መንገሻ አየነ (ዶ/ር) የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመደቡ፡፡
መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ከሰኔ 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መመደባቸውን ሰኔ 10/2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ የወጣ የምደባ ደብዳቤ ያሳያል፡፡
የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸውን ተከትሎ፤ ፕ/ር እሰይ ከበደ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው በመወከል ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡
አዲስ የተመደቡት የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ፤ ከመስከረም 2014 ዓ.ም ጀምሮ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡
@tikvahuniversity
መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ከሰኔ 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መመደባቸውን ሰኔ 10/2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ የወጣ የምደባ ደብዳቤ ያሳያል፡፡
የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው መሾማቸውን ተከትሎ፤ ፕ/ር እሰይ ከበደ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው በመወከል ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡
አዲስ የተመደቡት የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ፤ ከመስከረም 2014 ዓ.ም ጀምሮ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡
@tikvahuniversity