#የmom


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


ኑ እናንብብ
#ተከታታይ ልቦለዶችን
#ግጥም #አስተማሪ ፅሁፎችን
#የህይወት እይታዎች #አሰገራሚ የመፅሃፍ ሀሳቦች
ከእናንተው ወደ እናአንተው እናደርሳለን
እንዲጨመር እንድናስተካክል ምትፈለገትን ሀሳቦች ፃፉልኝ
ለማንኛውም ሀሳብ አስተያየት ይፃፍልን👇
@Yemom_bot
@BM846
@yemomdan

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


" ሲገባኝ ሁሉም ሰው የሆነች ”የለውጥ ኩርባ” አለችው።  አስተሳሰቡ ወይ ስሜቱ አሊያም ድርጊቱ የሚቀየርባት ። ወደ ዐዲስ  ምዕራፍ የሚታጠፍበት ወይም ከወደቀበት መቀመቅ የሚስፈነጠርበት ወይም ለዛለው ጉልበቱ አቅም የሚያገኝበት። ለውጥ ወደ ተሻለ ማደግ ብቻ አይደለምና ኩርባውን ሲታጠፍ ውድቀትም ሊሆን ይችላል። ያች የለውጥ ኩርባ አንድ የሆነች ኢምንት ክስተት ልትሆን ትችላለች ወይም ዐረፍተ ነገር ወይም አንዲት ቃል ምናልባት አንዲት መሳም ወይም የአንድት ደቂቃ መታቀፍ ወይም.... "

- ከ'ጠበኛ እውነቶች ' መጽሐፍ ገፅ  116

ደራሲ :- ሜሪ ፈለቀ


እናቴ ብዙ ጊዜ ሲከፋኝ ስታይ “ህይወት እንደዚ ነዉ ትለምደዋለህ ባክህ ፡ ዋናዉ ነገር ፀፀት የእለት ጉርስህ ሆኖ አለማደሩ ነዉ” ትለኛለች

    እና የገባኝ ነገር ቢኖር ህይወት በጣም overwhelming ነዉ፣ ህይወትን ለመግፋት በእያንዳንዱ ፈተና መሰበር የለብንም፥

አንዳንዴ “life ነዉ፣ ሰዉ ነኝ፣ እወድቃለዉ፣ እነሳለሁ፣ አጠፋለሁ፣ እማራለሁ” ብለን ለማለት አቅም ሊኖረን ይገባል
አይመስላችሁም?




Forward from: ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
አብዘርዲዝም - ካምዩ

ምንጭ ፦ ፍልስፍና ከዘርዓያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ምንጭ ፦ ፍሉይ አለም

መጠለያ ባጣህበት ሁኔታ በዝናብ እየተደበደብክ እየተጓዝክ ሳለ፣ መሳቅ ጀምረህ አታውቅም? የሆነ ጉዳይ በእጅጉ ተበላሽቶብህ ከዚህ በላይ ምን ሊመጣ አይነት ስሜት ፈገግ ብለህ አታውቅም? በችግሮችህ ውስጥ ሳለህ እያንዳንዷን ደቂቃ ወደህ አታውቅም? ይህን አልበርት ካምዩ አብሰርዲቲ ይለዋል፡፡

ካምዩ ፈረንሳያዊ የኤግዚስታንሻሊዝም (ህላዌነት) ፈላስፋ ነው፡፡ በቀላል ታሪክም ፍልስፍናውን ይጀምራል፡፡

ሲሲፈስ የተባለ የጥንታዊቷ ግሪክ ንጉስ አማልክቱን የሚያስቆጣ ተግባር ፈጸመ። ሲሲፈስ ሞትን በሰንሰለት አሰረው፡፡ ይህንንም በማድረጉ የሰው ልጅ ዘላለም ኗሪ ሆነ። በመጨረሻም አማልክቱ ሲሲፈስ ያደረገውን አወቁ፤ በርሱ ላይም ዘላለማዊ ቅጣት ፈረዱበት፤ የሞትንም ሰንሰለት በጠሱ፡፡ እናም ሲሲፈስ ለመቀጣጫ እንዲሆነው ዘላለም ድንጋይ ሲያንከባልል እንዲኖር ተፈረደበት። ግዙፍ ቋጥኝ እየገፋ ወደ ተራራ አናት ያደርስዋል፤ ወዲያውም ቋጥኙ ወደ ተራራው ስር ተንከባሎ ይወርዳል፤ ሲሲፈስም እንደገና ከታች ጀምሮ ወደ ላይ ቋጥኙን ይገፋዋል፡፡ ቋጥኙም ተመልሶ ወደ ተራራው ግርጌ ይወርዳል...

ይህ የሲሲፈስ ዘላለማዊ ቅጣቱ ነው። ያንተስ ሕይወት ከርሱ ይለያልን? የሲሲፈስ እልፍ ጊዜ እየተመላለሰ ቋጥኝ ማንከባለሉ ትርጉም አልባ እንደሆነ ይሰማሃል? ሆኖም ያንተ ሕይወት ትርጓሜው ምንድን ነው?

ሕይወትህን ልክ እንደ ሲሲፈስ ትርጉም አልባ ቋጥኞችን ስትገፋ ነው የምታሳልፈው፡፡ የማይሞላ ሆድ አለህ... ሚልዮን ጊዜ መግበኸው ሚልዮን ጊዜ ጎድሎብሃል፤ የማይሞላ ፍላጎት አለ... ሚልዮን ጊዜ ተደስተህ ሚልዮን ጊዜም ተከፍተሃል። በጠዋት ከእንቅልፍህ ትነሳለህ፤ ገንዘብን ፍለጋም ወደ ስራ ትሄዳለህ... ቀኑ ይመሻል ዳግም ይነጋል... በጥዋት ወደ ስራ ትሄዳለህ. ከእለታት በአንዱ ቀንም ራስህን በሞት አልጋ ላይ ታገኘዋለህ፡፡ እናም በሕይወት ዘመንህ የምታደርገው ነገር ሁሉ ልክ እንደ ሲሲፈስ ቋጥኝ መግፋት- ዘበት ነው!

የሰው ልጅ ህልቆ መሳፍርት በሌለው ሁለንተና ላይ ራሱን ሲያገኘው፤ “ለምን?” የሚል ጥያቄን ይጠይቃል። ለምን ተፈጠርኩ? ለምን እኖራለሁ? የሕይወቴ ትርጉምስ ምንድን ነው? ሆኖም እውነታው ይህ ነው... ያንተም የኔም የመኖር ሁኔታ በአጋጣሚዎች የተፈጠረ እንጂ ትርጓሜ ያለው ነገር አይደለም በጸጥታ ውስጥ ባለው በግዙፉ ሁለንተና ውስጥ አንተ ማን ነህና ሕይወትህ ትርጉም ይኖረዋል? ሁለንተናም ስላንተ ግድ የለውም... ለጥያቄህም መልስ የለውም፡፡ ሆኖም ይህ መሆኑን ብናውቅም፤ ሰው ነንና የሕይወታችንን ትርጉም መፈለጋችንን አናቆምም የሞትን ቀን ያበቃለታል። ሞት በሕይወታችን የኖርንላቸውን ተግባራቶች በሙሉ ዋጋ ያሳጣቸዋል፡፡ ይህንን ነው አብሰርዲዝም ወይም የሕይወት ዘበትነት ሲል የሚጠራው፡፡

እና ዘበት በሆነ ዓለም ላይ እንዴት እንኑር?

ታይታኒክ በተባለው ፊልም መጨረሻ ላይ መርከቧ እየሰመጠች ሳለ ሙዚቀኞች ቫዮሊን ሲጫወቱ ይታያል፡፡ እንደሚሞቱ ቢያውቁም፣ ቅጽበታቸውን ብቻ መኖር ጀመሩ፤ የሚወዱትንም ሙዚቃ ከልባቸው ተጫወቱ፡፡

ካምዩ በአንደኛው መጽሐፉ ላይ እንዲህ ይለናል - "የምር የሆነ አንድ የፍልስፍና ጥያቄ ብቻ ነው ያለው፤ ጥያቄውም - ራሴን ላጥፋ ወይስ ቡና ልጠጣ?”

እንደ ካምዩ እሳቤ የሰው ልጅ የሚኖርበት ምክንያት ከሌለው ሶስት ነገሮች ያደርጋል፡

የመጀመሪያው ራሱን ያጠፋል፡፡ ማለቂያ አልባ በሆነው ሁለንተና ውስጥ የምትበራ አንድ ሻማ የርሷ ጭል... ጭል ማለት ትርጉም የለውምና ራሷን እፍ ብላ ታጠፋለች፡፡ ይህን ካምዩ የዓለምን ዘበትነት ማምለጫ ይለዋል።

ሁለተኛው philosophical suicide ይፈጽማል፡፡ ይህም ማለት ሕይወት ትርጉም ባይኖራትም ትርጉም እንዳላት አድርጎ ማሰብ ይጀምራል። ለዚህ ዋነኛ ተጠቃሽ የሚሆኑት ጭፍን አማኞች ናቸው፡፡ በእምነት ውስጥ መመርመር የለም... የምትኖርበት አላማ እንዳለህ እና የምታምንበት ሀይል ለዚህ አላማ እንደፈጠረህ ያለምንም መጠራጠር በጭፍን ትቀበላለህ፡፡ ስለሆነም መኖርህ ዋጋ አልባ ወይም ዘበት እንደሆነ አይሰማህም፡፡

በሶስተኛነት የምናገኘው ካምዩ absurd hero ይለዋል። ይህ ሰው ሕይወቱ ትርጉም እንደሌላት ያውቃል፤ ለሌሎች ሰዎች ትርጉም የማይሰጥ ነገር ግን ለእርሱ ብቻ ዋጋ ያለው ... ለእርሱ ብቻ የሚሰራ የሕይወት ትርጉምንም ይፈጥራል። ይህ የትርጉም ፈጠራ ሂደትም በራሱ ደስተኛ ያደርገዋል። ለሲሲፈስም ድንጋዩን ወደ ተራራ ማንከባለሉ ለእርሱ ትርጓሜ አለው፡፡ ይህ ለስው ልጆች የከፈለው መስዋእትነት ምልክት ነው. ይህ አማልክቱ ለእርሱ የሰጡት ቅጣት ምንም እንዳልሆነ ማሳያ መንገዱ ነው... ፈገግ ብሎም ድንጋዩን ይገፋል... የእርሱ ፈገግታም አማልክቱን እንደሚያስቆጣቸው ያስባል። እናም ድንጋይ ማንከባለሉ ብቻ ልቡን በደስታ ይሞላዋል።

ካምዩም ሕይወት ትርጉም አልባ እንደሆነች ቢያውቅም እንኳ እንደ ሲሲፈስ ሁን ይልሃል። በዝናብ ውስጥ ደንስ... ትርጉም አልባ በሆነች ዓለም ላይ ለራስህ ብቻ እውነት የሆነ የመኖር ትርጉም ፍጠር፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy


ሰላም ሰላም ያው የህይወት ጥድፊያ ቢያጠፋፋንም ዛሬ ተከስቻለው ለምሽታችሁ ማድመቂያ ይቺን ጀባ ብያለው😊

1.ትልቅ ሰውነት በዘር ወይም በትውልድ ሳይሆን በተግባራዊ ስራና በህይወት ፈተና ውስጥ ነጥሮ የሚወጣ ነው።

2.ከይስሙላ አንድነት ፣በእምነት ካልተዋቀረ ህብረት፣ በግርግር ከተሞላ መንጋነት ይልቅ ጥርት ያለ ልዩነት ለመፍትሄ ያበቃል።

3.በእውቀት ተመራምሮ አዲስ ነገር ማግኘት ለሰው ልጅ የስልጣኔ መጥረጊያ  መንገድ ከፋች ሲሆን የሀሰት ወሬ መፍጠር ግን የዝቅጠት መንገድ ነው።

4.ከሚጎትቱንና ከሚያደናቅፉን አሮጌ ችግሮች መውጣት ያሻናል፣አሮጌ ባላንጣዎቻችን በትላንት አባዚያችን ውስጥ እንድነቅዝ እንደሚሹ ማስተዋል አለብን።


5.ዋና ቀጣፊ ሰው ራሱን የሚያታልል ነው።

6.ገደልን የዘለለ ፈረስና ቂምን የተወ ሰው አዋቂ ነው።

7.የሚፈልገውን ያላገኘ ልብ ዘውትር መንገደኛ ነው።

8.ያለውን የማያውቅ የጎደለውን አያውቅም።

9.ጭንቀትህን በስራ ተካውና ተአምር ሲፈጠር ተመልከት።


10.ክፋት የአእምሮ በሽታ ሲሆን ቅንነት ግን የህሊና እረፍት ነው።

11.ሌሎችን ለመምሰል እንደሚመኝ ሰው ጭንቀት የበዛበት ሰው የለም።

12.ፍቅር የከንፈር ወይም የገንዘብ መገጣጠም ሳይሆን የልብ መገጣጠም ነው።


13.ቆንጮ ሴት ባየህ ጊዜ ተፈጥሮን አድንቅ እንጂ የዝሙት መንፈስ አይሰማህ። ዝሙት ከደካማ መንፈስ የሚመነጭ ነው።

14.ብዙ የሚናገሩ ሰዎች የማሰቢያ ጊዜ የላቸውም።

15.የማያውቀውን ነገር ያልተናገረ ጥበበኛ ነው።

16.ፍቅር በድንገት መጥቶ እንደሚያልፍ ጎርፍ ሳይሆን ጠልፎ የማያሰጥም የውቅያኖስ ማዕበል ነው።

17."ቅናት" ፍቅር እና ትዳርን ገዝግዞ የሚጥል ስለት ነው።

18.ሴቶች ጆሮዋቸውን ወንዶች አይናቸውን ያምናሉ።

19.ፍቅር የተፈጥሮ ሁለተኛ ፀሀይ ነው።

20.በፍቅር የተሞላች ቃል የወደቀን ሰው ታነሳለች።
 


እስኪ ምን ያህሉቻችሁ አብራችሀኝ ናችሁ ብሞነጭጭር አብራችሁኝ ከሆናችሀ


Forward from: BM
ዱብ ዱብ ባይ እንደበረዶ
በልጅነቱ በረሀ ለምዶ።
እጥፍጥፍ እንደ ኩታ ልብስ
አተኳኮሱ አንጀት የሚያርስ።

⚔️⚔️⚔️⚔️⚔️⚔️⚔️⚔️⚔️⚔️
እንኳን ለ 126ኛው የአድዋ ድል በአል አደረሰን ክብር ደማቸውን አፍስሰው የባርነት ቀንበርን ለናዱት አያቶቻችን
ኢትዮጵያ ለዘለአለም ትኑር።








ወይ ያ'ኔ
ሰላም ተሸርሽሮ መሰረቱን ሲያጣ
የስልጣን እርካቡ ታሪክን ሲተካ
ጸሀይ ነዉ ያልነዉ ቀን ዳምኖ አዘነበ
ዘርም ተበላሸ ሰብልም ረገፈ
ወይ ያ'ኔ ያልነዉ ቀን ወይዘንድሮ ሆነ
ስሙን በመለወጥ ታሪክን ደገመ
በልጽገን አሽተን አፍርተን የኖርነዉ
ለካስ እየረገፍን ወድቀን ተነስተን ነዉ
እንደዘመን እማ እንደ ታሪክማ
እንደ ነገስታቱ እንደ ሀገር ጀግና
ታቦቱን አዉጥተዉ ድል የተቀናጁ
ደማቅ ታሪክ ጽፈዉ ሀገርን ያቆዩ
እልፍ ሰማእታት ነግሰዉ ነበር ያኔ
ያኔ ጥሩ ነበር ዛሬ እንበል ወያኔ
ለኛም ገርሞናል ሆነና ብሂሉ
እኛም አልገባንም ከተነሳንበት ወድቃቹሀል ሲሉ
😁😁😁😁😁😁😁😁
እንቁ ማርያም (መባ)


🙏🙏🙏🙏🙏እግዚኦ🙏🙏🙏🙏🙏
መሀረነ አምላክ ባክህ ይቅር በለን
በምረትህ እንጂ በቁጣ አትዳኘን
ሃያ ሰባት አመት ሁሉ ወሰለተ
ሶስት አመት ንሰሀ አንተ ብትፈቅድለት
ቅድስናን ትቶ ሀጢያትን ናፈቀ
በርህንም ዘጋ ማንኳኳቱን ትቶ
ብትዘገይ ማትቀር መሆንህ ተረስቶ
እኔ ግን እላለዉ ማረኝ ይቅር በለኝ
የነርሱ ዉርስ ሀጢያት እኔን አያግኘኝ
እንቁ ማርያም (መባ)


Forward from: የስብዕና ልህቀት
ጨለምተኝነትን ማሸነፍ

ጨለምተኛ ሰው ሁልጊዜም ማለት በሚቻል ሁኔታ ተጠየቃዊ መነሻ (አሳማኝ ምክንያት) ባይኖርም እንኳ መጠራጠርን ፣ ያለማመንን ፣ ልክ ነው ብሎ ያለመቀበልን ይመርጣል። ታዲያ ሰዎች ለምንድን ነው እንዲህ ያለ ጠባይ የሚያዳብሩት? በጉዳዩ ላይ ልዩ ልዩ አመለካከቶችን የሚያራምዱ የተለያዩ የአስተሳሰብ አሉ። አንዳንዶች ሰዎች ልባቸውን ለፍቅርና ለጓደኝነት ክፍት ማድረግን ስለሚፈሩ እንግዳ
ይሆን? ብሎ በማሰብ) ጨለምተኛነትን እንደመከላከያ አጥር ያቆሙታል ሲሉ አመክኖያዊ መከራከሪያ ያቀርባሉ። ሌሎች ደግሞ በአንፃሩ በልጅነት የተስተናገዱ ጉዳቶች (የመንፈስ
መናወጥን የሚያስከትሉ ወይም ሌላ) ሰዎችን «ዝግ» እንዲሆኑ እንደሚያሰገድዱዋቸው ይገልፃሉ።

ራስዎን ከጨለምተኛነት አረንቋ መንጥቀው ወደ ብሩህ አስተሳሰብ እንዲራመዱ የሚያግዙ የተወሰኑ ቀላል ብልሃቶች እነሆ።

1 የችግሩን መኖር ለይተው ይወቁ

እንደ የትኛውም ችግር ለጨለምተኛነትዎ መላ ለመምታት ከሻቱ የመጀመሪያው እርምጃዎ
መኾን ያለበት እንከኑን ለይቶ መረዳት ነው። ጥቂት የማይባሉ ሰዎች የራሳቸውን መራር እውነታ ሳያውቁ ኑሮዋቸውን እንዲሁ ይገፋሉ። ለዓለምና ለህይወት መጥፎ አስተያየት ያላቸው ፣ ቅጭም ያለ ገፅታ የተላበሱ ጠርጣሮች መሆናቸውን ሳይገነዘቡ የማልጎምጎም ህልውናቸውን በዘልማድ ይገፉበታል። ችግርዎን የመረዳት እድለኛነትን በመጎናፀፍዎት ደስ ይበልዎት ፤ ምክንያቱም ካወቁት ወዲያ ለመፍትሄው ለመስራት መነሳሳት ይችላሉ።

2 እያንዳንዷን ጨለምተኛ አስተሳሰብ መንጥረው ይወቁ

ጨለምተኛ ሊሆኑ እንደሚችሉ ከተቀበሉ ቀጣዩ ተግባር በዝርዝር አስተሳሰብዎን መፈተሽ
ይሆናል። በቻሉት አቅም ሁሉ ደጋግመው ራስዎን ይፈትሹ። ይህንን የራስዎን ግንዛቤ እንደሚጨምር የአዕምሮ ስፖርት ይቁጠሩት። ዋናው የዚህ ግብ ከጭንቅላትዎ ምንጭ
የሚንፎለፎሉ ሃሳቦችን በአጉሊ መነፅር ለመመርመርና የአስተሳሰብዎ ገዥነትን ለመቀዳጀት ነው። ሽው የሚሉብዎትን ጨለምተኛ ሃሳቦች ከስረ መሰረታቸው ለመከታተልም ይጠቅምዎታል።


3 ጨለምተኛ ሐሳቦችዎን በተጠየቅ (ሎጂክ) ይሞግቷቸው

አመክንዮ (ሎጂክ) እጅግ አስገራሚ ነገር ነው። አመክንዮ በህይወትዎ እየተከሰቱ የሚበጠብጡ አውዳሚ ስሜቶችንና አሉታዊ ሃሳቦችን ለመቋቋም ይረዳዎታል። ምክንያቱም 99 በመቶው የድብታም ፤ የቁጣዎ ፤ የጭንቀትዎ እና የሌሎችም አሉታዊ ስሜቶችዎ መንስዔ ኢ-ምክንያታዊ
ወይንም አጥጋቢ ምክንያታዊ ድጋፍ የሌለው ነው። ስለዚህ ስሜቶችዎን በተጠየቃዊ ሙግቶች ከተጋፈጧቸው አፍራሽ ሃይላቸው ይቀንሳል።

4 ቀና አስተሳሰብን ለማዳበር አጥርተው ይወስኑ

በህይወት የሚያጋጥመን የትኛውም መልካም ነገር የምርጫ ውጤት ነው። በሆነ አቅጣጫ*ለመራመድ አልያም የሆነ ዓይነት ኑሮን ለመምራት ስንመርጥ ውሳኔያችንን እውን ለማድረግ ብርቱ ጥረት ፅናት ይጠይቀናል

5 በሰዎች መልካም እሴቶች ላይ ያተኩሩ

በመጨረሻ የማቀርብልዎት ብልሃት እኔ በግሌ አዋጭ ሆኖ ያገኘሁትን ነው። በዕለት ተለት የህይወት ውጣውረድ የሚያንጋጥሙንን ሰዎች አሉታዊ ባህርያት ተወት አድርጎ በሰናይ
እሴቶቻቸው ላይ የማተኮርን ቀላል ጥበብ መልመድ በእውነቱ እጅግ ጠቅሞኛል። ለእርስዎም እንደሚበጅዎት አምናለሁ።

ፓውሎ ኩዌልሆ

@Human_intelligence
@Human_intelligence


Forward from: ሰው ካለ ሳይኮሎጂ አለ፡፡
"ደግነትህ በዛ!"
=========
አንድ የ45 አመት ጎልማሳ እግሩን አሞት ወደ ሆስፒታል ይመጣል። የሚያሳየው ፀባይ እጅግ መልካምነት የተሞላ ነበር። ነገር ግን ሚስቱንና ልጆቹን ትቶ የጎዳና ተዳዳሪዎች የሚያድሩበት ቦታ በጉልበቱ እያገለገለ እዛው ነበር የሚያድረው። ሀኪሙ ለማንኛውም ሳንካትሪስት ቢያየው ይሻላል በሚል ወደ ሳይካትሪስት ተላከ።

ሳይካትሪስቱ ሲጠይቀው በድንገት ስራውን እንደተወና ቤተሰቦቹንም ትቶ ለበጎ አድራጎት እንደወጣ ነገረው። ሳይካትሪስቱ በጎ ነገር ለማድረግ ምን እንዳነሳሳው ሲጠይቀው "ምንም አላነሳሳኝም። አንድ ቀን ድንገት ከእንቅልፌ ስነሳ ነው።" ብሎ መለሰ። ይሄኔ ተጠራጥሮ CT scan የተባለውን የራጅ አይነት እንዲነሳ ላከው። ውጤቱ ሲመጣ የፊለፊተኛው የአእምሮ ክፍል ያለ የደምስር ተዘግቶ ስትሮክ (Stroke) አጋጥሞታል።

ሳይካትሪስቱ "ስትሮክ ያሳያል።" ሲለው ታካሚው "እንዴ ስትሮክማ እግርን ወይም እጅን ፓራላይዝ አይደል የሚያደርገው? እኔ እጄም እግሬም ደህና ነው።" ብሎ ይመልሳል። ሳይካትሪስቱ "የደም መፍሰሱ ወይም የደም ስር መዘጋቱ እንደተከሰተበት የአእምሮ ክፍል ይወሰናል። እጅን የሚያዘው ክፍል ከሆነ ፓራላይዝ ያደርጋል። ያንተ ፀባይን የሚቆጣጠረው ክፍል ላይ የተከሰተው። ስለዚህ ከመጠን ያለፈ ለጋስ (Pathologically generous) አድርጎሀል።" አለው።

"እና ደግ የሆንኩት በህመም ምክኒያት ነው?" አለ ፈገግ ብሎ። ሳይካትሪስቱ "አዎ" አለው። ታካሚው "ይሁና ደግነት ደስ የሚል ስሜት ይፈጥራል። እንዳታክመኝ" አለ። ሳይካትሪስቱ ፈገግ ብሎ "ይቻላል።" አለው።....ከChicago Med ሲዝነ አንድ ኢፓሶድ 7 የተወሰደ

ምክኒያቱ ደም መርጋት ቢሆንም ባይሆንም፣
ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም።

ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!
@UoG_Psych


Forward from: ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy
"ሳይንስ ውጫዊውን ምስጢር ሲፈልግ ሃይማኖት ደግሞ ውስጣዊውን ምስጢር ይፈልጋል።"

ሊቅነት ይብቃ። ሊቅነት የማይረባ - ነገር ነው፤ በሳይንስና በሃይማኖት መካከል ድልድይ ሊሆን አይችልም፡፡ ቡድሃዎች እንጂ ስለ ቡድሃዎች የሚያውቁ አያስፈልጉንም፡፡ የሚያስፈልጉን ተመሳጮች፣ አፍቃሪዎች፣ የተግባር ሰዎች ናቸው። ቀኑ ደርሷል፡፡ ሳይንስና ሃይማኖት ተገናኝተው በመታገል ሊጣመሩ ይችላሉ፡፡ ያም ቀን በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ ቀን ይሆናል፤ በዚያ ዕለት የስብዕና መከፋፈል ይጠፋና ቀኑ የደስታ፣ ተነፃፃሪ የሌለው፣ የተለየ ይሆናል፡፡ ከዚያም ሳይንስና ሃይማኖት ተብለው የተከፈሉ ሁለት ነገሮች አይኖሩንም - አንድ ብቻ እንጂ፡፡

የሰው ልጅ ለውጭው ሳይንሳዊ ዘዴን ይጠቀማል፣ ለውስጡ ደግሞ ሃይማኖታዊ ዘዴን ይከተላል፡፡ «ሚስቱዝም» የሚለው ቃል ውብ ነውና ለሳይንስ ወይም ለሃይማኖት ሊያገለግል ይችላል፡፡ «ሚስቱዝም>> የሚለው ቃል የተዋበ መጠሪያ ይሆናል፡፡ ሳይንስ ውጫዊውን ምስጢር ሲፈልግ ሃይማኖት ውስጣዊውን ምስጢር ይፈልጋል፤ እነዚህ ሁለቱ የሚስቲዝም ሁለት ክንፎች ይሆናሉ፡፡ ሚስቲዝም የሁለቱ ውህድ ሊሆን ይችላል፡፡

ከዚህ ውህደት በኋላ ብዙ ውህደቶች ተከታትለው ይመጣሉ። ለምሳሌ፣ ሳይንስና ሃይማኖት በሚስቲዝም ከተዋሃዱ ምስራቅና ምዕራብ ይዋሃዳኑ፣ ወንድና ሴት ይዋሃዳሉ፣ ግጥምና ስድ ፅሁፍ ይወሃዳሉ፣ ሎጂክና ፍቅር ይዋሃዳሉ፣ አንድ ወሰን ከሌላኛው ይዋሃዳል። አንዴ ይህ ከሆነ ፍፁም፣ ምሉዕ፣ ሚዛናዊ ሰው እናገኛለን፡፡

ሳይንስ አሁን ባለበት ሁኔታ የተዛባ ነው፤ ከግምት የሚያስገባው ቁስ አካላዊ ነገሮችን ብቻ ነው፤ መንፈሳዊ ነገሮች ላይ አያተኩርም:: ይህ ደግሞ በጣም አደገኛ ነው::

ሰው ቁስ አካል ብቻ ከሆነ ትርጉም ያለው ነገር በሙሉ ከህይወት ይጠፋል፡፡ ሰው ቁስ አካል ብቻ ከሆነ ሀይወት ምን ትርጉም ይኖራታል? ምን አይነት ቅኔ ይፈጠራል? ጥቅሙስ ምን ይሆናል? ሰው ቁስ ነው የሚለው ሃሳብ ሰውን ክብር ወደሌለው ሁኔታ ዝቅ ያደርገዋል:: ይህ ሳይንስ የሚባል ነገር የሰውን ልጅ ክብር ጠራርጎ ወስዷል፡፡ ለዛም ነው በመላው ዓለም የትርጉም አልባነት ስሜት የተንሰራፋው::

ሰዎች ፍፁም ባዶነት እየተሰማቸው ነው:: አዎ፣ የተሻሉ ማሽኖች፣ የተሻለ ቴክኖሎጂ፣ የተሻሉ ቤቶች፣ የተሻለ ምግብ አላቸው:: ይህ ሁሉ ሃብት፣ ይህ ሁሉ ቁስ አካላዊ ዕድገት ግን ከቁስ አካል፣ ከአካል፣ ከአዕምሮ የላቀ ዕይታ ከሌላችሁ፤ የወዲያኛውን ማጣጣም ካልቻላችሁ ምንም ዋጋ አይኖረውም፡፡ ሳይንስ ደግሞ የወዲያኛውን ዘንግቶታል።

ሳይንስ ህይወትን በሁለት ከፍሎ ያያል፤ የታወቀውና ያልታወቀው፡፡ ሃይማኖተኝነት ህይወትን በሶስት ከፍሉ ይመለከታል፤ የታወቀው፣ ያልታወቀው እና የማይታወቀው:: ትርጉም የሚመነጨው ከማይታወቀው ነው:: የታወቀው ትናንት አይታወቅ የነበረው ነው፡፡ ያልታወቀው ደግሞ ነገ የሚታወቀው ነው:: በታወቀውና ባልታወቀው መካከል ምንም የባህርይ ልዩነት የለም-የጊዜ ጥያቄ ወይም ጉዳይ ነው።

የማይታወቀው በባህርዩ ከታወቀው/ካልታወቀው ዓለም ይለያል፡፡ የማይታወቅ ማለት ሚስጥር አለ ማለት ነው፤ የፈለገ በጥልቀት ብትገቡበት ምስጢሩን ልትፈቱ አይቻላችሁም:: በጥልቅት በገባችሁ ልክ ምስጢሩም የበለጠ ጥልቅ ይሆናል፡፡ ይህ አይነቱ ምስጢር ፈላጊ በፍለጋው ሊገፋ በማለዳ ፀሃይ እንደሚጠፋ ጤዛ ህይወቱም እንዲያ የሚሆንበት ጊዜ ይመጣል። ይሄኔ ምስጢሩ ብቻ ይቀራል፡፡ ይህ የእርካታ ጫፍ ነው፤ ሰውየው ቤቱ ደርሷል ማለት ነው። ይህንንም እግዚአብሄር፣ ኒርቫና ወይም የፈለጋችሁትን ልትሉት ትችላላችሁ::

እኔ ሳይንስን አልቃረንም - አቀራረቤ በመሰረቱ ሳይንሳዊ ነው። ነገር ግን ሳይንስ ውሱንነቶች አሉበት። እኔ ሳይንስ በቆመበት አልቆምም፤ ከዚያ አልፌ ርቄ እሄዳለሁ።

ሳይንስን ተጠቀሙበት እንጂ መጠቀሚያው አትሁኑ:: ትልቅ ቴክኖሎጂ መያዝ መልካም ነገር ነው፡፡ እንዲህ አይነት ቴክኖሎጂዎች ካላስፈላጊ ስራ፣ ካላስፈላጊ ጭቆና ያወጣሉ፡፡ ቴክኖሎጂ ለሰውም ለእንስሳትም ሊጠቅም ይችላል፡፡ እንስሳት እየተጠቀምንባቸው ስለሆነ ስቃይ ውስጥ ናቸው፡፡ ማሽኖች እነዚህን እንስሳት ተክተው ሁሉን ስራ ሊሰሩ ይችላሉ. .. ሰውና እንስሳት ነፃ ሊሆኑ ይችላሉ::

የሰው ዘር በሙሉ ከስራ ነፃ እንዲሆን እፈልጋለሁ - ምክንያቱም - ከስራ ነፃ ስትሆኑ በስነ - ውበት፣ ስሜታዊነት፣ መዝናናት፣ ተመስጦ ረገድ ማደግ ትጀምራላችሁ፡፡ የበለጠ ጥበበኛና መንፈሳዊ ትሆናላችሁ- ምክንያቱም በቂ ጊዜና ሃይል ይኖራችኋል፡፡

እኔ ሳይንስን ተቃዋሚ አይደለሁም፤ ፍፁም ሳይንስን አልፃረርም፡፡ ሰው ለትልቅ ነገር ዝግጁ እንዲሆን፣ አንድ ምስኪን ሊያገኘው የማይችል ትልቅ ነገር፣ ዓለም በብዛት ከሳይንስ ተቋዳሽ እንድትሆን እፈልጋለሁ፡፡

ሃይማኖት የድሎት መጨረሻ ነው፡፡ ድሃው ሰው ስለ ቁራሽ ዳቦ እንዲያስብ ተገድዷል፡፡ ማግኘት ስላልቻላቸው መጠለያ፣ ልብሶች ሊያስብ የግድ ነው:: መላ ህይወቱ ዋጋ ቢስ በሆነ ነገር የተጨናንቀ በመሆኑ ለአምላኩ የሚሆን ጊዜና ስፍራ አይኖረውም።

ምንጭ ፦ ህያውነት ፫ (ኦሾ)
ትርጉም ፦ ሀብታሙ ተስፋዬና
ተስፋሁን ምትኩ

@Zephilosophy
@Zephilosophy


· 

የሰርጉ አልበም ላይ ይሄ ፎቶ የለም… የሙሽሮቹ የወጪ ዝርዝር ውስጥ ግን በግልፅ ይታያል… የደሃ ህይዎት ላይ ይሄ የለም… የደሃ ህልም ውስጥ ግን ከእንቅልፍ የበለጠ ስፍራ አለው።

የአንዱ ተራ ጉዳይ ለሌላው ህልም ነው ህልሜን ለምን አልኖርኩም ከሌላው ለምን አነስኩ? ብለህ አትጨነቅ አንተ ሳታውቀው የህልምህን ቀን ትኖራለህ ጉጉትህ ጉልበት ይሁንህ ወደፊት እንድትራመድ… ትግስትህ ተስፋህን ያፋፋ ነገን በደስታ እንድጠብቅ… ሌላው በአንተ እጅ አይደለም ተወው አትጨነቅለት ማንም በራሱ 100% አቅም የትም ቦታ አልደረሰም።

Nuri Sultan



Share and join https://t.me/yeemom


Forward from: የሜሪ አጫጭር ተረኮች
ስህተት ልክነት
ልክነት ስህተት

የእኔ ‘የልክነት ጥግ‘ ነው ብዬ ያመንኩበት ‘እውነት‘ ለወዳጄም ‘እውነቱ‘ መሆን አለበት ብዬ ወዳጄን በተሳሳች ሂሳብ መዳኘት ከቂልነቴ ባሻግር የጠበበ የሀሳብ ምህዳሬን ገልቦ አደባባይ ማስጣት ይመስለኛል።

ወዳጄ የቆመበትን ጫማ ‘ስህተት‘ ብዬ ለመዳኘት ለመሆኑ የእኔ ‘ልክ‘ በየትኛው ሚዛንና በማን ዳኝነት ተሰፍሮ ነው ልክነቱ የተረጋገጠው?

አይደለም ለሌላ ሰው ለራሴ እንኳን ‘ልክ ነው‘ ያልኩትን እምነቴን ጊዜ አላንጓለለብኝም? የዛሬ ምናምን ዓመት በፊት የእውነትና የእምነት ጫፍ የመሰለኝ ዛሬ አልተቀየረም? በጠበበም ወይ በሰፋ አስተሳሰቤ 'ልክነቴ'ን አልቀየርኩም?

እንዴት ነው በጊዜ፣ በመረዳቴ መጠን፣ በቦታና በበሽቃጣ የህይወት ክስተቶች እንደማይቀየር ዋስትና በሌለኝ ‘ልክነቴ‘ ወዳጄን በስህተት የምዳኘው?

ሊቀያየር ቢችልም እንደብዙዎች የራሴ አቋምና እምነት አለኝ። እንደራሴ ‘ልክ‘ እና ‘ስህተት‘ የምላቸው ሁነቶች አሉኝ። …… የኔ ‘ስህተት‘ ውስጥ ተዘፍቀህ ሳገኝህ… … ልልህ የሚገባው ‘ይመስለኛል‘ ብቻ መሰለኝ። ምክንያቱ ደግሞ የእኔ ልክ የልክ ጣሪያ ሊሆን አይችልም። የሆነ ቦታ……የሆነ ጊዜ… … ለሆነ ሰው ስህተቱ ሊሆን ይችላል።……

እኔና አንተ አንድ ቦታ ላይ በተለያየ አቅጣጫ ፊታችንን አዙረን ብንቆም የእኔ ቀኝ ያንተ ግራ ነው። …… ያንተ ግራ የኔ ቀኝ ነው። …… ቀኝ ይሄ ነው…… ግራ ይሄ ነው… … ብዬ ብከራከርህ ቂል ነኝ። …… እንዳንተ አቋቋም ያንተ እውነት ይሆናል። …… እንደ እኔ አቋቋም ደግሞ የእኔ እውነት ይሆናል። …… ባንተ እውነት ለማመን ያንተን ጫማ መዋስ አለብኝ።…… የቆምኩበት ሆኜ ለስህተትህ ሒሳብ እየሰራሁ ስዳኝህ እቀሽማለሁ። ………

በየራሳችን እውነትና እምነት መከባበርና እና መዋደድ በአብሮነት ብዙ ያስጉዘናል።

እየሆነ ባለው አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ውብ ቀን ውብኛ አዋዋል ዋሉልኝ❤️❤️❤️❤️❤️




┄┄┄┄┉✽‌»‌🌹 ✿ 🌹»‌✽‌┉┉┄┄┄
ግመልን ስትጠይቅ ቀበሮነትህን አትርሳ

ግመሉ ወንዙን እንደተሻገረ ቀበሮውም ለመሻገር መጣና ስለወንዙ ጥልቀት ለማወቅ ከወንዙ በወድያኛው ዳር ያለውን ግመል ጠየቀው። ግመሉም ጥልቀቱ ጉልበት ድረስ እንደሆነ ነገረው።

ቀበሮውም ጉልበት ድረስ ከሆነማ አያሰምጠኝም በማለት ለመሻገር ወደ ወንዙ ገባ። በሚያሳዝን ሁኔታ ወንዙ
ያሰምጠው ጀመረ። ይሄኔ ቀበሮው ግመሉ እንደሸወደው ተረዳና እንደምንም ተፍጨርጭሮ ወደ ነበረበት ተመለሰ፤ ራሱንም ከሞት አተረፈ።

ይሄኔ በንዴት ጮክ ብሎ "አንተ ያምመሀልን? ጥልቀቱ ጉልበት ድረስ ነው አላልክምን?" አለው።

ግመሉም "አዎና! ታዲያ በራሴ ጉልበት ነው እንጂ ያልኩህ ባንተ ጉልበት መች አልኩህ?" በማለት መለሰለት። ቀበሮው በልምድ የቀደመውን አካል መጠየቁ ትክክል ቢሆንም የግመሉን ማንነት መርሳቱ ግን ስህተት ነበር። ግመሉም ልምዱን ማካፈሉ ትክክል ቢሆንም የቀበሮውን ማንነት ግን መርሳት አልነበረበትም።

ሁለት ሰዎች ሲነጋገሩ እንደየራሳቸው ተሞክሮ ቢነጋገሩም የአንዱ ልምድ ለሌላው መፍትሔ ሊሆን ግድ አይደለም። ባይሆን የአንደኛውን የህይወት ልምድ ለሌላኛው መጥፊያው ሊሆን ይችላልና ጥንቃቄ ማድረጉ ግድ ይላል። ለምሳሌ አንድ ሁለት ሴቶች አረብ ሀገር ሰርተው ተመልሰው ውጤታማ ቢሆኑ ሁሉም አረብ ሀገር የሄደ ሰው ውጤታማ ይሆናል ማለት አይደለም፡፡ ስለዚህ የሰዎችን የህይወት ተሞክሮ ወደ እራሳችን ህይወት አምጥተን ለመትግበር ስንዘጋጅ ማስተዋልና ጥንቃቄ አይለየን፡፡

መልካም ቀን
┄┄┄┄┉✽‌»‌🌹 ✿ 🌹»‌✽‌┉┉┄┄┄

✌️ 😳 😜


Forward from: ሰው ካለ ሳይኮሎጂ አለ፡፡
#መሰላቸትን_ለራስህ_ፍቀድ

የአብዛኞቻችን ሕይወት ስራችንን ብንተው እንኳን ትኩረታችንን በሚሰርቁ ድርጊቶች የተሞላ ከመሆኑ የተነሣ ለትንሽ ደቂቃ እንኳን ምንም ሣንሰራ ዘና ብለን መቀመጥ አንችልም። አንድ ጓደኞዬ “ሰዎች ሰብአዊ ፍጡራን መሆን አቁመው ሰራተኛ ፍጡራን ሆነዋል” ብሏል።
አልፎ አልፎ መሰላቸት የሚኖረውን ጥቅም የተረዳሁት ከዋሽንግተን ወጣ ብላ የምትገኝ ትንሽ ከተማ ውስጥ የንግግር የስነ ልቦና ሕክምና በምማርበት ጊዜ ነው። ከተማዋ ትንሽ ስለነበረች ብዙ የሚደረግ ነገር አልነበረም። የመጀመሪያ የትምህርት ጊዜ እንዳለቀ አስተማሪዬን “እዚህ አካባቢ ማታ ማታ ምን ማድረግ እችላለሁ?” አልኩት። እሱም “ራስህን እንድትሰላች ፍቀድለት። ምንም አታድርግ። በዛ ላይ መሰላቸትን መልመድ የትምህርትህ አንድ አካል ነው።” አለኝ። በመጀመሪያ እየቀለደ መስሎኝ ነበር። “ለምንድነው በገዛ እጄ እንድሰላች የማደርገው?” ብዬ ጠየቁት። እሱም እራሴን ለአንድ ሰዓት ያህል እንኳን እንድሰላች ከፈቀድኩለት እና የሆነ ጊዜ ማሣለፊያ ነገር ከማድረግ ከተቆጠብኩኝ የመሰላቸቱ ስሜት ወደ ሰላማዊ ስሜት እንደሚለወጥ አስረዳኝ። ሳይዋጥልኝ ተቀበልኩት።

ከሞከርኩት በኋላ እሱ እንዳለኝ መሆኑን ሣይ በጣም ተገረምኩ። መጀመሪያ መሰላቸቱን መቋቋም ከባድ ነበር። ጊዜ ማሣለፊያ የሆነ ነገር ማድረግ ስለለመድኩ መጀመሪያ ላይ ዘና ለማለት ተቸግሬ ነበር። ከትንሽ ጊዜ በኋላ እየለመድኩት መጣሁ። ከዛ እንደውም በጣም እያዝናናኝ መጣ። እየተናገርኩ ያለሁት ለሰዓታት ያለ ስራ በስንፍና ስለመቀመጥ ሣይሆን ዘና የማለትን ጥበብ ስለመማር ነው። ምንም ነገር ሣያደርጉ እራስን ሆኖ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ዘና ማለት። የተለየ ዘዴ አያስፈልገውም በቃ አስበንበት ለተወሰነ ጊዜ ምንም አለመስራት ብቻ ነው። ረጋ ብሎ ተቀምጦ ሀሣባችንንና ስሜታችንን ማጤን። መጀመሪያ ላይ የተወሰነ ሊጨንቀን ይችላል። በተለማመድነው ቁጥር እየቀነሰልን ይመጣል። የምናገኘው እርጋታ ደግሞ ከፍተኛ ነው።

አብዛኛው ጭንቀቶች የሚፈጠሩት አዕምሯችን በጣም እየሰራ፣ የሚያተኩርበት ነገር ፍለጋ ሲባዝን ነው። አንድ ስራ እየሰራ ስለሌላ ስራ ያወጣል ያወርዳል። “ከዛስ?” ሲለን ምሣ እየበላን ቡና የት እንደምንጠጣ እናስባለን። ቡና እየጠጣን ስንጨርስ የት እንደምንሄድ እናውጠነጥናለን። ሳምንቱ ሊያልቅ ሲል ቅዳሜና እሁድ ምን እንደምንሰራ እናቅዳለን። ቤታችን እንደገባን በቀጥታ ቲቪ ወይም ፌስ ቡክ እንከፍታለን፤ ወይ ስልክ እንደውላለን፤ ወይ መፅሀፍ እንገልፃለን፤ ወይ የሆነ ነገር መስራት እንጀምራለን። ለደቂቃ እንኳን ምንም ነገር ሣንሰራ መቀመጥ የሚያስፈራን ነው የሚመስለው። ምንም ነገር ሣይሰሩ መቀመጥ እንዴት ዘና ማለት እንደምንችልና አዕምሯችን አንዴት ተረጋግቶ ማሰብ እንደሚችል ያስተምረናል። መሰላቸት ማለት ለአዕምሯችን “ቆይ አሁን አይደለም” ብለን ዘና የምንልበት ነፃነት እንደመስጠት ነው። ልክ እንደአካላችን አዕምሮአችንም ከጥድፊያ ኑሮ ጋብ የሚልበት እረፍት ያስፈልገዋል። አዕምሮአችን እረፍት ስንሰጠው በጣም ጠንካራ፣ ፈጣንና ትኩረት ማድረግ የሚችል ሆኖ እናገኘዋለን።

እንድንሰላች ለራሣችን ስንፈቅድ በያንዳንዱ ቀን በየአንዳንዱ ደቂቃ መስራት ያሉብን ነገሮች ከሚያሳድሩብን ከፍተኛ ጫና አእምሯችን ለተወሰነ ጊዜ “እፎይ” እንዲል እናደርገዋለን።
ከሁለቱ ልጆቼ አንዳቸው እኔ ጋር መጥተው “አባዬ ሰለቸኝ።” ሲሉኝ “በጣም ጥሩ ለትንሽ ጊዜ እንደዚሁ ቀጥሉ ይጠቅማችኋል” እላቸዋለሁ። እንደዚህ ማለት ከጀመርኩ በኋላ እየመጡ የሆነ ነገር እንዳደርግ መጠየቃቸውን አቁመዋል። የሆነ ሰው “እራስን እንድትሰላች ፍቀድ” ይለኛል ብላችሁ አስባችሁ አታውቁ ይሆናል። ያ የሂደቱ መጀመሪያ ይመስለኛል።

ከ"ቀላሉን ነገር አታካብድ" መፅሀፍ የተወሰደ
@UoG_Psych

20 last posts shown.