Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦
1) ከቁርኣን፣
2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ]
3) ከታማኝ ዑለማዎችና
4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል።
√ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ።
√ አላማዬ በዲኔ ላይ ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው።
ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @Murad_Tadesse ላይ አስፍሩት።
ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ።
ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹
Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②②③②]👌


#ቁርኣን

7.3k 0 10 28 142

በውስጥ መጥቶ አንዱ፦
«ድሮ ሙስሊም ነበርኩ፤ አሁን ግን እድሜ ለእፎይ ከእስልምና ወጥቻለሁ!»

እኔ፦ «ኦ! ይገርማል! እና ሙስሊም እያለህ ሰላተል ጀናዛ ስንት ሰዓት ላይ ነበር የምሰግደው?»

እሱ፦ «ቀን 10 ሰዓት ላይ!»

እኔ፦ እውነትም አንተ ጀናዛ ነህ¡


©: ከፌስቡክ መንደር የተገኘ


ተው! ልተኛበት… በጾሙ አታስቀልዱኝ¡

7.8k 0 13 53 667

ሲያሳዝኑ¡


በቃ! ለኮፒ ሊንክ ሰሑር ላይም ከኛው ጋ ሊነሱ ነው¿

8k 0 8 74 258

እናንተም ሪፖርት ማድረግ እንዳይረሳ።

ለብዙ ሰው ሼር በማድረግና በብዙ ሰው አካውንት በመግባት በዙሪያችሁ ያለውን ሁሉ አሰባስባችሁ ሰሑር ላይ ሪፖርቱን አዝምቱት።

8.2k 0 12 51 225


8.7k 0 7 43 550

አሁን'ማ ጭራሽ በየ 30 ደቂቃው ጋፕ ሊሆን ነው እንደ?

ለካ ለዚህ ነው ቅጥል ብለው ከውይይት ይልቅ ብሽሽቅና ጸያፍ ስድብ ውስጥ የገቡት?

8.8k 0 6 74 608

በየሰዓቱ እየሆነ ያለው ይህ ነው። ከስድብና ጥላቻ የጸዳ ሰላማዊና ኢስላማዊ አስተምህሮ!

እንዳውም ስድብ ሲከሰትም በትዕግስት አሳልፎ በመልካም ቃላት መመለስ! ወንድማችን ሑሴን አላህ ይጨምርለት።

እንኳን ለብዙ ሰው ለአንድ ሰው የሂዳያ ሰበብ መሆን በራሱ ትልቅ መታደል ነው። አላህ ኢኽላሱን ይወፍቀው።

9.3k 0 2 110 652

«ሁሉም ባለ ማተብ እፎይ ነው!»

«እፎይ ለኔ የተዘመኑ ጳውሎስ ነው!»

ይህ ቅድም የተሳዳቢው እፎይ መንጋዎች በቴሌግራም ካደረጉት Live ምክክር በኋላ ወደ ቲክቶክ መንደር ሂደው ሲዶልቱ ከነበሩት ድምፅ ላይ ያስቀረሁት ነው።

ነውረኛውን ግለሰብ በዚህ ደረጃ ነው እየደገፉት ያሉት። ከአንደበታቸው እንደምትሰሙት፤ አንድ ጊዜ በአንዳቸው የቲክቶክ አካውንት፣ ሌላ ጊዜ በሌላኛው እየተቀያየሩ Live በመግባት ሚስኪኑን ህዝብ ጥላቻ፣ ሐሰተኛ መረጃና «ተጠቅተናል» አይነት ቁጭት እየጋቱ ስሜታዊ በማድረግ ወደ አላስፈላጊ ነገር እንዲያመራ እያደረጉት ነው።

እየተቀያየሩ ቀን ሙሉ ቲክቶክ Live ላይ ናቸው። ኧረ! ያ ጸያፍ ቃልና አገላለፅ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚልን አይወክልም ብንላቸውም፤ በግድ ግብራችን ነው ብለዋል። አናስገድዳቸውም። አዎ! እፎይ ናቸው። እፎይ ብሎ መናገር በራሱ እንደ ስድብ የሚቆጠር ቃል እስኪሆንና መጨረሻውን ሲያዩ አናውቀውም እስኪሉ ድረስ መታገል አለብን። ሐቅ ያሸንፋል።


የቲክቶክን መንደር ለነርሱ የሐሰተኛና ጥላቻ ሰበካ መድረኩን መልቀቅ የለብንም።

ቲክቶክ የምትጠቀሙ ወንድምና እህቶች እናንተም ሐቅ ከኛ ነውና ኮንተንቶችን ሥሩ። እነርሱ ያንን ነውረኛ ታቅፈው ያላፈሩትን እኛ በሐቅ አናፍርም።


እንደየአስፈላጊነቱ ስለምጠቀመው ቲክቶክ ላይ ላላችሁ ይህ የኔ አካውንት ነው።
በዛ ሰፈርም ብቅ ብለን ሐቅን ማሰራጨት፣ ውሸትን ማጋለጥ፣ ጥላቻን መዋጋትና ሰላምን መስበክ አለብን።


ፎሎው አድርጉት።

https://www.tiktok.com/@muradtadesse?_t=ZM-8ud8gKHzvzq&_r=1


እናንተም ፎሎው ተደራረጉ።

10.5k 0 23 22 258

ሁሉንም ነውረኛ ስድቦቻቸውን ከእፎይ ጀምሮ ከላይ እስከ ታች ያሉትን በሙሉ፤ በቪድዮ፣ በጽሑፍ፣ በድምፅና በምስል የሚጋራበት ራሱን የቻለ የቴሌግራም ቻነል ተከፍቷል።

በዚህ ሊንክ ግቡ።


t.me/ArrestEffoy

ያንን ሁሉ ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ከግብረ ገብነት የወጣ፣ እንኳን ኃይማኖተኛ ነኝ ከሚል ሰባኪ ከተራ ዱርዬ እንኳ የማይጠበቅ ብልግና ጭምር ያፍሩበት ዘንድ፣ እውነትም የርሱ ደጋፊ መሆናቸውን ከልብ ይመሰክሩ ዘንድ ይለቀቅበታል።

በዚህ የጥላቻ ሰበካ የሚፈለጉ ግለሰቦች በፎቶና አድራሻቸው ይለቀቃል።

ቻነሉን ለሌሎችም አሰራጩት!


አይገባችሁም እንጂ… ተመልከቱ ምን እንደሚባባሉ!

እናንተ ትርጉም የሌለው ይመስላችኋል ኣ? ይሄው የአንግሪ 😡 ኢሞጇን ንኩ እየተባባሉ ነው።


በሉ! እናንተ ግን ❤️ ንኩለት።




እነ ቅመም ሁሌ መናገር አለብኝ እንደ?

ፍጠኑ ወደ ❤️ ሪአክሺን!

የሆነ የላላ ቡለን ካለ ላጥብቅላችሁ፣ ተመሳሳይ ሃሳብ አታስደጋግሙኝ።

14.5k 0 12 63 550

ወይ ጣጣ…

«ቢሰርቁ እዳ፣ ቢለምኑ አይሰጡ!» እንዲሉ አበው።

ደግሞ ቀሲሱ ሶለዋት ስላደረገ ሰልሟል በሉና ፈስሩታ¡

እዛው በጸበልሽ ብሏል¡ የለሁበትም!


የእፎይ አካውንት ከተዘጋ፤ አለቀልን‼
=========================

የዛን እፎይ የሚባል ባለ'ጌ ልጃቸውን ገመና አቅፈው ሳያፍሩበት በኩራት አሁን በሚስጥር Live ላይ እየተወያዩ ነበር።

(የድምፅ ሪከርዱን እዚህ ላይ አዳምጧቸው'ማ።
https://t.me/MuradTadesse/40462)

«የኃይል ሚዛኑን ወደኛ ማምጣት አለብን፣ አጀንዳ ማስቀየስ አለብን፣ ከተከሳሽነት ወደ ከሳሽነት እናምራ፣ አካውንቱ እንዳይዘጋበት ኮፒ ሊንክ እናድርግ… » እያሉ መክረዋል።

አንዷ ያሳቀችኝ … "የሚሉትን ሚስጥር ልንገራችሁ!_" አለችና «እነርሱ እንደተኙ ሰሑር ላይ ሪፖርት እናድርግ ስለተባባሉ ኮፒ ሊንክ እናድርግ!» ብላ ትናገራለች። በርሷ ቤት በፐብሊክ ግሩፕ ላይ አንዱ የፃፈውን አይታ ሚስጥር አግኝታ ሞታለች።



ለማንኛውም ወጥራችሁ ሪፖርት አድርጉና አንዱ የጥላቻ ልሳናቸው ይዘጋ።

አሁን ደግሞ ወደ ሌላ ወደሚያሴሩበት መርሃ ግብር ስለሄዱ፤ እኔ ልከተላቸውና ልሂድ።

በተለያዩ አደረጃጀቶች እያሴሩ እንደሆነ ገልፀዋል። የሁሉንም ተሳታፊና ተናጋሪ ሙሉ ስም ይዣለሁ። የአንዱ አደረጃጀት ከተገኘ ሲቀፈደድ ሌላውን ይጠቁማል። ግን የሚመለከተው የመንግስት አካል ነገሩ ፈር ሳይለቅ ወንጀለኞችንና በየቦታው የሚያሴሩትን ለቅሞ በአስቸኳይ ስርዓት ቢያሰፍን ጥሩ ነው።


እናንተ ወደ ብዙ ሰው በማሰራጨት ሪፖርት አስደርጉ፣ አድርጉ።

ሌላው ደግሞ ሲመቻቸው «መና'ፍቅ» እያሉ እንዳላሳደዷቸው ሁላ፤ "ፕሮቴስታንቶችንና ካቶሊኮችን እየሱስ የናንተም ነው!" ብለው ስትራቴጂክ አጋር ለማድረግ ጥሪ አቅርበውላቸዋል። ሞኝ ካልሆነ በስተቀር "ራሳችሁን ቻሉ!" ነው የሚላቸው። ሲቀጥል እየሱስ ከማንም በላይ የኛ ነው። እንወደዋለን፣ የአላህ ሰላምና እዝነት በርሱ ላይ ይስፈንና!

ከፈለጉና ባለጌው እኛንም ይገልፃል ካሉ ያግዟቸው። እኛ ምን አገባን! በዛ ብልግና ንግግር አፍረው መደበቅ ሲገባቸው ገፍተው መጥተዋል። በመጡበት መልሶ፣ ጥላቻቸውን አለዝቦ፣ ወንጀለኛቸውን ለፍርድ አቅርቦ አደብ ማሲያዝ ያስፈልጋል።

ሪፖርት አድርጉ።

ከሪፖርት በተጨማሪ ቀጥታ ወደ ቲክቶክ ካምፓኒ የምንልከው ኢሜይል ይኖረናል ከቀናት በኋላ። በባሌም በቦሌም መዘጋት አለበት።

እነርሱ ለሐሰትና ለብልግና ይህን ያክል ከወገኑ፤ እኛ ሐቅ ይዘንና ተበዳይ ሆነን መሳነፍ የለብንም።

17.5k 0 73 76 639

በእንግሊዝኛ እነዚህን 5ቱን ነጥቦች ለየብቻ አድርጋችሁ ኮምቷቸው።

በዚህ ፖስታቸውና በሌሎችም ከኃይማኖት ጋር ተያይዞ እየደሰኮሩ ባሉት ላይ እውነታውን ንገሯቸው።
https://www.facebook.com/share/r/1FTKB8MbHm/

ተሳዳቢዎችና ጥላቻ ሰባኪዎች ለፍርድ ካልቀረቡ፤ ስለ መቻቻልና መከባበር በወሬ ደረጃ ቢወራ ውሃ ይቋጥራል እንደ? ሃሳቡስ እንደ ሊዋጥ ይችላል? መጀመሪያ አጥፊዎች ከነ ግብረ አበሮቻቸው ተጠያቂ ይደረጉ፣ ለፍርድ ይቅረቡ።

①)We, the Muslim community, stand against spiritual hatred of our Prophet Muhammad (PBUH) and his Beloved Ones (Salawatullah). The speech of hate has no right to live in our society. Therefore, law and religious diversity have to be adhered to! #JusticeForMuslims #ArrestEphoy #StopHateSpeech #Ethiopia #ReligiousFreedom #Accountability 


②)The public should not take lightly the dangerous effect of Ephoy (Solomon Shiferaw)'s dangerous speech which aim against Islam and Prophet (PBUH). The code of silence by the public is not sensible. Who can be held accountable to avoid repetition of this? #ProtectReligiousHarmony #NoToHate #Ethiopia #JusticeNow #ArrestEphoy #HateSpeechIsNotFreeSpeech 

③)Interference with the sanctity of Allah, Islam, and the Prophet Muhammad (PBUH) is not freedom of speech; that is hate speech by itself. Thus, the man himself, Ephoy (Solomon Shiferaw), who said so, must be brought to justice. It is our obligation that we as society do not tolerate this criminal action. #RuleOfLaw #Ethiopia #NoToHate #ArrestEphoy #JusticeSystem #ProtectMinorities 


④) 
Urgent intervention is required! Ephoy (Solomon Shiferaw) is a harsh critic of Islam. Therefore, arrest him and make sure that law is being in place! #ArrestEphoy #HateSpeech #Ethiopia #Justice #Islamophobia


⑤)Ephoy through such words has directly affected an end to the peace and unity of Ethiopia. Plead hereby with the authorities to swiftly take legal action and prosecute him for his dangerous rhetoric. To begin with, we have to join hands against hate. #EthiopianUnity #Peace #NoToHate #ArrestEphoy #JusticeForAll #ReligiousTolerance


EBC ከሦስቱም ኃይማኖቶች ተወካዮች ብሎ ቀጥታ ስርጭት እያስተላለፈ ነው።


በዚህ ሊንክ ግቡና ንገሯቸው።


https://www.facebook.com/share/v/1AC9pKsy47/



ፍትሕ ሳይሰፍን፣ የጥላቻ ሰባኪው ፍርድ ሳይሰጠው፣ … በባዶ ወሬ ስለ ኃይማኖት መቻቻልና መከባበር ማውራት ራስን መሸወድ ነው በሏቸው።


#BringHimToJustice


እነ ሲወልዱ አይታ በጠጧን ጣለች…

«ፍትሕ ያለ ጥፋቱ የሞት ጅሀድ ለታወጀበት እፎይ!» አላሉም።

መካድንማ እነርሱ ይካዷት።

ሰው ግን እንደት ውስጡ እውነታውን እያወቀ፤ አስችሎት በአፉ ይዋሻል?

አወይ ኃይማኖተኝነት!

እምነትን ከውሸታምነት ካልታደገ ምንድን ነው በግለሰቡ ላይ ያሳደረው ተፅዕኖ?


በEBC የፌስቡክ ገፅ በዚህ ፖስት ስር ከላይ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ገፅ ኮምቱ ያልኳችሁን ኮምቱ።


https://www.facebook.com/share/1BLpt3vYGd/



እነርሱ ትናንት አንሻፈው ነው ዘገባ የሠሩት። የጋራ ሚዲያ ሆነው ማንሻፈፍ ነውር ነው። ንገሯቸው!

አሁን ሚዛናዊ ሚዲያ ሊመስሉ የጋራ ጾም፣ የሀኘኃይማኖት መቻቻልና መከባበር… ይላሉ። መጀመሪያ ከአንድ የህዝብ ሚዲያ የሚጠበቅ ሥራ ይሥሩ።


 ማኅበራዊ ሚድያን በመጠቀም በግለሰቦችና በቡድኖች እየተፈጠረ ያለውን ሃይማኖት ለበስ ችግር መንግሥት የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል ባወጣው ሕግ መሠረት ሕግን የማሰከበርና ተጠያቂነት እንዲያሰፍን የማድረግ ኃላፊነቱን እንዲወጣ እንጠይቃለን።

 ችግሩ የማኅበረሰብ የጸጥታ እና የሰላም ዕጦት ፈተና ከመሆኑ በፊት የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ለችግሩ ልዩ ትኩረት በመስጠት እና ተገቢውን ክትትል በማድረግ መንግስታዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን።

 ንጽጽራዊ ትምህርተ ሃይማኖት ወይም ዕቅበተ እምነታዊ ሥራዎች ለማኅበረሰቡ አስተማሪ በሆነ መልክ በሃይማኖት ሊቃውንቶች መካከል የሚደረግ፣ በሥርዓትና በመከባበር የሚከወን እና ስክነትና ሥነ-ስረዓት የሚጠይቅ መሆኑን ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል።

ይሁንና ማህበራዊ ሚድያን በመጠቀም ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን ሆነ ንጽጽራዊ ትምህርቶችን የሚያቀርቡ ወገኖች እነዚህን መርሆዎች ባከበረ መልኩ እንዲያከናወኑና ለትውልዱ አርኣያ በመሆን ለዘመናት በህዝባችን መካከል የቆየውን አብሮነትና ወንድማማችነትን በማይጎዳ መልኩ እንዲተገብሩ አባታዊ ምክራችንን እናስተላልፋለን፡፡

እንደሚታወቀው ጊዜው በክርስትና እና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ወርኃ ጾም በመሆኑ ለሀገራችን እና ሕዝባችን የፈጣሪን ቸርነትና ምህረት እዝነት የምንለምንበት የተለየ ጊዜ ነው፡፡  

በዚህ የጾም ጊዜ እንደዚህ ዓይነት ችግር መፈጠሩ አሳዛኝ ቢሆንም፥ በሌላ መልኩ እየተፈጠረ ያለውን ይህንን አሳሳቢ ጉዳይ ወደ ፈጣሪ ለማቅረብ ዕድል የሰጠ በመሆኑ መላው የከተማችን የክርስትና እና የእስልምና እምነት ተከታዮች በጽሞና እና በትህትና ወደ ፈጣሪ በመቅረብ ፈጣሪ ለሃገራችን ጽኑ ሰላምን እንዲሰጥልን ልንማጸን ይገባል ሲል ጉባኤው ለሀሩን ሚድያ በላከው የአቋም መግለጫ አስታውቋል።

©ሀሩን ሚድያ

16k 0 3 4 154

የአዲስ አበባ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ነብዩ ሙሀመድ "ﷺ" እና እስልምናን የዘለፈውን ግለሰብ ተግባር አወገዘ!


የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በማኅበራዊ ሚድያ ሃይማኖትን በመጠበቅ ሽፋን እየተሰራጩ ስለሚገኙት የጥላቻ እና ጠብ ጫሪ መልእክቶችን አስመልክቶ ወቅታዊ መግለጫ አውጥቷል።

ጉባኤው በመግለጫው ከሰሞኑ በአንድ የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ ነኝ በሚል ግለሰብ የእስልምና ሃይማኖት ነብይ በሆኑት በነቢዩ መሃመድ ሰ.ዐ.ወ ላይ ክብረ ነክ እና ኢ-ሥነ ምግባራዊ ንግግሮች መነገራቸው ተከትሎ የእስልምና እምነት ተከታዮችን ብቻ ሳይሆን ብዙዎችን ያሳዘነ ጉዳይ ሆኗል። ይህ ድርጊት ሁሉም ማህበረሰብ ሊወግዘው የሚገባ ተግባር መሆኑን አንስቷል።

የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ይህ ዓይነቱ ኢ-ሥነ ምግባራዊ እና ሕገ ወጥ ተግባር የትኛውንም የሃይማኖት ተቋም የማይወክል፣ ይልቁንም የሚወገዝ ተግባር መሆኑን ገልጿል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ይዘት እንደሚከተለው ቀርቧል።

በማኅበራዊ ሚድያ ሃይማኖትን በመጠበቅ ሽፋን እየተሰራጩ ስለሚገኙት የጥላቻ እና ጠብ ጫሪ መልእክቶችን አስመልክቶ ከአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ

የተከበራችሁ የሁሉም ሃይማኖቶች ቤተሰቦች እና ወገኖች !!

በሀገራችን ሕገ መንግሥትም ሆነ በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች የሃይማኖት ነፃነት እና እኩልነት የተረጋገጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የሃይማኖት ተቋማትም ይህንን ነፃነትና እኩልነት ሲጠቀሙ የእርስ በእርስ ግንኙነታቸውን ባከበረ፣ ሰላማዊና መተሳሰብ የሞላበት እንዲሆን የማድረግ ኃላፊነት አለባቸው፡፡

የሃይማኖት ተቋማት በአስተምህሮአቸው እና መልእክቶቻቸው ለአብሮነት፣ ወንድማማችነትና አንድነት ጉልህ አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ተቋማችን ሃይማኖቶች ለማኅበረሰብ መከባበር፣ አብሮነትና ወንድማማችነትና መተሳሰብ ያላቸውን ፋይዳ በውል ይገነዘባል። ለዚህም አበክሮ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡

በሃይማኖት ተቋማት መካከል የሚደረጉ ምክክሮች ከሌሎች ተቋማት በተለየ መልኩ ፈጣሪን ከመፍራት፣ በሥነ-ምግባርና በግብረገብ ዕሴት የሚመራ በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል፡፡

ሃይማኖት ተቋማት በውስጣቸውና ከሌሎች ጋር የሚያደርጉት ምክክር የውስጥ ጥንካሬን፣ ለርስ በርስ መተማመን እና ለጋራ ርእይ በጋራ መሥራትን ሲያጎለብት በሃይማኖቶች መካከልም መከባበርን ፣ መተባበርን እና አብሮነትን በማሳደግ ጥርጣሬንና ስጋትን የሚቀርፍ ይሆናል፡፡

ችግሩ የቆየ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንድ አንድ ግለሰቦችና ቡድኖች በማኅበራዊ ሚድያዎች ሃይማኖታዊ ውይይትን እና ሃይማኖትን በመጠበቅ ሽፋን በሚተላለፉ መልእክቶች ወሰን ያለፋ ድፍረቶች መታየት ጀምረዋል።

የዚሁ ቀጣይ ጥፋት የሆነውና ከሰሞኑ በአንድ የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ ነኝ በሚል ግለሰብ የእስልምና ሃይማኖት ነብይ በሆኑት በነቢዩ መሃመድ ሰ.ዐ.ወ ላይ ክብረ ነክ እና ኢ-ሥነ ምግባራዊ ንግግሮች መነገራቸው ተከትሎ የእስልምና እምነት ተከታዮችን ብቻ ሳይሆን ብዙዎችን ያሳዘነ ጉዳይ ሆኗል። ይህ ድርጊት ሁሉም ማህበረሰብ ሊወግዘው የሚገባ ተግባር ነው።

ጉባኤያችንም ይህ ዓይነቱ ኢ-ሥነ ምግባራዊ እና ሕገ ወጥ ተግባር የትኛውንም የሃይማኖት ተቋም የማይወክል፣ ይልቁንም የሚወገዝ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ ይወዳል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንዳንድ የኦርቶዶክስ አማኝ ነን የሚሉ ወንድሞችና እህቶች የግለሰቡን ሕገ-ወጥ ተግባር ተቋማዊ ለማድረግ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ተገቢ አለመሆኑን እና ግለሰብንና ተቋምን እንዲለዩ እናሳስባለን፡፡

በአንፃሩ አንዳንድ የእስልምና እምነት ተከታይ ነን የሚሉ ግለሰቦች ተደፈርን በሚል ስሜት የክርስትና አስተምህሮንና ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ክብረ ነክ እና ኢ-ሥነ ምግባራዊ መልዕክቶች በመተላለፋቸው የክርስትና እምነት ተከታዮችን እንዳሳዘነ እና ቅሬታዎች መኖራቸውንም አስተውለናል፡፡

እንዲህ ዓይነት የሌሎችን የሃይማኖት አስተህምሮና ሃይማኖታዊ ሥርዓትን በማኅበራዊ ሚዲያ የማነወርና የማጥላላት ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ድርጊት የትኛውንም የሃይማኖት ተቋማትን የማይወክል ነው።

ሆኖም ግን እነዚህ ኢ-ሃይማኖታዊ እና ሕገ ወጥ ተግባራት የቆዩ ሲሆኑ፥ ባለፈው ዓመት በተቋማችን ሃይማኖትን ሽፋን ያደረጉ የግጭት መንስኤ የሚሆኑ ጉዳዮችን በዳሰሳ ጥናት ከተለዩት ዋና ዋና ጉዳዮች አንዱ ነበር።

በማኅበራዊ ሚድያ የሚሰራጩ ሃይማኖትን ሽፋን ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች በጊዜ መፍትሔ ካልተበጀለት የሰላምና የጸጥታ ሥጋት እንደሚሆንና በተናጠልና በጋራ ሥራ መሰራት እንዳለበት ምክረ ሐሳብ የቀረበበት ጉዳይ መሆኑ ይታወሳል፡፡

ተቋማችን ባሉት መዋቅሮች በሚድያ አጠቃቀምና ሌሎች በዳሰሳ ጥናቱ በተለዩ ጉዳዮች ላይ ስልጠና በመስጠትና ምክከሮች በማድረግ ችግሮቹን ለመቅረፍ የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቶአል። አሁንም ይህንኑ አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

በተለይ ሰሞኑን ማህበራዊ ሚድያን በመጠቀም በአንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች የሌሎች የሃይማኖት ተቋማትን አስተምህሮ ፣ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን እና ትወፊቶችን የመንቀፍና የመዝለፍ ድርጊት ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ በመምጣቱ ጉዳዩ አሳሳቢና አፋጣኝ መፍትሔ ሊፈለግለት የሚገባ እንደሆነ ጉባዔያችን ግንዛቤ ወስዶአል፡፡

በችግሩ ወስጥ እየተሳተፉ ያሉ ወገኖች ባንድም በሌላ በሁሉም የሃይማኖት ተቋማት የሚገኙ በመሆኑ፥ ችግሩ ከተወሰኑ የሃይማኖት ተቋማት ጋር ብቻ የሚያያዝ አይደለም፡፡ በመሆኑም ለችግሩ የሰከነ፣ ሚዛናዊ፣ ፍትሐዊ እና የጋራ መፍትሔ መፈለግ ወቅቱ የሚጠይቀው ጉዳይ መሆኑን ጉባኤያችን ያምናል፡፡ በመሆኑም የሚከተለውን የጉባኤያችንን አቋም እና ምክረ ሐሳብ ማስተላለፍ እንወዳለን፦

 በማኅበራዊ ሚድያ የሌላ ሃይማኖትን አስተምህሮ እና ሃይማኖታዊ ሥርዓትን የማነወርና የማጥላላት ተግባራት ላይ እየተሳተፉ ያሉ የየትኛውም ሃይማኖት ተከታዮች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ እናሳስባለን።

 የተፈጠረውን ችግር መነሻ በማድረግ፣ በግለሰቦችና በቡድኖች በማኅበራዊ ሚድያ የሚተላለፋ አደገኛ መልእክቶችና ጉዳዩን የሚያባብሱ የድጋፍና ተቃውሞ እንቅስቃሴዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ እናሳስባለን።

 የተለያዩ ሚድያዎችን በመጠቀም የሚሰጡ መግለጫዎች የቆየውን የሕዝባችንን አብሮነት፣ መከባባርና ወንድማማችነት በሚያጎለብት መልኩ ሚዛናዊ እና ፍትሐዊ በሆነ መልኩ እንዲደረጉ እንጠይቃለን።

 በማኅበራዊ ሚድያ የሌሎችን የሃይማኖት አስተምህሮና ሃይማኖታዊ ሥርዓትን የማነወርና የማጥላላት ተግባራት የሃይማኖት ተቋማቱን በቀጥታ ባይመለከትም፤ ግለሰቦቹም ሆነ ቡድኖቹ በአንድም ሆነ በሌላ የሃይማኖት ተቋማቱ አባላት በመሆናቸው የሃይማኖት አባቶች በዚህ ጉዳይ እየተሳተፉ ያሉ የመንፈስ ልጆቻቸውን የመምከርና የመገሰጽ ኃላፊነቸውን እንዲወጡ እናሳስባለን፡፡

 ሁሉም ሃይማኖት ተቋማት አገልግሎት በሚሰጡባቸው መድረኮችና ሚድያዎች የሚተላለፉ መልእክቶች የሌሎችን ሃይማኖቶች የሚነቅፍና የሚያጠለሽ እንዳይሆንና የሰላም ፈተና እንዳይሆን እንደ ተቋምና ግለሰብ (አገልጋይ) ኃላፊነትና ተጠያቂነትን እንዲያሰፍኑ እንጠይቃለን።

 ሀገራችን በሕግና በሥርዓት የምትተዳደር በመሆኗ አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች በማኅበራዊ ሚድያ የሚሰነዝሩአቸውን ዛቻዎች ፤ የደቦ ፍርድ እና ሌሎች አፍራሽ ተግባራትን በማቆም፥ ችግሮች በሕግና በሕግ ብቻ እንዲፈቱ ጥያቄዎቻቸውን ለሚመለከታቸው የሕግ አካላት እንዲያቀርቡ እንመክራለን።

Показано 20 последних публикаций.