለምሳሌ ያህል በሰማርያ እጅ ከባድ ረሀብ ተነሥቶ ሁለት ሴቶች ልጆቻቸውን ቀቅለው ለመብላት ከተስማሙና የአንዲቱን ከበሉ በኋላ ሁለተኛ ልጇን ስትደብቅ በተፈጠረው ክርክር ንጉሡ ስሞቶ በኤልሣዕ ላይ ተቆጥቶ ነበር። በኋላ ላይ ግን “የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ነገ በዚህ ጊዜ በሰማርያ በር አንድ መስፈሪያ መልካም ዱቄት በአንድ ሰቅል፥ ሁለትም መስፈሪያ ገብስ በአንድ ሰቅል ይሸመታል አለ። ንጉሡም በእጁ ተደግፎ የነበረ አለቃ ለእግዚአብሔር ሰው መልሶ፦ እነሆ፥ እግዚአብሔር በሰማይ መስኮቶች ቢያደርግ ይህ ነገር ይሆናልን? አለው። እርሱም፦ እነሆ፥ በዓይኖችህ ታየዋለህ፥ ከዚያም አትቀምስም አለ” /2ኛ ነገ 7/ ተብሎ እንደተጻፈ ንጉሡ በመጠራጠሩ ምክንያት በሕይወቱ እንዲቀጣ ሆኗል። ስለዚህ ከመጠራጠር መጀመር ውጤቱ አደገኛ መሆኑን መረዳት እና በእምነት ጸንቶ የማያውቁትን ለማውቅ መጣር ተገቢነት ይኖረዋል ማለት ነው። ለዛሬው በእነዚሁ ልፈጸም። ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን

©ዲያቆን ብርሀኑ አድማስ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


ስለ ሃይማኖታዊ ውይይት አንዳንድ ነገሮች

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያው ሃይማኖታዊ ክርክሮች በረከት እያሉ መጥተዋል። እነርሱን ተከትሎ ደግሞ በአንድ ቤት ውስጥ ባሉትም መካከል ውይይቶች አለፍ ሲልም መነቃቀፎች አንዳንድ ጊዜም ደግሞ በእወቀትም ይሁን ያለዕውቀት መጠላለፍ የሚመስሉ ሁኔታዎች እንዳሉ ይታያል። በእንዲህ ያለው ጊዜ ማድረግ የሚገባን ምንድን ነው የሚሉ ድምፆችም ይሰማሉ። የምናደርገው ነገር በዚህ ጊዜ በዚያ ጊዜ የሚባልበት መሆኑ ባይቀርም በእኔ እምነት በአግባቡ ከተጠቀምንበት እና ከተማርንበት ከሁሉም ልንጠቀም እና መንገዳችንን ትክክል የሆነልን እርሱኑ ልናጸና ፈንገጥ ያልነው ወይም የመንገድ ጠርዝ በመርገጥ የተንሸራተትን ካለንም ልንመለስ እና በመሐል መንገድ እንድንጓዝ ሊጠቅመን ይችላል። እጅግ በትንሹ ከሰማኋቸው ተነሥቼ አጠቃላይ መርሕ ተኮር ሁኔታዎች በዚህ ጽሑፍ ልጠቁምና እንዳስፈላጊነቱ ደግሞ በመከራከሪያ ነጥቦቹም ላይ ላክል እችላለሁ። ከዚህ በፊት “አድማሱ ጀንበሬ ሕይወቱ እና ትምህርቱ” የሚለው መጽሐፍ ሲታተም በመቅድምነት የወጣ አጭር ጽሑፍ ላይ ከንባቦቼ ከቀራረምኩት የተወሰኑ ሀሳቦችን ማጋራቴ ይታወቃል። እነዚያን ያላየ ቢያያቸው አንድ ነገር እንኳ የሚጠቅም ሊያገኝ ይችላል ብዬ አምናለሁ። እነዚያን ያነሣሁበት ምክንያት ግን እነዚህን ጉዳዮች የእነዚያ ቀጣይ አድርጋችሁ እንድትወስዷቸው ለማሳሰብ ያህል ነው።

በውይይትም ሆነ በክርክር ውስጥ ያለን አገልጋዮች ልንጠነቀቅባቸው የሚገቡን ጉዳዮች መካከል

1) በራስ ማስተዋል አለመደገፍ

በመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱስ ከተጻፉት ታሪኮች፣ ምክሮች እና ትርጓሜዎች መካከል አንደኛው በራሳቸን መረዳት፣ ማስተዋል (reasoning) ላይ እንዳንደገፍ እና በዚህ ምክንያት ወደ ፈተና እናዳንገባ መጠበቅን የሚመለከት ነው። ለምሳሌ ያህል ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን የወሰደበትን ሒደት ስንመለከተው በምንም ዓይነት ተፈጥሮአዊ አመክንዮ ይሠራል ይሆናል ለማለት የሚቻል አይደለም። የአብርሃምና ሣራ እንዲሁም የዘካርያስ እና የኤልሳቤጥ በዕርጅና ልጅ መውለድ የሚያስተምረንም ይህንኑ ነው። ዋናው ጉዳይ ግን እግዚአብሔር እርሱ ባወቀ ኤሳው ቀድሞ እንዳይወለድ እና ያዕቆብ ቀድሞ እንዲወለድ ማድረግ እየቻለ ከተወለደ በኋላ በኩርናውን እንዲወስድ ለምን አደረገ? ለእነ አብርሃም እና ለእነ ዘካርያስ ልጆችን ቀድሞ ለምን አልሰጣቸውም ብለን ብንጠይቅ ዋናው መልስ እግዚአብሔር ሊያስተምረን የፈለገው ከተፈጥሮ ሕግ እና ከየትኛውም አመክንዮ ወይም የሰው የሕሊና መረዳት የሚያልፉ ነገሮችን የሚያደርግ መሆኑን ለማሳየት ነው። በመጽሐፍም “በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤” /ምሳ 3 ፡ 5/ ተብሎ የተጻፈው ለዚህ ነው።

በርግጥ ሃይማኖት የሚባለውም ይህ ነው። ከመረዳታችን እና ከሎጂካችን ባሻገር እግዚአብሔር የሠራውንና የሚሠራውን ማመን። ጌታችን ከእመቤታችን ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም የተጸነሰበት፣ የተወለደበት፣ የሞተበት፣ ድኅነታችን የፈጸመበት፣ የእመቤትችን በሁለንተና ንጽሕት መሆን እና የመሳሰሉትን ነገሮች መረዳት የሚቻለው ያዕቆብ ከዔሳው ብኩርናውን በወሰደበት መንገድ ብቻ ነው። ይህም ማለት ከሎጂክና ከአመክንዮ ተላልቅቆ እግዚአብሔር አምላክነቱን በየዘመኑ ትውልድ እግዚአብሔርነቱን የገለጸባቸውንና በአእምሮ ከመታሰብ፣ በሎጂክ ከመረዳት በላይ የሆኑትን በመቀበል ነው። ያዕቆብ ብኩርናን የወሰደበት መንገድ በእምነት የምንቀበለው ብቻ ነውና። እነዚህ ነገሮች የተፈጸሙት፣ እና በቅዱሳት መጻሕፍት የተመዘገቡበት ዋና ዓላማም የአካላዊ ቃል ሰው መሆን ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጥያቄዎች በሙሉ አስቀድመው የተዘጋጁ መልሶች እንዲሆኑ ነው።

በራስ ማስተዋል ወይም በራስ የመረዳት ችሎታ ላይ መደገፍ ቢያንስ ሁለት ታላላቅ ፈተናዎችን ወደ እኛ ያመጣል። የመጀመሪያው ከእምነት መጉደል ነው። ይህ ደግሞ እንኳን በእኔ ቢጤዎች ይቅርና ጻድቁ ዘካርያስንም ፈትኖታል። ዘካርያስ ቅዱስ ገብርኤልን የተከራከረው ዕውቀት ወይም የተፈጥሮ ሕግ ገድቦት ነውና። ሰው ካረጀ ካፈጀ በኋላ አይወልድም የሚለው ዕውቀቱ ወይም የተፈጥሮ ሕጉ ስሕተት ሆኖ አልነበረም። የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ግን ከእነዚህ የሚያልፍ ነበረ። ስለዚህ በመረዳት ወይንም በማስተዋላችን ላይ መደገፍ መጀመሪያ የሚያመጣው ፈተና እንኳን ሰዎች መላእክትም ቢናገሩን እንድንከራከር ሊያደርገን ይችላል ማለት ነው። ሌላው ቀርቶ ትናንት ያከበርነው የልደተ ስምዖን ታሪክ የሚያስታውሰንም ይህንኑ ገጠመኝ ነው። ሴት እንጂ ድንግል አትወልድም የሚል ሀሳብ ይዞ ድንግል ትጸንሳለች የሚለውን የነቢዩን የኢሳይያስን ቃል ሴት ወደሚል ለመቀየር ሞክሮ ከእግዚአብሔር ይህን ሳያይ እንዳይሞት የተረዳው የእግዚአብሔር አሠራር ከሰው ማስተዋል እና መረዳት ባሻገር ስለሆነ ነው። በዚህች መንገድ መጓዝ የጀመረ ሰው አይሁድ ከመስቀል ውረድና እንመንብህ እንዳሉት በራስ መረዳት ቅድመ ሁኔታ አስቀመጦ እግዚአብሔርን መፈተኑ የማይቀር ነው።

ሁለተኛው እና ከባዱ ፈተና ደግሞ ሌሎች ይህን መረዳት እንደማይችሉ በማሰብ የዲያብሎስ ረቂቅ ወጥመድ በሆነው የትዕቢት ወጥመድ ውስጥ መውደቅን ሊያስከትል ይችላል። ይህ ደግሞ ብዙ ጥፋቶችን አከታትሎ ያመጣብናል። ሰሎሞን “በልቡ የታበየ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነው፥ እጅ በእጅም ሳይቀጣ አይቀርም” /ምሳ 16 ፡ 5/ ሲል እንደገለጸው ቅጣቱም ቀጥታ ከእግዚአብሔር ይሆናል። ለሰውየው ግን እያወቀ ወይንም እውቀቱ ትክክል ስለሆነ እንጂ እየታበየ እና እየተጎዳ እንደሆነ አይሰማውም። ለዚህም ነው “ለሰው ቅን የምትመስል መንገድ አለች፤ ፍጻሜዋ ግን የሞት መንገድ ነው” /ምሳ 16 ፡ 25/ ተብሎ የተጻፈው ። ስለዚህ ከሁለቱም ለመጠበቅ በራስ መረዳት ላይ አለመደገፍ ትልቁ መፍትሔ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች እና ምክሮች ያረጋገጡልንም ይህንኑ ነው።

2) ከትዕቢት / ካለመሸነፍ መንፈስ መራቅ

የትዕቢት ነገር ከላይም የተጠቆመ ቢሆንም በዓለም ለተፈጠሩት ችግሮች ሁሉ መሠረቱ ትዕቢት ነው። በተለይ በሰው ፊት ተሸናፊ መባልን፣ አያውቅም መባልን መፍራት፣ ተሳስቷል መባልን መሸሽ ወደ ማስረዳት እና ራስን ነጻ ለማውጣት ሲባል ወደ ተለጠጠ ክርክር ይስባል፣ ከዚያም ወደ ባሰው ችግር ወይም ፈተና ሊያደርስ ይችላል። ስለዚህ ጥያቄዎች ሲፈጠሩ ቆም ብሎ ማድመጥ ፣ መጸለይ እና ቅዱሳት መጻሕፍትን እያጠኑ ሊቃውንትን ደጋግሞ መጠየቅ ብዙ ችግሮችን ያስወግዳል። ይልቁንም ልሳሳት እችላለሁ በሚል ትሑት ሰብእና ውስጥ ሆኖ እግዚአብሔርን የሚለምን ሰው እግዚአብሔር በፍጥነት ከዚህ ችግር እንደሚያወጣው የታመነ ነው።

3) የምንጮችን ዐውድ በአግባቡ ለመራዳት መጣር

ብዙ ጊዜ ወደ ክርክር ተይዘው የሚወጡት ምንጮች ወይም ማስረጃዎች በራሳቸው ምንም ችግር የለባቸውም። ሆኖም ከተነገሩበት ወይም ከተጻፉበት ዐውድ አውጥተን ከተመለከትናቸው ችግር ውስጥ ልንወድቅ እንችላለን። ለምሳሌ ያህል ጥንተ አብሶን በተመለከተ የሚነሣው ክርክር ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ሊሆን ይችላል። የጥንት ሊቃውንት ጌታ ሥጋውን ከሰማይ ይዞ ወርዷል፣ በእመቤታችን አደረባት እንጂ ሥጋን ከእርሷ አልነሣም ለሚሉ የዚያ ዘመን መና/ፍቃን የተሰጡ መልሶች ያንኑ የበደለውን ሰው የአዳምን ሥጋ ነው የተዋሐደ ሲሉ ያንን የሳተውን፣ የወደቀውን፣ የጎሰቆለውን የእዳም ሥጋ እንደተዋሐደ ተከራክረው አስረድተዋል። ሆኖም እነዚህ አገላለጾች እመቤታችንን ጥንተ አብሶ አለባት ሊያስብሉ አይችሉም። (ይህን ጉዳይ

20 last posts shown.