“ዘለንስኪ ይቅርታ ይጠይቀኝ“ ትራምፕ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የዩኬሬኑ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ በዋይት ሃውስ ያደረጉት ዱላቀረሽ እሰጣገባ አሁንም የዓለምን ትኩረተ እንደሳበ ነዉ።
ይህን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የዩኬሬኑ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ በዋይት ሃውስ ላሳየው የማይገባ ድርጊት በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቃቸው እንደሚፈልጉ ብሉምበርግ አስነብቧል። ፕሬዝዳንቱ ይህን ማለታቸው ደግሞ በበርካቶች ዘንድ ግርምትን እያጫረ ነዉ።
ዘለንስኪ በኋይት ሀዉስ ባደረገዉ ዉይይት ሰብዓዊ ክብር ተነፍጎታል የቃላት ዉረፋና ጊዜዉን ያልጠበቁ ጥያቄዎች ማስተናገዱ አግባብ አደለም በሚል በርካቶች የሶሻል ሚዲያ ርዕስ አድርገዉታል። ይህ ባልረገበበት ሁኔታ የትራንፕ ጥያቄ ደግሞ ተአምር ማሰኘቱ ተደምጧል።
ዘለንስኪ ከዋይት ሀውስ ከወጡ በኋላ በቀጥታ ያመሩት ወደ እንግሊዝ ሲሆን 2.6 ቢሊዮን ዶላር ተበድረው መመለሳቸውም ተሰምቷል።
የአውሮፓ ህብረት ደግሞ በመጪው አርብ የ100 ቢሊዮን ዶላር ለዩክሬን ድጋፍ ለማድረግ አቅዷል ሲሉ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ተናግረዋል።
በ-ማህሌት ግርማ
@Ethionews433 @Ethionews433
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ የዩኬሬኑ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ በዋይት ሃውስ ያደረጉት ዱላቀረሽ እሰጣገባ አሁንም የዓለምን ትኩረተ እንደሳበ ነዉ።
ይህን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የዩኬሬኑ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ በዋይት ሃውስ ላሳየው የማይገባ ድርጊት በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቃቸው እንደሚፈልጉ ብሉምበርግ አስነብቧል። ፕሬዝዳንቱ ይህን ማለታቸው ደግሞ በበርካቶች ዘንድ ግርምትን እያጫረ ነዉ።
ዘለንስኪ በኋይት ሀዉስ ባደረገዉ ዉይይት ሰብዓዊ ክብር ተነፍጎታል የቃላት ዉረፋና ጊዜዉን ያልጠበቁ ጥያቄዎች ማስተናገዱ አግባብ አደለም በሚል በርካቶች የሶሻል ሚዲያ ርዕስ አድርገዉታል። ይህ ባልረገበበት ሁኔታ የትራንፕ ጥያቄ ደግሞ ተአምር ማሰኘቱ ተደምጧል።
ዘለንስኪ ከዋይት ሀውስ ከወጡ በኋላ በቀጥታ ያመሩት ወደ እንግሊዝ ሲሆን 2.6 ቢሊዮን ዶላር ተበድረው መመለሳቸውም ተሰምቷል።
የአውሮፓ ህብረት ደግሞ በመጪው አርብ የ100 ቢሊዮን ዶላር ለዩክሬን ድጋፍ ለማድረግ አቅዷል ሲሉ የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ተናግረዋል።
በ-ማህሌት ግርማ
@Ethionews433 @Ethionews433