የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር መግለጫ
የትግራይ ሐይል አዛዦች ያስተላለፉት ውሳኔ ተከትሎ አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ መጥራቱን የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ። የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ማምሻው ባወጣው መግለጫ የትግራይ ሐይሎች ከፍተኛ አዛዦች "ከተልእኳቸው ውጭ ለአንድ ሕገወጥ ቡድን ወግነው ግዚያዊ አስተዳደሩን የማፍረስ፣ ስርዓት አልባነት የማንገስ እና ሰራዊት የመበተን ግልፅ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆናቸውን አሳውቀዋል" ብሏል።
የትግራይ ሐይል አዛዦች በዛሬው ዕለት ያስተላለፉትን ውሳኔ ግዚያዊ አስተዳደሩ የማያውቀውና "ሕጋዊ ይሁን ሞራላዊ ቅቡልነት የሌለው" ሲል ያመለከተው የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር መግለጫ፤ ከዚህ በተጨማሪ የፕሪቶርያ ውልንም ለአደጋ የሚያጋልጥ እና ሃላፊነት የጎደለው ብሎታል። ካለፈው ጥር 10 ቀን 2017 ዓመተምህረት ጀምሮ ስብሰባ ሲያደርጉ የሰነበቱ ሁለት መቶ ገደማ የሚሆኑ የትግራይ ሐይሎች ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ በሰጡት መግለጫ በዶክተር ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ክንፍ በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ያለው ሃምሳ ሲደመር አንድ ድርሻ እንዲረከብ እንደሚሹ አስታውቀዋል። ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ያሉ ታጣቂዎች በትግራይ ሰላም እና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ስር እንዲሆኑ፥ ከዚህ ውጪ በሆነ ላይ ግን እርምጃ ይወሰዳልም ብለዋል።
የወታደራዊ መሪዎቹ መግለጫ በንባብ ያቀረቡት ኮነሬል ገብረ ገብረፃዲቅ "የደከመ እና ተልእኮው የዘነጋ ግዚያዊ አስተዳደር እንዲጠናከር የሚተኩ አመራር ተተክተው ሊስተካከል ይገባዋል። በግዚያዊ አስተዳደሩ ማቋቋሚያ መሰረት ሓምሳ ሲደመር አንድ ድርሻ ያለው፣ የፕሪቶርያ ውል ተደራዳሪ እንዲሁም 14ተኛ ጉባኤ ያደረገ ህወሓት ግዚያዊ አስተዳደር ለማስተካከል የወሰነው ውሳኔ ያለ ያለመዘግየት ተግባራዊ እንዲሆን ድጋፋችንን እንገልፆለን" ሲሉ አስታውቀዋል።
ይህ ተከትሎ መግለጫ ያወጣው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራዉ የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር፥ የትግራይ ሐይል አዛዦች ውሳኔ የህዝብ ችግርን የሚያባብስ እና የጦርነት እና ስርዓት አልበኝነት አዋጅ ነዉ ሲል የኮነነው ሲሆን፥ በመሆኑም በትግራይ ያሉ የፀጥታ ሐይሎች ውድቅ እንዲያደርጉት እንዲሁም ከዚያ የሚመጣ ትእዛዝ ተግባራዊ እንዳታደርጉ ሲልም ጥሪ አቅርቧል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ከውሳኔ በዘለለ በችኮላ ወደታች ለማውረድም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፥ ይህ በአስቸኳይ ይቁም ሲልም ግዚያዊ አስተዳደሩ ገልጿል።
ዘገባ፤ ሚሊዮን ኃይለሥላሴ ከመቀሌ
@Ethionews433 @Ethionews433
የትግራይ ሐይል አዛዦች ያስተላለፉት ውሳኔ ተከትሎ አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ መጥራቱን የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ። የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ማምሻው ባወጣው መግለጫ የትግራይ ሐይሎች ከፍተኛ አዛዦች "ከተልእኳቸው ውጭ ለአንድ ሕገወጥ ቡድን ወግነው ግዚያዊ አስተዳደሩን የማፍረስ፣ ስርዓት አልባነት የማንገስ እና ሰራዊት የመበተን ግልፅ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆናቸውን አሳውቀዋል" ብሏል።
የትግራይ ሐይል አዛዦች በዛሬው ዕለት ያስተላለፉትን ውሳኔ ግዚያዊ አስተዳደሩ የማያውቀውና "ሕጋዊ ይሁን ሞራላዊ ቅቡልነት የሌለው" ሲል ያመለከተው የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር መግለጫ፤ ከዚህ በተጨማሪ የፕሪቶርያ ውልንም ለአደጋ የሚያጋልጥ እና ሃላፊነት የጎደለው ብሎታል። ካለፈው ጥር 10 ቀን 2017 ዓመተምህረት ጀምሮ ስብሰባ ሲያደርጉ የሰነበቱ ሁለት መቶ ገደማ የሚሆኑ የትግራይ ሐይሎች ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ በሰጡት መግለጫ በዶክተር ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ክንፍ በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ያለው ሃምሳ ሲደመር አንድ ድርሻ እንዲረከብ እንደሚሹ አስታውቀዋል። ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ያሉ ታጣቂዎች በትግራይ ሰላም እና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ስር እንዲሆኑ፥ ከዚህ ውጪ በሆነ ላይ ግን እርምጃ ይወሰዳልም ብለዋል።
የወታደራዊ መሪዎቹ መግለጫ በንባብ ያቀረቡት ኮነሬል ገብረ ገብረፃዲቅ "የደከመ እና ተልእኮው የዘነጋ ግዚያዊ አስተዳደር እንዲጠናከር የሚተኩ አመራር ተተክተው ሊስተካከል ይገባዋል። በግዚያዊ አስተዳደሩ ማቋቋሚያ መሰረት ሓምሳ ሲደመር አንድ ድርሻ ያለው፣ የፕሪቶርያ ውል ተደራዳሪ እንዲሁም 14ተኛ ጉባኤ ያደረገ ህወሓት ግዚያዊ አስተዳደር ለማስተካከል የወሰነው ውሳኔ ያለ ያለመዘግየት ተግባራዊ እንዲሆን ድጋፋችንን እንገልፆለን" ሲሉ አስታውቀዋል።
ይህ ተከትሎ መግለጫ ያወጣው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራዉ የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር፥ የትግራይ ሐይል አዛዦች ውሳኔ የህዝብ ችግርን የሚያባብስ እና የጦርነት እና ስርዓት አልበኝነት አዋጅ ነዉ ሲል የኮነነው ሲሆን፥ በመሆኑም በትግራይ ያሉ የፀጥታ ሐይሎች ውድቅ እንዲያደርጉት እንዲሁም ከዚያ የሚመጣ ትእዛዝ ተግባራዊ እንዳታደርጉ ሲልም ጥሪ አቅርቧል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ከውሳኔ በዘለለ በችኮላ ወደታች ለማውረድም እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፥ ይህ በአስቸኳይ ይቁም ሲልም ግዚያዊ አስተዳደሩ ገልጿል።
ዘገባ፤ ሚሊዮን ኃይለሥላሴ ከመቀሌ
@Ethionews433 @Ethionews433