Shewa press


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ማንቻውንም አይነት ጥቆማ እና አስተያየቶችን ለማድረስ 👉 @Natuu8

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


አቶ ልደቱ አያለው ምህረቱ ፣ አቶ ሀብታሙ አያሌው ተሾመ ፣ አቶ ዘመድሁን በቀለ ዲዳ በአዲስ አበባ ውስጥ ያለና በስማቸው የተመዘገ ቤት ከእነ ካርታው ታግዷል።

@Showapress


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
በለንደን የሚኖሩ አማራወች ምስጋና ይገባቸል በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን መንግስት ተኮር ጭፍጨፋ የሚያወግዝ ሰልፍ አድርገዋል።

@showapress


በለንደን የሚኖሩ ፋኖዎች እና ኢትዮጲያኖች በዛሬው ዕለት ለህዝባቸው ድምፅ ሆነዋል!

@showapress


አንድነት ኃይል ነው ✊

አንድ በመሆን ለሕዝባችን፤ ሰላም ለትግላችን መቋጫ እንስጠው።

@showapress


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ጥቁር ክላሽ በገፍ ገብቷል !

#ዘመቻ_አንድነት✊

@showapress


የአንድነት ዘመቻ በጎጃም ግንባር
በትናንት 04/07/2017ዓ.ም አሽፋ ላይ በነበረ ውጊያ
ጎጃም አገው ምድር 3ኛ ክፍለጦር የማረከው መሳራያ።

@Showapress


ምን ማለት ይቻላል ?
ነፍስ በሰላም ትረፍ😭😭

@showapress


በቁጥጥር ሥር ዋሉ

እንዳልካቸዉ ዘነበ እና ሌሎች ሁለት ሰዎች ቤተክርስቲያንን አዋርደዋል በሚል በቁጥጥር ስር ዋሉ
አቶ ጽጌ ስጦታው እና አቶ ምስጢረ መዝገቡ ብለው የሚጠሩ ግለሰቦች በቅድስት ቤተክርስቲያኛችን ሥርዓተ እምነት ላይ በወንጀል የሚያስጠይቅ ድርጊት ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው በሕግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡

እራሳቸውን ‹‹መሪጌታ›› ጽጌ ስጦታው እና ‹‹መሪጌታ›› ምስጢረ መዝገቡ ብለው የሚጠሩ ግለሰቦች በቅድስት ቤተክርስቲያኛችን ሥርዓተ እምነት ላይ በወንጀል የሚያስጠይቅ ድርጊት ፈጽመዋል  በሚል  ተጠርጥረው የወንጀል አቤቱታ በቀረበባቸው መሠረት የፌደራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ በዛሬው ቀን ተጠርጣሪዎችን በሕግ ቁጥጥር ሥር በማዋል የወንጀል ምርመራውን በማጣራት ላይ እንደሚገኝ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ ኮሚቴ አባል ጠበቃ አያሌው ቢታኔ ለኢኦተቤ ቴቪ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ጠበቃ አያሌው አያይዘው እንደገለጹት ከግለሰቦቹ በተጨማሪ   እንዳልካቸው ዘነበ  የተባለ ግለሰብ  በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያናችን ላይ  ፈጽሞታል ተብሎ በተጠረጠረበት ስም ማጥፋት በቅርቡ  በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውሎ  ቃሉን  ሰጥቶ   በዋስትና መለቀቁን እና በአቃቤ ሕግ በኩልም የወንጀል አቤቱታ ክስ ቀርቦ በሒደት ላይ  እንደሚገኝ አያይዘው ተናግረዋል።

የሕግ ባለሙያዎች ዐቢይ ኮሚቴ አባል ጠበቃ አያሌው ቢታኔ ለኢኦተቤ ቴቪ በሰጡት መረጃ  ኮሚቴው  ወደ ፊት ጉዳዩን ተከታትሎ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጸዋል።

© ኢኦተቤ ቴቪ

@Showapreas


የአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለጦር ሺፈራው ገርባው ብርጌድ አዲስ ፋኖዎችን አስመርቋል ።

@showapress


በለጠ ሞላ በህዝብ ተመርጦ ፓርላማ የገባውን ደሳለኝ ጫኔን ለመዝለፍ መሞከሩ ፈገግ ያሰኛል¡

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ማለት በ ህይወቱ ተወራርዶ ለወጣበት ህዝብ በፓርላማ ድምፅ የሆነ ብቸኛው እንቁ የ አማራ ጀግና ነው።

@showapress


አብን ከዚህ በኋላ ከመኖሩ ይልቅ ባለመኖሩ የአማራን ሕዝብ የሚጠቅም ፓርቲ ነው''

ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ

@showapress


ከአራቱም ግዛቶች የተሰጠ የጋራ አቋም።

@showapress


ሰከላ ከተማን የአማራ ፋኖ በጎጃም በዚህ ሰዓት ተቆጣጥሯል።

#ዘመቻአንድነት
@showapress


በሰሜን ሸዋ የቀጠለዉ እገታና አንድምታዉ ዝምታዉ ለምን?
(ታዬ ደንደአ )
➖➖➖
ሰሜን ሸዋ ኦሮሚያ ክልል... እጅግ አደገኛ የእገታ ወንጀል ለዓመታት ቀጥሏል። የዞኑ ነዋሪዎች በየተራ ከከተማና ከገጠር ይታገታሉ። እገታዉ በተመሳሳይ በመንገደኞች ላይም ሲፈፀም ዛሬ ደርሷል። ለታጋቾች ማስለቀቂያ በሚሊየኖችና በመቶ ሺዎች ይጠየቃል። የቻለ ጥሪቱን ሽጦ ወይም ዘመድ አዝማድ አስቸግሮ በመክፈል ይለቀቃል። ከፍያዉ ደግሞ ከካሽ ባሻገር በባንኮች ጭምር እንደሚፈፀም ኢሰመኮም አረጋግጧል። መክፈል ያልቸለዉ እንደሚገደልም ታዉቋል። በዚህ ምክንያት ብዙዎች ጥሪታቸዉን በመነጠቅ ለከባድ ችጋር ተጋልጧል። በርካቶችም ህይወታቸዉን አጥቷል።

ትላንትም በሰሜን ሸዋ ወረ-ጃርሶ ወረዳ የተለመደዉ አሳዛኝ የእገታ ወንጀል መፈፀሙን ሰምተናል። አንድ የመንገደኞች አዉቶቢስ ላይ ተኩስ ተከፍቶ በርካቶች ሲቆስሉ ከአስር በላይ ንፁኃን ዜጎች መገደላቸዉ ተዘግቧል። ታፍነዉ የተወሰዱ ስለመኖራቸዉም ይነገራል። ዜጎች በዚህ ሁኔታ መንገድ ላይ መቅረታቸዉ እጅግ ያሳዝናል። የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ያለበት አካል ግን የፓርክና የሪዞርት ግንባታ ላይ አተኩሯል።

ከሁለት ቀን በፊት አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር ሁለት መቶ ብር ጉቦ መቀበሉ ትልቅ ዜና ነበር። ኢቲቪና ፋናም "ሌብነት ላይ ለተጀመረዉ ትግል አበረታች እርምጃ" ብለዉታል። ከሳምንት በፊትም "ሀሰተኛ መረጃን ለማጋለጥ" ጥረዋል። ጉዳዩ የማይመለከታቸዉ ባለስልጣናት ጭምር በየተራ ወጥተዉ የብርቱካን ድራማ "ኢትዮጵያን ለመግደል የተሸረበ ሴራ ነዉ" ብለዉናል። የበርካታ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈዉና አካል ያጎደለዉ የትላንቱ ወንጀል ግን ዝም ተብሏል። የሁለት መቶ ብር ጉቦ ያንበገባቸዉ ኢቲቪና ፋና በሚሊዬኖች እየዘረፈ ብዙ ዜጎችን ለመከራ ያጋለጠዉ ተደጋጋሚ የእገታ ወንጀል ምንም ያልመሰላቸዉ ለምን ይሆን? የኢትዮጵያ ህዝብ በሀሰተኛ መረጃ እንዳይጎዳ በዚያ ልክ የተረባረቡት ሚዲያዎችና ባለስልጣናት ንፁኃን ዜጎች በየግዜዉ በመታገት ሲገደሉና አካላቸዉን ሲያጡ ለምን አያማቸዉም? በድራማዉ የታሰበለት የኢትዮጵያ ህዝብ የትላንቱን ተጎጂዎች አያጠቃልልም እንዴ?

ተጨማሪ ጥያቄዎችም አሉ። መጠኑ ቢለያይም በኦሮሚያ የነዋሪዎች እገታ በየቦታዉ ተለምዷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በአብዛኛዉ ቅንጦት ሆኗል። ሰላም ሳይረጋገጥ ስለብልፅግና መስበክም ቀልድ ይሆናል። ይሁንና በዚህ ሁሉም ይመሳሰላል። በመንገደኞች እገታ ላይ ግን ግልፅ ልዩነት ይታያል። ከመንገዶች ሁሉ የጎጃም መስመር በዋናነት ተደጋጋሚ ጥቃቶችን አስተናግዷል። የዚህ መስመር ላይ ብዙዎች ተዘርፈዉ ለመከራ ሲጋለጡ በርካቶች ህይወታቸዉንና አካላቸዉን አጥተዋል። ሚስጢሩ ምንድ ነዉ? አጋቹስ በትክክል ማን ይሆን? ተመሳሳይ ወንጀል በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ቦታ ላይ ለምን ይፈፀማል? ኃላፊነት ያለበት አካልስ ለምን ዝም ይላል? ይህ አደገኛ ወንጀል በመንግስት ሚዲያ የማይዘገበዉስ ለምንድነው? በርግጥ የእገታዉ ዓላማ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ነዉ ወይስ የፖለቲካ ቁማር አለበት? ምናልባት የፖለቲካ ቁማር ኖሮበት ዓላማዉ ኦሮሞንና አማራን ለማጣላት ከሆነ ውጤቱ ማንን ይጠቅማል? ኢቲቪና ፋና ልክ እንደብርቱካን "ድራማ" ተረባርበዉ ቢያጋልጡትስ?

ለሟች ወገኖቻችን እጅግ አዝኛለሁ! የቆሰሉትም ፈጥነዉ ይድኑ ዘንድ እመኛለሁ! ዋናዉ ጉዳይ ግን የፖለቲካ ቀዉሱንና እንቆቅልሹን መፍታት መሆኑን ልብ እንበል እላለሁ!

@showapress


(ዘመቻ አንድነት በጎጃም ግንባር|፲፱ኛ ቀን)

፩. 5ኛ ክፍለጦር ወርቅ አባይ ብርጌድ 83 የሚሊሺያ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን ተቀላቅለዋል።

፪. ባህርዳር ላይ!

ሀ- የአማራ ፋኖ በጎጃም ፩ኛ ክፍለ ጦር በሰጠው ልዩ ኦፕሬሽን ባህርዳር ብርጌድ የቦንብ እና የሞርተር ጥቃት ተፈፅሟል። በቦንብ ጥቃቱ ቀበሌ 16 ስታዲየም አካባቢ ጥበቃ ላይ የነበሩ የአገዛዙ ጭፍሮች ሙትና ቁስለኛ ሁነዋል።

ለ- ዘሪሁን 13 በመጠቀም ቆላ ፅዮን ማርያም ቀበሌ 11 ስራ አመራር መሰብሰቢያ አካባቢ ሊሰበሰብ የነበረው ካድሬ እንዲፈረጥጥ ተደርጓል።

ሐ- በሰባታሚት በኩል ደግሞ የሞርተር ጥቃት በመፈፀም በአገዛዙ ሊሰራ የታሰበው ፖለቲካዊ ፕሮፓጋንዳ እንዲከሽፍ ተደርጓል።

የቦንብ ጥቃቱ ከትላንት ምሽት ጀምሮ ነው የተፈፀመው።

[አማራ ፋኖ በጎጃም]
መጋቢት 28/2017 ዓም

@Showapress


መከላከያ ደምስሸዋለሁ ያለውን የሽኔ አመራር የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በፀጥታ ዘርፍ ሹመት ሰጥቶታል።

@showapress


"ይህ የመጨረሻው የሚያነባ የአማራ ትውልድ ይሆናል"

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ መግለጫ!

ባለፉት 500 ዓመታት ለነጋሪም፣ ለሰሚም ለፀሐፊም ያስቸገሩ ለታሪክ ገፆች የከበዱ ፍጅቶች በአማራ ህዝብ ላይ ተፈፅመዋል። በተለይ ባለፉት ሰማንያ ዓመታት ውስጥ ጠላቶቻችን አማራ አልቦ ምድር ሊፈጥሩ ጥረዋል። የጠላቶቻችን የጦር መኳንንት አማራ የሌለባት ኢትዮጵያን ለአለቆቻቸው ሊያስረክቡ ቃል ገብተው ሊፈፀሙት ተንቀሳቅሰዋል። በመሆኑም ሚሊዮን አማራዎች በዚህ እቅድ የተነሳ አልቀዋል። ይህንን ግፍ ለማስቆም ቀደምቶቻችን በተለያየ ጊዜ የተሳካም ያልተሳካም የጀግንነትና የአርበኝነት ስራ ሰርተዋል። በነዚህ ሰማንያ ዓመታት ውስጥ አንድ የአማራ ጭንቅላት ተቆርጦ ሰላሳ ብር ተሽጧል። የአማራን አንገትበላይ በብዛት ያመጣ ባንዳ ለስኬቱ ተሸልሟል። አካላችንም መሬታችንም እየተቆራረጠ ተጥሏል፤ ተሸጧልም። በዚህ ሁሉ ረጅም ዘመን ውስጥ አማራ ፈጅ ጥፋቶችና ክፋቶች ምንጫቸው አንድ በመሆኑ የዚሁ ተቀጥላና ዲቃላ ሕዝብ አውዳሚ መንፈስ የወለደው የአብይ አህመድ የጥፋት ዘመን ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ/ም ሰባተኛ ዓመቱን አስቆጥሯል::

አማራም ከአምስት መቶ ዓመት የውድቀትና የውርደት ዘመን በኋላ በዚህኛው ትውልድ ጊዜ ነቅቶ ተደራጅቶ ታጥቆና የመከራ መሻገሪያ ርዕዮቱን ሰንቆ የተነሳ ሲሆን ከሰባት መቶ ዓመታት በላይ የከበዱ ሰባት ዓመታት እያሳለፈ ይገኛል። አብይ አህመድ የአማራ ህዝብ አንድ አንገት ኖሮት በአንድ ጊዜ በአንድ ቅፅበት በአንዳች ሰይፍ ቆርጦ ጥሎት ቢገላገል ደስታውን መሸከም የማይችል የ21ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያዊ ካሊጉላ ነው። በአማራ ህዝብ የሺህ ዓመታት ታሪክ ጉዞ በተለያየ ጊዜ ብቅ እያለ ሲያደማንና ሲያወድመን የኖረ መንፈስ አሁንም በአብይ አህመድ ዘመን አብይን ፈጥሮ በአብይ አህመድ በኩል እየወጋንና እየጨፈጨፈን ይገኛል።

ጉዳዩ ተራ ፖለቲካዊ ግብግብ አይደለም። የአማራ ህዝብ እየተከላከለ ያለው ጦርነት ጥልቅ የማንነት የታሪክና የእሴት ጦርነት ነው። ከፖለቲካ ትግል አለፍ ያለ ውስብስብ ጦርነት ነው። ጠላቶቻችን አማራ አልባ ኢትዮጵያን ሊፈጥሩ ለራሳቸው ቃል እንደገቡት ሁሉ ተመሳሳይና አንድ መንፈስ የወለደው አብይ አህመድና ዘመኑ አማራ የሌለባት ኢትዮጵያን ሊፈጥሩ አየተጉ ይገኛሉ። ይህ የጥፋት ፕሮጀክት ነው ዛሬ መጋቢት 24/2017 ዓ/ም ሰባት ዓመት የሞላው!

ሰባት የውድመትና የመንቃት፣ የደምና የድል፣ የመውደቅና የመነሳት፣ የእልቂትና ጠላትን በኩራትና በጀግንነት የመጋፈጥ ተጋፍጦም የማሸነፍ አስገራሚ አመታት!

ሰባት በደምና በድል የተነከርንባቸው፣ በእንባና ሳቅ የታጠብንባቸው፣ ከሞት ውቅያኖስ ተስፋ፣ ከእልቂት ባህር ድል የቀዳንባቸው ግራጫ አመታት!

አሁን የአማራ ልጆች ተነስተናል ነቅተናል ተደራጅተናል ታጥቀናል ድልን ለምደናል። ህልውናችንን የምናረጋግጥበት ዘመን እሩቅ እንደማይሆን ከተረዳንም ውለን አድረናል። እንደ ህዝብ ለእልቂት ሳይሆን ለድል መፈጠራችንን አምነናል። ውስጣዊ አማራዊ አንድነታችን በመዋቅር ደረጃ ማረጋገጥ ብቻ ይቀረናል። ይህም በቅርቡ እውን ይሆናል። ከዛማ ማን ከፊታችን ይቆማል? ማንም። ተራሮች እንኳን ቀና ብለው አያዩንም። ውሃው ይጎድልልናል፤ ነፋስም ይታዘዘናል።

ይህ የመጨረሻው የሚያነባ ትውልድ ይሆናል።

ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !
ድላችን በተባበረ ክንዳችን

የአማራ ፋኖ በሸዋ
የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር
የአማራ ፋኖ በወሎ(ቤተ-አማራ)
የአማራ ፋኖ በጎጃም

ዘመቻ አንድነት ግለቱን ጠብቆ ይቀጥላል

መጋቢት 24/2017 ዓ/ም

@showapress

Показано 17 последних публикаций.